FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Sunday, June 30, 2013

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመጀመሪያው ጋዜጣዊ መግለጫ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመጀመሪያው ጋዜጣዊ መግለጫየቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ የተኳቸው የኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሥልጣን ላይ በወጡ በዘጠነኛ ወራቸው ከአገር ውስጥ ጋዜጠኞች ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በመገናኘት፣ በአጠቃላይ የአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባለፈው ዓርብ ማለዳ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
“ጥያቄ ለማቅረብና ማብራሪያ በመሻት በመምጣታችሁ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡ ከዚሁ ቀጥሎ የምትፈልጉትን ጥያቄ እንደትጠይቁ ዕድል እሰጣለሁ፤” በሚል የመግቢያ ንግግር ጋዜጣዊ መግለጫውን የጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ የፈጀ ቆይታ ከጋዜጠኞች ጋር አድርገዋል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ የተገኙ ከ20 በላይ ጋዜጠኞች ያገኙትን ዕድል በመጠቀም በአገሪቱ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ በተለይም በቅርብ በተከሰተው የዓባይ ግድብ ውዝግብ፣ በሙስናና በሌሎች ጉዳዮች ላይ በርካታ ጥያቄዎችን በማቅረብ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ዝርዝር ምላሽ ሰምተዋል፡፡ በዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት ማብራሪያ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ኢኮኖሚያዊና ተያያዥ ጉዳዮች
ከ2005 ዓ.ም. አጋማሽ በኋላ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ የአክሲዮን የንግድ ድርጅቶች ላይ የጣለው የዲቪደንድ ታክስ (የትርፍ ድርሻ ክፍፍል ላይ የሚጣል ታክስ) ጉዳይ በመጀመሪያ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበ ጥያቄ ነበር፡፡
የአገሪቱ የታክስ ሕግ የተጠቀሰውን የታክስ ዓይነት አስመልክቶ በተከፋፈለ የአክሲዮን ድርሻ ትርፍ ላይ የአሥር በመቶ ታክስ የሚጥል መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በአክሲዮን የተቋቋሙ ድርጅቶች በአጠቃላይ የአሥር በመቶ ታክሱን የትርፍ ድርሻ ክፍፍል አደረጉም አላደረጉም በአጭር ጊዜ ሊከፍሉ ይገባል በሚል ባወጣው መመርያ፣ የንግዱ ኅብረተሰብን ሲያጉላላና ሲያከራክር ቆይቷል፡፡ ታክስ ባለሥልጣኑ ባወጣው መመርያ መሠረት ድርጅቶቹ የተጠቀሰውን ታክስ ወደኋላ ለአምስት ዓመታት በማስላት እንዲከፍሉ በመወሰኑ የተነሳ፣ ድርጅቶቹ በጉዳዩ ላይ ያነሱት የሕግ ጥያቄ ሳይመለስ ቅጣትን ፍራቻ ክፍያ እየፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ የዚህን ታክስ አግባብነት የተጠየቁት አቶ ኃይለ ማርያም ተከታዩን ብለዋል፡፡
“ከትርፍ ድርሻ የሚከፈል ታክስ የሚጠየቀው የትርፍ ድርሻው ከተከፈለ ብቻ ነው፡፡ የትርፍ ድርሻው ሳይከፋፈል ለኢንቨስትመንት ከዋለ ታክስ አይከፈልበትም፡፡ ይህ የቆየ የመንግሥት አቋም ነው፤” ብለዋል፡፡
በታክስ ባለሥልጣኑና በንግዱ ኅብረተሰብ መካከል የተፈጠረው ክርክር የትርፍ ድርሻው ተመልሶ ለኢንቨስትመንት ውሏል? በሚል ጥያቄ ላይ መሆኑን አቶ ኃይለ ማርያም ከገለጹ በኋላ፣ መጣራት ያለበት የትርፍ ድርሻው ለባለሀብቶች ተከፋፍሏል ወይስ ለኢንቨስትመንት ውሏል የሚለው እንደሆነና ይህ እየተሠራ መሆኑን አሳውቀዋል፡፡
ስህተቱን የሠራው መንግሥት መሆኑ ከተረጋገጠ በንግዱ ኅብረተሰብ ላይ ለደረሰው መጉላላትና ጥቅም ማጣት መንግሥት ይቅርታ ይጠይቃል? የሚል ተያያዥ ጥያቄ ቀርቦላቸው፣ “ስህተት መኖሩን ካረጋገጥን ይቅርታ የማንጠይቅበት ምክንያት የለም፤” ብለዋል፡፡
ጉዳዩ አከራካሪ እንደሆነ በመጠቆምም አንዳንዱ ትርፉን ተቀብሎ መክፈል የማይፈልግ መኖሩን፣ ነገር ግን ለኢንቨስትመንት የዋለም እንደሚገኝ እንደሚገነዘቡና ይህንን ማጣራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ዕድገት ዙሪያ ከዚህ ቀደም ሲጠራጠሩ የነበሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ዕድገቱን ወደ መቀበል መምጣታቸውን፣ ነገር ግን እንደ የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ያሉ ተቋማት አሁንም የሚያወጧቸው መረጃዎች አሉ፡፡ ለአብነትም ዘንድሮ ይመዘገባል ብለው የገመቱት የኢትዮጵያ ዕድገትና የመንግሥት ግምት አሁንም የተለያዩ መሆናቸውን በተመለከተ፣ መንግሥትም ሌሎች ተቋማትም የሚግባቡበት በኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ኢንቨስትመንት መኖሩንና በዚህ መሀል የገንዘብ ፖሊሲውን በማጥበቅ የዋጋ ንረትን መዋጋት የሚለው የመንግሥት አቋም ግጭት የለበትም ወይ? እንዲሁም ባለፈው ዓመት የታየው የግብርና ምርት ዝቅተኝነት፣ በተመሳሳይም የኢንዱስትሪው ዘርፍ ዝቅተኛ አፈጻጸምን ከግምት በማስገባት ባለ ሁለት አኀዝ ዕድገት ዘንድሮ መጠበቅ አይከብድም ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡
በሰጡት ምላሽም፣ “ላለፉት 11 ዓመታት በአይኤምኤፍና በኢትዮጵያ መንግሥት የዕድገት ትንበያ ዙሪያ ልዩነቶች ነበሩ፡፡ ወደ ትክክለኛው መረጃ ስንመጣ ግን የእኛን መረጃ ሲያስቀምጡ ነው የኖሩት፡፡ የለመድነው ነገር ዛሬ ቢደገም ምን አዲስ ነገር አለው፤” ብለዋል፡፡ በማከልም፣ “ግምት ግምት ነው ግምቱ ወደ እውነት መጠጋት ግን አለበት፤” በማለት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግምት ሁሌም ወደ እውነት የተጠጋ እንደነበርና አሁንም እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
ባለፈው ዓመት 8.5 በመቶ ዕድገት እንዲመዘገብ ምክንያት የሆነው ግብርናው ያሳየው የ4.9 በመቶ ዝቅተኛ አፈጻጸም መሆኑን፣ በዚሁ ዓመት ተስተውሎ የነበረው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ዝቅተኛ አፈጻጸም የመነጨው በጥቃቅንና አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት ወደ 13 በመቶ በመውረዱ እንጂ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በ18.6 በመቶ አድጎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
የጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ያሳየው ዝቅተኛ አፈጻጸም አጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ወደኋላ እንደሳበው፣ ነገር ግን መንግሥት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ላይ በወሰደው ዕርምጃ ውጤት በመታየቱ፣ ከዚህ ባለፈም የግብርና ዘርፍ የሰብል ምርት ዕድገት ብቻ ስድስት በመቶ ማደጉንና ከስታስቲክስ ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ ከሌሎቹ የግብርና የዘርፍ ዓይነቶች ዕድገት ጋር ሲደመር፣ ቢያንስ የግብርና ዕድገቱ ሰባት በመቶ ስለሚሆን ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የመንግሥት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እያለ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር የሚለውን በተመለከተ ምላሽ የሰጡት፣ ከዋጋ ንረት ጋር በተያያዘ ሁለት ዓይነት አስተሳሰቦች መኖራቸውን በማስቀደም ነበር፡፡
“አንደኛው ዕድገት እያስመዘገቡ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር ሲሆን፣ ሁለተኛው ዕድገትን ገቶ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር ይገባል የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ ይህ ሁለተኛው አስተሳሰብ በምሥራቅ እስያ አገሮች ልምድ አልሠራም፡፡ ዕድገት እየመጣም የዋጋ ንረትን ተቆጣጥሮ መሄድ ይቻላል የሚለው በተግባር የተረጋገጠ ነው፡፡ በእኛም ሁኔታ ዕድገት እያስቀጠልን የዋጋ ንረትን ማውረድ ችለናል፤” ብለዋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት በሰጡት ማብራሪያ ዋናው ነገር የዋጋ ንረቱ ምንጭ እንደየአገሩ የሚለያይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ባደጉ አገሮች ያለው የዋጋ ንረት ምንጭና ግፊት ባላደጉ አገሮች ካለው ጋር ፈጽሞ እንደሚለያይ ተናግረዋል፡፡
“የእኛ መነሻ ምንድን ነው? የእኛ የምግብ ዋጋ ንረት ነው መነሻው፡፡ ዋናውና ትልቁ የግብርና ምርት ላይ ትንሽ ፈቅ ሲባል ዋጋው ይወርዳል፡፡ አርሶ አደሩ ዋጋ ወደቀ ብሎ መንጫጫት ይጀምራል፡፡ ስለዚህ መነሻው እንጂ አጠቃላይ ቲዎሪው አይደለም የሚወስነው፤” ብለዋል፡፡
ገንዘብ ወደ ኢኮኖሚው ውስጥ ሲገባ የሚያመጣው የዋጋ ግሽበትና በአቅርቦት ምክንያት የሚመጣውን ግሽበት መንግሥት ከፋፍሎ መመልከቱን አቶ ኃይለ ማርያም የገለጹ ሲሆን፣ “ገንዘብ በኢኮኖሚው ውስጥ በሚገባበት ወቅት ግሽበት አይፈጥርም ሳይሆን፣ አቅርቦት በሚጎልበት ወቅት የዋጋ ንረቱ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚጨምር አይተናል፡፡ ስለዚህ አቅርቦቱን በማሻሻል የዋጋ ንረቱን መቆጣጠር ይቻላል፤” በማለት አስረድተዋል፡፡
በማጠናከርም ግሽበትን ለመፍታት አቅርቦቱን ማሻሻል ማለት በሌላ በኩል ግብርናን ማሳደግ መሆኑንና ይህም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደ መግደል እንሚቆጠር በመግለጽ ይህ ሊሆን የቻለው ከኢኮኖሚያዊ አወቃቀሩ የተነሳ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
የግብፅ ጉዳይ
በኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምክንያት የኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ስለተከሰተው አለመግባባትና ችግሩን ለመቅረፍ ያለው ዕድል፣ የሁለቱ አገሮች አለመግባባትን ተከትሎ በግብፅ በኩል ስለታየው የጦርነት ጉሰማ አካሄድና የባለሙያዎች ቡድን ያቀረበውን ሪፖርት በተመለከተ ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት አስተያየት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ተፋሰሱን በጋራ የመጠቀም ፅኑ እምነትን አጉልተው አንፀባርቀዋል፡፡
“ፍላጎታችን በጋራ ብልፅግና ላይ የተመሠረተ ትብብር ይኑር የሚል ነው፡፡ ይህ አቋማችን ይቀጥላል፡፡ ይህንን አቋም የዓለም ኅብረተሰብ በአጠቃላይ እየተቀብለው ነው፤” ብለዋል፡፡
ሰጥቶ በመቀበል መደራደር ላይ የተመሠረተ አቋም በኢትዮጵያ በኩል መኖሩን በመግለጽ፣ የባለሙያዎቹ ቡድን ያቀረበው ሪፖርት ግድቡ የተፋሰሱን አገሮች ሊጠቅም እንደሚችል ያለማወላዳት እንዳስቀመጠ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ የቡድኑ ሪፖርት ሌሎች የሰጣቸው የመፍትሔ ሐሳቦች መኖራቸውን ከዚህም ውስጥ የግድቡ ዲዛይንን እንደሚመለከት ገልጸዋል፡፡
ይህንንም ሲያብራሩ የግድቡ ኮንትራት የኢንጂነሪንግን ግዥና ግንባታን ያጠቃለለ መሆኑን፣ ይህም ማለት የመጀመሪያው ዲዛይን ብቻ ተሠርቶ ቀጣይ ዙር ዲዛይኖች በዚህ ላይ መሠረት ተደርገው እንደሚሠሩ፣ በመሆኑም ቀጣይ ዲዛይኖች ላይ መካተትና ሊተኮርባቸው የሚገባቸውን ሐሳቦች ባለሙያዎች በሪፖርታቸው እንዳቀረቡ ገልጸዋል፡፡
“የእኛ መንግሥት ከቀረቡት ሐሳቦች ውስጥ እጅግ አብዛኞቹን በአሁኑ የሥራ ወቅት በዲዛይኑ እያካተተ የሄደበት ሁኔታ አለ፡፡ ስለዚህ አስተያየቶቹን ለማካተት ቆም ብለን እንነጋገራለን የሚል ስምምነት ከግብፅ ጋር ተደርሷል፤” ብለዋል፡፡
ሌላው የባለሙያዎቹ ቡድን ግድቡ ሊፈጥር የሚችለው የአካባቢ ተፅዕኖ መጠናት ያለበት መሆኑን እንደጠቆመ የገለጹት አቶ ኃይለ ማርያም፣ “ግብፅና ሱዳን በዚህ ረገድ መረጃ ሊሰጡ ፈቃደኛ ስላልነበሩ ባለን መረጃ ላይ ብቻ ተመሥርተን ነው የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናቱን ያካሄድነው፤” በማለት በዚህ ጉዳይ ላይም ተነጋግሮ መሥራት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ግብፅ ለመደራደር ዝግጁ መሆኗ ጥሩ ነገር እንደሆነ ነገር ግን ውጤቱን መተንበይ እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡ በድርድሩ ወቅትም ሆነ በማንኛውም ጊዜ ቢሆን፣ “የግድቡ ሥራ የማይቆም መሆኑንና መጠኑ የማይቀንስ መሆኑም መታወቅ አለበት፤” ሲሉም የመንግሥታቸውን አቋም ግልጽ አድርገዋል፡፡
የግብፅ ፕሬዚዳንት ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በግድቡ ዙሪያ በመወያየት በግልጽ በሚዲያ የታየው ኢትዮጵያን የማተራመስ አቋም ሆን ተብሎ ይሆን በስህተት ባይታወቅም፣ ከ120 ዓመታት በፊት ጀምሮ በግብፅ ይራመድ የነበረ አስተሳሰብ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
“በዚህ አስተሳሰብ መመራት ትክክል እንዳልሆነ ለግብፅ መሪ በተደጋጋሚ ገልጫለሁ፡፡ መንግሥታቸው ይህንን አቋም ይዟል የሚል እስካሁን አልሰማንም፤ ይህንን አቋም በያዘ ጊዜ ግን አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይገባሉ ማለት ነው፤” ብለዋል፡፡
የሙስና ጉዳይ
በቅርቡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣናትና ባለሀብቶች በሙስና ተጠርጥረው መያዛቸውን ተንተርሶ፣ በኢሕአዴግ የፖለቲካ ልዩነት የተነሳ የተወሰደ ዕርምጃ ስለመሆኑና በቀጣይ የመንግሥት ተመሳሳይ ዕርምጃዎች ላይ ተጠይቀው በሰጡት ማብራሪያ፣ ዕርምጃው በኢሕአዴግ ጉባዔ እንዲሁም በማዕከላዊና በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ደረጃ ጥልቅ ውይይት ተካሄዶበት የተያዘ አቋም መሆኑን ገልጸዋል፡፡
“ኪራይ ሰብሳብነትን አንዳንዶች እስከሚያሾፉበት ድረስ እየተነገረ ያለ ቃል ነው፡፡ ይህንን ዕውን በማድረግ የድርጅታችን አንድነት፣ የመንግሥትና የሕዝብ ጠላት መታገል አለብን ብለን ነው ያስቀመጥነው፤” ሲሉ አክለዋል፡፡
የሙስና ሥራ የሰዶ ማሳደድ ሥራ ባለመሆኑ በተጠና መንገድ ሥራ መጀመሩን፣ በዋነኛ ደረጃ ከተለዩት ውስጥ የመሬት አስተዳደር ሥርዓቱ ላይ በተወሰደ ዕርምጃ ግለሰቦች ተጠያቂ እንደተደረጉ ገልጸዋል፡፡
ሙሰኞችን መቅጣት ብቻ ሙስናን መዋጋት አይደለም፡፡ ሥርዓቱ ለሙስና ምቹ እንዳይሆን ማድረግ ይገባል ከሚል ፅኑ እምነት በመነሳት የመሬት ሥርዓቱን የማስተካከሉ ሥራ መካሄዱን ተናግረዋል፡፡
“በሁለተኛ ደረጃ ታክስ ላይ መጥተናል፡፡ ቢሮክራሲውንም ከፍተኛ አመራሩንና ባለሀብቶችን ተጠያቂ አድርገናል፤” ብለዋል፡፡ “የፖለቲካ ልዩነት ስላለ ነው በሚል ለቀረበው ጥያቄ ይህንን ሊል የሚችል ካለ የፖለቲካ ልዩነት ሳይሆን የመቀራረብ ልዩነት ነው፡፡ ከሙሰኞች ጋር የተቀራረበ ካለ ደስ ሊለው ይችላል ብሎ መውሰድ አይቻልም፡፡ ….. ከየቤታቸው በሻንጣ የተከማቸ ገንዘብ እየወጣ እየታየ ምን የፖለቲካ ልዩነት ሊባል ይችላል?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ቀጣዩ መንግሥት ያተኮረበት የሙስና ምንጭ የመንግሥት ግዥ ዘርፍ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ኃይለ ማርያም፣ “ይህ አገር ከፍተኛ የመሠረተ ልማት እያካሄደ ነው፡፡ ከውጭ ባለሀብቶች ጋር ከፍተኛ የኮንትራት ስምምነትና ድርድሮች የሚደረግበት ነው፡፡ በመሆኑም የሙስና ምንጭ ነው፡፡ ስለዚህ በጥናት ላይ የተመሠረተ የመፍትሔ ዕርምጃ እንወስዳለን፤” ሲሉ ቀጣይ ዘመቻቸውን ጠቁመዋል፡፡

Saturday, June 29, 2013

ኦባማ – “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ”

“ግብረሰዶማዊነት ወደፊት!”
obama in senegal


በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አፍሪካን እየጎበኙ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሴኔጋል ጉብኝት ባደረጉት ወቅት የግብረሰዶማውያን መብት ሊከበር እንደሚገባው አስታወቁ፡፡ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት ሰዶማውያንን የሚደግፍ ውሳኔ ሰሞኑን በማሳለፉ ደስታቸውን ገለጹ፡፡ የሴኔጋሉ አቻቸው ግብረሰዶማውያን እንዳይወነጀሉ ለማድረግ አገራቸው ዝግጁ አለመሆኗን ተናገሩ፡፡
ሰሞኑን በአፍሪካ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ፕሬዚዳንት ኦባማ ጉብኝታቸውን በጀመሩባት ሴኔጋል የግብረሰዶማውያንን መብት በተመለከተ ለአፍሪካውያንና ለመሪዎቻቸው ማብራሪያና “ትምህርት” ሰጥተዋል፡፡ “መንግሥታት ዜጎቻቸውን እንዴት ሊያስተናገዷቸው ይገባል፤ ሕጉስ እንዴት ሊያያቸው ይገባል ለሚለው ጥያቄ መልሱ ሁሉም ሰው በእኩልነት ሊስተናገድ ይገባዋል” በማለት “ግብረሰዶማዊነት ወደፊት” የሚያስብል ንግግር አድርገዋል፡፡
አፍሪካን እየጎበኙ የሚገኙት ኦባማ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት የግብረሰዶማውያንን መብት ሊያስከብር የሚችል ውሳኔ ማስተላለፉ እንዳስደሰታቸው በጉብኝታቸው ወቅት ጠቁመዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ያስተላለፈው ውሳኔ ለጋብቻ መጠበቅ ከለላ የሚያደርገውን Defense of Marriage Act (DOMA) የተባለው ሕግ ለወንድና ሴት ተጋቢዎች ብቻ በማለት ያስቀመጠው ከለላ የግብረሰዶማውያንን መብት ይጻረራል በማለት ነበር፡፡ ስለሆነም በፍርድቤቱ ውሳኔ መሠረት  በተመሳሳይ ጾታዎች መካከል የተፈጸመ “ጋብቻ” ከፌዴራል መንግሥት የሚሰጡ ጥቅማጥቅሞችን ሊያስከለክል አይገባም በማለት ወንድ ሚስትም ሆነ ሴት ባል ያላቸው ሁሉ የጥቅሙ ተካፋይ እንዲሆኑ ፈቅዶላቸዋል፡፡ እንዲሁም በካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት የሰዶማውያን ጋብቻ እንዲቀጥል ፈቃድ የሚሰጥ ውሳኔ ጠቅላይ ፍርድቤቱ አስተላልፏል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በበርካታ የአፍሪካ አገራት ግብረሰዶማዊነት በህግ የሚያስቀጣ ወንጀል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል በበኩላቸው ግብረሰዶማውያን እንዳይከሰሱ ለማድረግ አገራቸው ዝግጁ አለመሆኗን ተናግረዋል፡፡ “በጣም በመቻቻል” የምንኖር ነን ያሉት የሴኔጋሉ መሪ አገራት ውስብስብ የሆኑ ሕጎችን በራሳቸው ጊዜ በተግባር ላይ እንደሚያውሉ በመጥቀስ የኦባማን ሃሳብ ተግሳጽ በተሞላበት ምላሽ አስተናግደውታል፡፡
በመቀጠልም አገራቸው ሴኔጋል ወንጀለኞችን በሞት መቅጣት ያቆመች መሆኗን በመናገር አሜሪካ ግን ይህንን እስካሁን ተግባራዊ አለማድረጓን በመጥቀስ ኦባማን ተሳልቀውባቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአሜሪካ ወንጀለኞችን በሞት የመቅጣት ህግ ከ30 በላይ ግዛቶች ውስጥ ተግባራዊ ሲሆን በተለይም በቴክሳስ በሰፊው እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ወንጀለኞችን በሞት መቅጣት እንደገና ከተጀመረ ከ1974ዓም በኋላ የቴክሳስ ጠቅላይግዛት 500ኛዋን ወንጀለኛ ሰሞኑን በመግደል የቀዳሚነቱን ስፍራ ይዞ ይገኛል፡፡

“ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ”

በፈረንሣይ አብዮት አካባቢ ህዝቡ መራቡን በተለይም የፈረንሣይ ጭሰኞች መቸገራቸውና በረሃብ እየተንገላቱ መሆናቸውን የተነገራት ልዕልት ማሪ አንቷኔ (“Qu’ils mangent de la brioche”) “ከራባቸው ኬክ ይብሉ” ብላ መልሳለች እየተባለ ለዘመናት ሲዘበትባት ኖሯል፡፡ ልዕልቲቱ ይህንን ለማለትዋ የተረጋገጠ ነገር ባይሆንም ነጻነት፣ መልካም አስተዳደር፣ ዴሞክራሲ፣ ፍትሕ፣ … ለጠማው የአፍሪካ ሕዝብ ባራክ ኦባማ “የግብረሰዶማውያን መብት ሊከበር ይገባል” በማለት መሠረታዊውን የህዝብ ጥያቄ ችላ ማለታቸው “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ” የማለት ያህል እንደሆነ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡
በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት “ለውጥ” እና “ተስፋ” ቀዳሚ ዓላማቸው አድርገው የበርካታዎችን ቀልብ የሳቡት ባራክ ኦባማ፤ ለአፍሪካ መሠረታዊ ችግር እስካሁን ጆሮ አለመስጠታቸው ብዙ የተባለበት ነው፡፡ ሰሞኑን በአሜሪካ ምክርቤት “ኢትዮጵያ፤ ድኅረ መለስ” በሚል ርዕስ በተደረገው ምክክር የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ የተናገሩትን በድጋሚ ያስታወሱም አሉ፡፡ በወቅቱ አቶ ኦባንግ ያሉት “ኦባማ ለምርጫ በተወዳደረ ጊዜ ጥቂት ደመወዝ የሚከፈላቸው ኢትዮጵያውያን የምርጫ ዘመቻውን ደግፈው ነበር፤ እስካሁን ከኦባማ የሰሙት ነገር የለም” በማለት ነበር፡፡
ከምዕራባውያን የሚመነጨውን ማንኛውንም ነገር – ከፖለቲካ እስከ ማኅበራዊ አመለካከት – ትክክለኛ አድርገው ለሚቀበሉ ግብረሰዶማዊነት ሥልጣኔ ይመስላቸዋል በማለት ለጎልጉል አስተያየት የሰጡ የሃይማኖትና የማኅበረሰብ ሳይንስ ጉዳዮች ምሁር “ጋብቻ” የሚለውን ቃል ለሁለት ወንዶች መጠቀም እርስበራሱ የሚጋጭ ጉዳይ ነው በማለት ተመሳሳይ ጾታ ብሎ ጋብቻ ማለት የተሳከረ አነጋገር መሆኑን አስረድተዋል፡፡ “ይህ የሰዶማውያን መብት ይከበር የሚለው ጉዳይ በሕግ እየጸደቀ ሲሄድ ድርጊቱን ከሃይማኖታቸው አኳያ የሚቃወሙ ሰባኪያን የሃይማኖት ትምህርታቸውን በሚያስተምሩበት ቤ/ክ ይሁን መስጊድ ወይም ምኩራብ ግብረሰዶማዊነትን እየተቃወሙ ሰበካ ማድረግ በህግ የሚያስጠይቃቸው ይሆናል” በማለት ወደፊት ሊመጣ የሚችለውን የማኅበረሰብ ቀውስ ጠቁመዋል፡፡
bush in africaበሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው ወቅት ዳግም የመመረጥ ፈተና የሌለባቸው የአሜሪካ መሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሆን የአፍሪካን የዱር እንስሳት እየጎበኙ ወደፊት ለሚሠሩት ፕሬዚዳንታዊ ቤተመጻህፍት (ፋውንዴሽን) ፎቶ እንደሚሰበስቡ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው፡፡ የባራክ ኦባማም ጉብኝት ከዚህ የተለየ አለመሆኑ ግልጽ ሲሆን “የአፍሪካ ልጅ” እየተባሉ ሲሞካሹ የኖሩት ፕሬዚዳንት ዛሬ ደቡብ አፍሪካ ሲገቡ ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ ገጥሟቸዋል፡፡ ቅዳሜ የክብር ዶክትሬት በሚቀበሉበት የዮሐንስበርግ ዩኒቨርሲቲም ተመሳሳይ ተቃውሞ ይጠብቃቸዋል፡፡
ዛሬ ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ደቡብ አፍሪካውያን “ይቻላል” (Yes! We can!) ለሚለው የኦባማ የምርጫ መፈክር “አትችልም!” (“No, You Can’t Obama,”) የሚሉ መፈክሮችን በመያዝ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡ “ኦባማ የመጣው አፍሪካንና ደቡብ አፍሪካን ለመዝረፍ ነው” በማለት ጠንካራ ተቃውሞውን የገለጸው አንዱ ተሰላፊ “አፍሪካውያን በብዙ መልኩ እየተሰቃዩ እያለ እርሱ ግን የአፍሪካን ሐብት፤ ወርቅ፣ አልማዝ፣ … ለመዝረፍ ነው የመጣው” ብሏል፡፡obama s africa
የዴሞክራሲ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕ፣ … ዕጦት ላንገላታውና በአምባገነኖች መዳፍ ሥር ለሚሰቃየው የአፍሪካ ሕዝብ በቃላት እንኳን ድጋፋቸውን ከመስጠት እስካሁን የተቆጠቡት ኦባማ አሜሪካ በአፍሪካም ሆነ በሌሎች አገሮች ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ፍላጎቱ እንደሌላት በማያወላውል መልኩ ያረጋገጠ መሆኑ የብዙዎች ግንዛቤ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፕሬዚዳንቱን የሥልጣን ኃይል ጥያቄ ውስጥ የሚጥልም ነው፡፡
በአውሮጳ የፖለቲካ ምጣኔሃብት ተመራማሪ የሆኑ እንደሚሉት “አሜሪካኖች እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ ዓይነቱን አምባገነናዊ አገዛዝ እስኪያስመልሰው ድረስ በዕርዳታ ገንዘብ ካሽሞነሞኑ በኋላ“ኢህአዴግን ምን እናድርገው” በማለት “ምክር ስጡን” እያሉ በሕዝብ ሰቆቃ ላይ ያላግጣሉ፡፡ ሲሻቸውም ደግሞ አፍሪካ ድረስ በመሄድ “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ” በማለት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን ችግር ያልሆነውን የግብረሰዶማውያን መብት መከበር ይሰብኩናል፡፡ ታዲያ ለዚህ ልግጫ መልሳችን መሆን የሚገባው “ራሳችንን ነጻ እናወጣለን፤ ነጻነታችንን አንለምንም፤ አሜሪካ ግን በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት እንድትሆንብን አንፈልግም” በማለት አቶ ኦባንግ ሜቶ ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ ምክርቤት በተካሄደው ምክክር የተናገሩትን ዓይነት ቁርጠኝነት ነው በማለት አስተያየታቸውን ደምድመዋል፡፡
obama africa trip100ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣው የኦባማ የአፍሪካ ጉብኝት በአሁኑ ጊዜ በበጀት ቀውስ ምክንያት በርካታ ሠራተኞች ደመወዛቸው እየተቆረጠ ባለባት አሜሪካ አነጋጋሪ መሆኑን ዋሺንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡ የደኅንነት ሰዎችን እንዲሁም 14ሊሞዚን፣ 56 ጥይት የማይበሳቸው ድጋፍ ሰጪ  መኪናዎች፣ ሙሉ የህክምና ባለሙያዎችን የያዘና ጀቶችን የጫነ መርከብ … ለፕሬዚዳንቱና ለቤተሰባቸው ጥበቃ በማድረግ ሥራ ላይ እንደሚውሉ ጋዜጣው ያብራራል፡፡
ፕሬዚዳንት ኦባማ በደቡብ አፍሪካ የሁለት ቀን ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሰኞ ወደ ታንዛኒያ ያመራሉ፡፡ የአባታቸው የትውልድ አገር ነው የሚባለውን ኬኒያ ሳይረግጡ በዚያው ወደ አገራቸው እንደሚያቀኑ የጉዞ መርሃግብራቸው ያስረዳል፡፡

ሰበር ዜናበጎንደር ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አባላት መታሰራቸው ቁጣን ቀሰቀሰ

-አንድነት በየትኛውም የመንግስት ህገወጥ ጫና ሰልፉን እንደማይሰርዝ ይፋ አድርጓል
በጎንደር ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 4 የአንድነት አባላት በፖሊስ መታሰራቸው በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ቁጣን ቀሰቀሰ፡፡ አንድነት ምንም አይነት ህገወጥ እስር በጎንደር የተዘጋጀውን የተቃውሞ ሰልፍ እንደማያስቆመው አሳውቋል፡፡
ዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2005 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ምዕራብ አርማጨሆ በጎንደር  ሰኔ 30 የሚደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ የሚመለከት በራሪ ወረቀት በማሰራጨት ላይ የነበሩት አለልኝ አቧይ፣ ዋኘው፣አብርሀም ልጅ አለም፣አንጋው ተገኝ የተባሉት የአንድነት አባላት ህገወጥ በሆነ መንገድ በአካባቢው ፖሊሶች መታሰራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችን እንዳስቆጣ ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመላክቷል፡፡ ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ወረቀት በመበተናቸው ብቻ የታሰሩት ግለሰቦች ሁኔታ የስርአቱን አምባገነንነት አመላካች ነው፡፡
የዞኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች “እስር ለጎንደር ነዋሪ በተለይም ለአንድነት አባላት አዲስ አይደለም” ካሉ በኋላ “የታሰሩት አባሎቻችንን ለማስፈታት ከምናደርገው ጥረት ጎን ለጎን የቅስቀሳ ስራው እንዳይስተጓጎል ተጨማሪ አባላት የቅስቀሳ ስራውን እንዲቀጥሉ ወደ ስፍራው ልከናል፡፡” ብለዋል፡፡
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ሙላት ጣሰው ለሰሜን ጎንደር አስተዳዳሪ ለአቶ ግዛቴ አብዩ ስልክ በመደወል የታሰሩት የአንድነት አባላት በአፋጣኝ መፈታት እንዳለባቸው ተናግረው ገዢው ፓርቲ የሚያደርገው አፈና ከህዝባዊ ንቅናቄ እንቅስቃሴያችን አያስቆመንም በማለት አሳስበዋል፡፡
አንድነት ፓርቲ የሚጠበቅበትን ስለሰልፉ የማሳወቅ ተግባር አጠናቆ ቅስቀሳ የጀመረ ቢሆንም በጎንደር ምዕራብ አርማጨሆ የተቃውሞ ሰልፉን አላማ የሚያብራራ በራሪ ወረቀት በማሰራጨት ላይ የነበሩ አባላቱ በህገወጥ መንገድ ከመታሰራቸውም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች የአንድነት ፓርቲ የቅስቀሳ ቡድን አባላት የሚደርስባቸውን ማስፈራሪያ ወደ ጎን ብለው ቅስቀሳውን አጠናክረው መቀጠላቸውንና የአከባቢው ነዋሪም በራሱ ተነሳሽነት በራሪ ወረቀቶችንና መረጃዎችን በማስተላለፍ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝ የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ጎንደር ዞን አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት አስታውቀዋል፡፡
አንድነት ፓርቲ በጎንደር ለሚደረገው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ የጎንደር ከተማና አከባቢው ነዋሪዎች በስፋት እንዲሳተፉ በቀየሰው ስትራቴጂ መሰረት ስኬታማ ቅስቀሳ እያደረገ ሲሆን ሁለተኛው የቅስቀሳ ቡድንም ዛሬ ወደ ጎንገር መንቀሳቀሱ ታውቋል፡፡

ESAT Kignit Negash Gebru 29 June 2013 Ethiopia


ተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!?

ተሜተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!?
ባለፈው ጊዜ አንድ ወዳጄ ጋር አዲሳባ ስልክ ደውዬ ሳናግረው በአካባቢው ከእርሱ ድምጽ ጎልቶ የሚሰማ የመኪና ጥሩንባ ሰማሁና ይሄ ሁሉ የመኪና ጥሩምባ ምንድነው… ብዬ ጠየኩት፡፡
ሃይለማሪያም ደሳለኝ እየገቡ ወይም እየወጡ ነው መሰለኝ መንገድ ተዘጋግቷል፡፡ አለኝ፡፡
ወዲያውም ቀጠል አድርጎ፤  እንደ ሀቁ ቢሆን ኖሮ መንገድ መዘጋጋት የነበረበት ለሀይለማሪያም ደሳለኝ ሳይሆን ለተመስገን ደሳለኝ ነበር… አለኝና በቁጭት፤ ይሄው የሚያጅቡትን አያቀውቁምና… እልኩ እያታዘብኩ ነው…! ሲል አወጋኝ!
ተመስገን ደሳለኝ ገዢውም ተገዢውም ፓርቲ ሊያመሰግነው የሚገባ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ነገር ግን ገዢዎቻችን ማመስገን የሚቆጥር ይመስል ሰውን ማመስገን አይወዱም፡፡  ስለዚህ ተሜንም በማመስገን ፈንታ ከሰሱት፡፡ ጎሽ በማለት ፈንታ እንደ ጎሽ ሊወጉት ቀንዳቸውን አሾሉበት፡፡ እሰይ በማለት ምትክ ሰይ ባንከረባብት ብለው ለሁለቱም አሰቡት፡፡ (ለማሰርም ለማሰደድም) (ሰይ ባንከረባብት በልጅነታችን ብይ ጨዋታ ላይ ተወርዋሪዋ ብይ ጉድጓዳ ውስጥ ብትገባም የተቃራኒውን ብይ ብትመታም ነጥቡ እንዲያዝልን ውል የምንገባባት ቃል ነበረች፡፡)
ተመስገን ደሳለኝ እንዲሰደድ መንግስት ከፀሎት ጀምሮ ሁሉንም አይነት የትግል ስልቶችን እንደተጠቀመበት ትዝ ይለኛል፡፡ ለምሳሌ ባለፈው ጊዜ ምንም የቀጠሮ ወረቀት ወይም መጥሪያ ሳይሰጠው በራዲዮን፤ “ተመስገን ደሳለኝ በሌለበት የፍርድ ሂደቱ ታየ ለሚቀጥለው ጊዜ ፖሊስ ይዞ እንዲያቀርበው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል!” የሚል አይነት ዜና በሰላም ቁጭ ብሎ ሻይ በሚጠጣበት ካፌ ውስጥ ሰማ፤ (እናጋን ካልን ደግሞ ዜናውን እንደውም ያነበቡት ተሜ ልክ ዜና ሲሰማ አይተው ነው…! ማለት እንችላለን…) የዚህ ዜና አላማ ግልፅ ነበር፡፡ ተሜ ደንግጦ ፖሊስ ሳይዘው በፊት መንገዱን እንዲያያዘው ማድረግ ነበር፡፡ ወዳጃችን ግን፤ ብታስሩኝ ባለ ጊዜም ባለ ብረትም ናችሁና እግሬ እምቢ ማለት አይቻለውም፡፡ ለመሰደድ ግን እሺ የሚል እግር የለኝም፡፡ ብሎ እንቅጩን ነገራቸው እና የመጣው ምጣ ብሎ ቁጭ አለ…
በነገራችን ላይ ተመስገን እስከ አሁን ድረስ በመንግስት የተሰነዘረበት ክስ ስፍር ቁጥር የለውም፡፡ እንደው የሪከርድ መዝጋቢ መስሪያ ቤቶች የሚያስታውሳቸው አጥተው እንጂ ከዚህ ሁሉ ክስ ጋር አብሮ መኖር የቻለ ጋዜጠኛ ብለው ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ የሚያሰፍሩት ሁሉ ይመስለኛል፡፡ መንግስታችን በክስ ላይ ክስ ሲደራርብ ሲደራርብ ክሱ ተቆልሎ አለመናዱም የእግዜር ተዓምር ነው፡፡ አንዱ ሳይቋጭ አንዱን አንዱ ሳይቋጭ አንዱ ክስ ሲመጣ በአሁኑ ሰዓት ተመስገን ደሳለኝ ከሃምሳ በላይ ክሶች ጋር ተመስገን ብሎ እየኖረ ነው፡፡
የተሜ እና የእኛ ፍትህ ጋዜጣ “መለስ ሞቱ” በማለቷ እኛ ሳንል ምን ሲደረግ እንዲህ ትያለሽ ተብላ ከሳላሳ ሺህ ኮፒ በላይ እንድትቃጠል ተደረገች፡፡ (የመለስ አምልኮ ይሎዎታል ተመስገን…!) አንዱ ሲዘጋ በአንዱ እንከሰታለን በምትለው ስትራቴጂ መሰረት፤ አዲስ ታይምስ ተተካች፡፡ አዲስ ታይምስ ደግሞ “ብር ከየት አምጥታችሁ ነው…” ተብላ ህትመቷ ተከለከለ፡፡ መንግስታችን እንደሆነ ኮሚክ ነው ጮክ ብለን በያይነቱ ስናዝ ራሱ “ብር ከየት አምጥተው ነው” ብሎ ይጨንቀዋል፡፡ በእርሱ ቤት እርሱ አበል ያልሰጠው ሰው፤ ወይም ከአዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም ያልተበደረ ሰው ምንም ገንዘብ የለውም…!
ተመስገን እና ጓደኞቹ እጅ መስጠት ብሎ ነገር አያውቁም ነበር፤ እና ከየትም ከየትም ብለው ድጋሚ ልዕልና ጋዜጣን አበረከቱልን፡፡ መንግስት መንግስት ሆኖ እንጂ… በብስጭት ካቲካላ ይጠጣ ነበር፡፡ ግን ሳይጠጣም ሞቅ አለው፡፡ ሰከረም፡፡ እናም ልዕልናንም ጥርቅም አድርጎ ዘጋት፡፡ (ይህ ውሳኔ የሞቅታ ካልሆነ ሌላ ሊሆን አይችልም)
ተመስገን ደሳለኝ ሲናገር ሰዎቻችን ደስ አይላቸውም፡፡ እናም በተቻለ አቅም ዝም ማሰኘት ይፈልጋሉ፡፡ ልጁ ግን በቀላሉ ዝም ብሎ የሚያስደስታቸው አልነበረም፤ በማህበራዊ ድረገፆች የሚተነፍሰውን ይተነፍስ ጀመር፡፡
ኢህአዴግ ሰው እንደማትንቅ ያወኩት እኔ ምስኪኑን ሳይቀር ለመከታተል የደህንነት ሰው የመደበች ዕለት ነው፡፡ ለተመስገን ደሳለኝማ ሁሉን አቀፍ የትግል ስልት ነው የተጠቀመችበት፡፡ በእውነቱ ከሆነ፤ ለአንድ ግለሰብ ሁሉን አቀፍ የትግል ስልት መጠቀም ትልቅ የሀይል ብክነት ነው፡፡ ፍጹም ተመጣጣኝ ያልሆነ ርምጃ፤ ጎጆ ቤትን በሚሳኤል እንደ መደብደብ በሉት…
ተሜ በኢህአዴግ ክሶች ብዛት፤ በኢህአዴግ ሚዲያዎች ማስፈራራት፣ በኢህአዴግ የደህንነት ሰዎች ከበባ፣ በኢህአዴግ ማተሚያ ቤቶች አድማ አበሳውን አየ፡፡
“አንበሳው” መንግስታችን ተመስገን ግለሰብ ነው ብሎ አልናቀውም፡፡ ያለውን አቅም ሁሉ ተጠቅሞ ሊገድበው ተንቀሳቅሷል፡፡ እርሱን ለመገደብ ያላደረገው ነገር ቢኖር ቦንድ ግዙ ብቻ አላለንም፡፡ ለአባይ የምንገዛው ቦንድ ብዙ ነገር ይገድባልና!
አሁን ተመስገን ደሳለኝ ከሜዳው ላይ ጠፍቷል፡፡ ከመንግስታችን ሃይል የተሞላበት አጨዋወት አንጻር እስከዛሬም በቃሬዛ አለመውጣቱ የሚገርም ነበር፡፡ ነገር ግን ያንን ሁሉ ችሎ ሜዳው ላይ ስናየው እኛ ደስ ይለን ነበር፡፡ አሁን ታድያ ሲጠፋብን ጊዜ በአዲስ መስመር ላይ ጮክ ብለን እንጮሃለን እንጂ እንደምን ዝም እንላለን…
ተመስገን ደሳለኝ ሆይ ማን ደስ ይበለው ብለህ ጠፋህ…!

Thursday, June 27, 2013

ESAT Special Program who killed him June 27 2013


ኢሳት (በደረጀ ሀብተወልድ)

ደረጀ ሀብተወልድ
ከሁለት ሣምንት በፊት ሲቪሊቲ ፓልቶክ ባዘጋጀው የጋዜጠኞችና የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ውይይት ላይ ኢሣትን በመወከል ተሳትፌ ነበር። በክፍሉ ታዳሚ ከነበሩት ከ 500 በላይ ተሳታፊዎች መካከል በጣም የሚበዙት የኢሳት ደጋፊዎች መሆናቸውን ሳይ ደስታ ሳይሰማኝ አልቀረም። ከደስታው ባሻገር የተሰማኝ ሌላ ስሜት ግን፦” ሰው እንደዚህ ሲደግፋችሁ፤ የበለጠ በርትቻችሁና ጠንክራችሁ  መሥራት አለባችሁ” የሚል አደራዊ ሸክም ነው።
ደጋፊዎቻችን የመብዛታቸውን ያህል ታዲያ ከጥቂት ሰዎችም ቢሆን  ቅሬታ አዘል ጥያቄዎች መሰንዘራቸው አልቀረም።ኢሳትን በተመለከተ የተሰነዘሩት እነዚህ ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎች ሲጨመቁ፦” ኢሳት የግንቦት 7 ነው፣ ግንቦት 7 እና መሪዎቹ  ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ ሰፊ የሚዲያ ሽፋን ያገኛሉ፣ ጭራሽ የሚዲያ ሽፋን የማትሰጧቸው ፓርቲዎች አሉ” የሚሉ ናቸው።
ለሦስቱም ጥያቄዎች ለመስጠት የሞከርኩትን መልስ ነው እዚህ  በመልኩ ለማስቀመጥ የሞከርኩት፦
1-      ኢሳት የግንቦት 7 ነው የሚለውን በተመለከተ፦
ይህ ጥያቄ መነሳት የጀመረው ከኢሳት ምስረታ ጊዜ አንስቶ መሆኑ ይታወቃል።በወቅቱ ይህን ወሬ ከሰሙት መካከል  አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ አንዱ ነበር። ታማኝ  የኢሳት 1ኛ ዓመት በዋሽንግተን ዲሲ ሲከበር ለጥያቄው መልስ የሰጠው፦” አይደለም እንጂ ቢኾንስ !?”በማለት ነበር። ቀደም ባሉት ዓመታትም ራዕይ ያላቸው አገር ወዳድ ዜጎች የቤት ካርታቸውን ሳይቀር እያስያዙ ከባንክ በተበደሩት ገንዘብ ያቋቋሙት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ኔትወርክ(ኢቲኤን) ይሰኝ የነበረው ተወዳጅ   የቴሌቪዥን ጣቢያ “አንዴ የ ሲ. አይ. ኤ ነው ሌላ ጊዜ የ እነ እገሌ ነው” ከሚል ሀሜት ሊያመልጥ ያለመቻሉን ታማኝ በማውሳት፤ ሰው እየወጣ ለሚናገርበትና ሀሳቡን ለሚገልጽበት  ጣቢያ ህልውና-  የድጋፍ ጥያቄ ሲቀርብለት ምላሽ ባለመስጠቱና የጣቢያውን ህልውና ማስቀጠል ከነዛ ጥቂት ሰዎች አቅም በላይ በመሆኑ ሊዘጋ መቻሉን አብራርቷል።Ethiopian Satellite Television, ESAT TV
“በጣም የሚያሳዝነው ኢ.ቲ.ኤን ተዘጋ ሲባሉ  እሠይ! ደግ ሆኑ!” ያሉ ሰዎች መሰማቱ  ነው።”ሲልም ታማኝ አክሏል።አዎ!ጣቢያው መዘጋቱ የሁሉም መናገሪያ አፍ መዘጋቱ ቢሆንም፤ በዚህ የተደሰቱ  <<ሰዎች>> እንደነበሩ ታማኝ ልምዱን አካፍሎናል።
በወቅቱ ኢሳት በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ መሆኑን የገለጸው ታማኝ፤ ይህን እውነት የማይቀበሉ- የማንም ይሁን የማን የባለቤትነቱ ጉዳይ ሊጨንቃቸው እንደማይገባ፣ ኢሳትን ሊጠይቁትና ሊተቹት የሚገባው እየሠራው ባለው ሥራ ሊሆን እንደሚገባው፣ የዚህ ዓይነት ሥራ የሚሠራ ሚዲያ አይደለም ግንቦት 7- ኢህአዴግም ቢሆን ካቋቋመ ሊመሰገን እንጅ ሊነቀፍ  እንደማይገባው በመንገር ነበር ምላሹን የቋጨው።
-የዩኒቲ ኮሌጅ ባለቤትና ፕሬዚዳንት በነበሩት በዶክተር ፍስሀ እሸቱ “ዕለታዊ አዲስ” የተሰኘ ዘወትር የሚታተም ጋዜጣ ሲቋቋም በፕሬስ ተቋሙ ታቅፈው ከሠሩት ጋዜጠኞች መካከል- ይህ ፀሀፊ አንዱ ነበር። ያኔ ዕለታዊ አዲስ ይታማ የነበረው “ሲ.አይ.ኤ ያቋቋመው ነው” እየተባለ ነበር። ጋዜጣው በርዕሰ-አንቀጹ  በሰጠው ምላሽም ፦”አረ በፍፁም! የሲ.አይ. ኤ አይደለሁም”የሚል ሙግት ውስጥ አልነበረም የገባው-ይልቁንም፦ “ሲ.አይ. ኤ ይህን ጋዜጣ፤ እየሠራ ላለው ተግባር አቋቁሞ ከሰጠ ሊመሰገን ይገባዋል” የሚል ነበር ምላሹ።ሁሌም አዲስና ተልቅ ነገር ከትችት  ሊያመልጥ እንደማይችል ያለፉ ልምዶቻችን ሁሉ ምስክሮች ናቸው።
በኢሳት ዙሪያ ለተነሳው ተመሣሳይ ጥያቄም በበኩሌ ከዚህ ውጪ ምላሽ የለኝም። ኢሳት በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ነፃ ሚዲያ መሆኑን እረዳለሁ።  እኔ የምናገረው፤ የማውቀውን ያህል ነው። ይህን ስነግረው <“አይ ተሣስተሀል ፤ኢሣት የግንቦት 7 ነው”  የሚለኝ ካለ ምላሼ፦”እና? ቢሆንስ?” የሚል ነው።ግንቦት 7ቶች ራሳቸውን የሚተቿቸው ሰዎች ሰይቀሩ በተደጋጋሚ  የሚስተናገዱበትን ነፃና ገለልተኛ ሚዲያ ካቋቋሙ በእውነት  ልናደንቃቸው ይገባል። አዎ!እንደሚወራው ኢሳት የግንቦት 7 ነው ብለን የምናምን ከሆነ፤ የግንቦት 7 መሪዎች ዲሞክራቶች መሆናቸውን በተግባር ከማስረገጥ ውጭ ሌላ የሚሰጠን ትርጉም ሊኖር አይችልም።
2-ግንቦት 7 እና መሪዎቹ በኢሳት የተለየ ሽፋን ያገኛሉ የሚለውን በተመለከተ፦
ይህ አባባል  በመረጃ ላይ ሳይሆን በግምት የተወሰደ ድምዳሜ እንደሆነ ተረድቻለሁ።ግምት ሁልጊዜ ህሊናዊ(ሰብጀክቲቭ) ነው። ይሆናል ብለን የገመትነው ነገር በመረጃ ሲመረመር ከግምታችን ውጪ የሚሆንበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም። ግንቦት 7 ሰፊ ሽፋን ያገኛል የሚለውን ወሬ ለመጀመሪያ ጊዜ  የሰማን ሰሞን ለማወቅ ያህል ” ለየትኛው ፓርቲ ብዙ ሽፋን ሰጥተናል?” በሚል -ዜናና ፕሮግራም ቆጠራ ድረስ ገብተናል።ያኔ አንድነት ፓርቲ ጥሩና ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ የሚያደርግበት ጊዜ ነበር(እነ አንዷለም ሳይታሰሩ ማለቴ ነው)  በወቅቱ ባደረግነው ቆጠራ ሰፊ ሽፋን አግኝቶ የነበረው አንድነት ፓርቲ ነው። ዶክተር ነጋሶ፣ አቶ አንዷለም፣አቶ አስራት ጣሴ… ሌሎችም  የአንድነት አመራሮች በተደጋጋሚ ቃለ-ምልልስ የሰጡበትና ያወጧቸው የነበሩት መግለጫዎች በሙሉ ሽፋን ያገኙበት ጊዜ ነበር።
-ግንቦት 7 በነጀነራል ከማል ገልቹ ከሚመራው የኦነግ አንድኛው ክንፍ ጋር ትብብር በመሰረተ ሰሞን ደግሞ- ከፍ  ያለ ሽፋን አግኝቶ ነበር።
-የሙስሊሞች መብታችን ይከበር ጥያቄ የተነሳ ሰሞን ደግሞ ጉዳዩ ከሁሉም የበለጠ ከፍተኛ ሽፋን አግኝቶ ነበር።
-የዋልድባም እንደ ችግሩ መጠን ሰፊ ሽፋን አግኝቷል።
-ከሳምንታት በፊት ሰማያዊ ፓርቲም እንዲሁ  ትርጉም ያለውና ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ማድረግ ሲጀምር ሰፋ ያለ ሽፋን አግኝቷል። ወዘተ..
-በግለሰብ ደረጃም የዓባይ ወንዝ ግድብ ይፋ መሆኑን ተከትሎ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እነ ዶክተር ጌታቸው በጋሻው እንዲሁም በአውስትራሊያ፣ በአውሮፓና በደቡብ አፍሪካ የ ኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ ሲያካሂዱ እነ  ታማኝ በየነ፣ በተለያዩ ጉዳዩች ፖለቲካዊ ትንታኔያቸውን እንዲያጋሩን ስንፈልግ  ደግሞ እነ ጃዋር መሀመድ… ወዘተ በተደጋጋሚ በኢሳት ላይ ቀርበዋል። ይህ ማለት ጋዜጠኞቹ ለምንሠራቸው ዘገባዎችና ቃለምልልሶች  በአመዛኙ እየተመራን ያለነው በክስተቶች (Events) ነው ማለት ነው።
አንዳንዶቻችን ግን ይህን አልተገነዘብንም ወይም ላለመገንዘብ አስቀድመን የራሳችንን መስመር አስምረናል። ከተጠቀሱት ድርጅቶችና ግለሰቦች ጎልቶ ሚታየን፤ እነ ዶክተር ብርሀኑ ኢሳት ላይ መናገራቸው ብቻ ነው።እደግመዋለሁ ሁላችንም ሳንሆን አንዳንዶቻችን።
ስለዚህ በዚህ ዙሪያ የምንወቀስበት ነገር ካለ ወቀሳው መቅረብ ያለበት ከላይ በአብነት  እንደተጠቀሱት ያሉ  ትኩረት ሳቢ(የዜና ዋጋ ያላቸውን) እንቅስቃሴዎች አድርጎ ሽፋን ያልሰጠንለት ድርጅት ካለ፤ ያን በማሳየት  ቢሆን ይመረጣል። “ጥሩ አንቀሰቃሴ(የዜና ዋጋ ያለው) አደርጌ ሽፋን አልሰጣች ኝም”የሚል ድርጅት ካለ በተጫባጭ በማሳየት ሊወቅሰንም፣ በአደባባይ ሊከሰንም ይችላል።ያ ሲሆን እኛም ያላየናቸውን ስህተቶች ዐይተን ለማስተካከል ዕድል ይኖረናል።እስካሁን ባለው ሂደት በማንም ይደረጉ በማን፤ ያየናቸውን ክስተቶች በሙሉ ያለምንም አድሎ ባለን አቅምና የሰው ሀይል ለመሸፈን ሞክረናል።ከዚህም አልፎ(ብዙዎቹ መረጃ ለመ ጠት ፈቃደኛ አይሁኑ እንጂ) በተለያዩ ጉዳዩት ዙሪያ የመንግስትን  ሀላፊዎች ለማነጋገር ብዙ ጊዜ ሙከራ ተደርጓል።
ይህን ስል  የተሟላ ሥራ እየሠራን ነው እያልኩ አይደለም።ብዙ በሚሠራ ተቋም አልፎ አልፎ ለስህተት መዳረጉ የሚጠበቅ እስከሆነ ድረስ ፤ ችግሮች ሊኖሩ ይችላሉ። እኛ ራሳችን የምናያቸውና የምንነጋገርባቸውም ነገሮች አሉ።በየጊዜው ግን ድክመቶቻችንን ለማሻሻል ጥረት እያደረግን ነው። አሁንም የምለው ነገር ቢኖር፤  በዚህ ረገድ ድክመቶች ተስተውለውብን ከሆነ፤ልንመከርና ልናስተካክል ዝግጁ ነን።
በ3ተኛ ደረጃ የተነሳውን ጥያቄ የማየውም ከዚሁ አንፃር ነው። እስከዛሬ የሚዲያ ሽፋን ያላገኙ ድርጅቶችና ግለሰቦች ይኖራሉ። ያ የሆነው ቀደም ሲል እንደጠቀስኩት በአመዛኙ በክስተቶች እየተመራን በመሥራታችን እንጂ በሌላ ምክንያት አይደለም። ወደፊት እነዚህን ጉዳዮች በዕቅዳችን በማካተት ያሉብን ጉድለቶች ለማሻሻል እንጥራለን። ኢሳት የኢትዮጵያ ሕዝብ ዐይንና ጆሮ ነው የምንለው ለመፈክር ብቻ አይደለም። ከልብ በማመን ነው።
በመጨረሻም፦
ሰሞኑን  በፌስ ቡክ በተሰራጨው የዶክተር ብርሀኑ ንግግር ዙሪያ አስተያየት እንድሰጥ የጠየቃችሁኝ በርካታ ናችሁ።የተሟላና የጠራ መረጃ ባላገኘሁበት ሁኔታ አስተያዬት መስጠት ስላልፈለግኩ ነበር ዝም ያልኩት። አንዳንዶቻችሁ ግፊታችሁን ባለማቆማችሁ በአጭሩ የምለውን ልበል፦
ዶክተር ብርሀኑ በንግግራቸው የጠቀሷቸው ሁለት ተቋማት አሉ-ግንቦት 7 እና ኢሳት። በሚመለከተኝ በኢሳት ጉዳይ ላይ  ባ’ጭሩ የምለው ነገር ቢኖር ፦የኢሣትን ህልውና  ለማረጋገጥና ቢያንስ አሁን በሚያደርገው መጠን ስርጭቱን ለማስቀጠል  ከተፈለገ ፤ ዲሞክራሲ በአገሬ እንዲያብብ እሻለሁ የሚሉ ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶች ሁሉ ኢሣትን የመርዳት ሀላፊነት ጭምር አለባቸው የሚል ነው። ኢሣት ከምስረታው ድረስ እስካሁን ድረስ “እባካችሁ እርዱኝ” እያለ እንደሚገኝ  በግልጽ የሚታወቅ ነው ።  ይሁንና እንደ ኢሣት ያለን -ከነ ኢቲቪ የተለየ ድምጽን የመጠበቅ  ሀላፊነቱ- የግለሰቦችና የድርጅቶች ብቻ አይደለም።  ስላልታደልን ነው እንጂ በዋነኝነት ኢሣትን  ሊረዳ የሚገባው የኢትዮጵያ መንግስት ነበር።
እዚህ ላይ ሊነሳ የሚገባው ዋነኛ ጥያቄ፦” ኢሳት ከግለሰቦችም ሆነ ከተለያዩ አካላት የሚያገኘው ድጋፍ የኢዲቶሪያል ነፃነቱን አያሳጠውም ወይ?” የሚል መሆን ነው ያለበት። አዎ! የገንዘብ ድጋፍ መቀበልን- የሚዲያን ነፃነትና ገለልተኝነት አሳልፎ ከመስጠት ጋር በማያያዝ ስጋታቸውን የሚገልጹ ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ። ይህ ተገቢ ስጋት ነው።
ይሁንና ኢሣት የተመሰረተበት ጊዜ፣ ቦታ(በስደት)፣ዓላማ፣ የተቋሙ አወቃቀር፣የሚገኝበት ሁኔታ ወዘተ..ለተጠቀሰው ስጋት የሚያጋልጠው አይደለም። ይነስም ይብዛም በተለይ በውጪ አገር የሚገኙ በርካታ  ኢትዮጵያውያን  በቋሚነት ሳይቀር ኢሣትን እየደገፉ ይገኛሉ። እነዚህ ወገኖች ኢሳትን እየደገፉ ያሉት ለራሳቸውና ላ’ገራቸው ሲሉ ነው። የድጋፍ መነሻቸውም ይህ አመለካከታቸው ነው። ሰዎቹ ኢሳትን በቋሚነት ስለሚደግፉ በግላቸው ያገኙት ወይም የተደረገላቸው ነገር የለም።ሊኖርም አይችልም። ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶችም ጉዳይ  ከዚህ በተለየ መልኩ ሊታይ አይችልም።አንድ ድርጅት ኢሳትን ሊረዳ የሚገባው የኢሳት መኖር ለማደርገው (ለሚደረገው) ዲሞክራሲን የማምጣት ትግል ጠቃሚ ነው በሚል አመለካከት እንጂ- ባደረገው ድጋፍ ምክንያት በተለየ መልኩ በሚዲያው ለመስተናገድ በማሰብ  አይደለም። ግንቦት 7ትም አንደተበለው አሣትን ደግፎ ከሆነ  ከዚህ እሣቤ ውጪ  ይሆናል ብዬ ፈጽሞ አልገምትም።  “በታገልነው ልክ የስልጣን ደመወዝ ይገባናል “ የሚሉ ገዥዎችን አምርረው የሚኮንኑ ሰዎች ይህን ያስባሉ ማለት በጣም ይከብዳል።     እስካሁን ያሉት የኢሣት አሠራሮችም ይህን አያመለክቱም።
ላብራራ፦  በኢሣት ጋዜጠኞች የኤዲቶሪያል ስብሰባ ላይ አንድም ቀን ከሌሎች በተለየ መልኩ ለእገሌ ፓርቲ ወይም ድርጅት  ይሄ ይሠራለት የተባለበት ጊዜ  ፈጽሞ የለም-ሊኖርም አይችልም።እስካሁን ድረስ የኢዲቶሪያል ነፃነታችን  የተጠበቀ እንደሆነ በድፍረት መናገር እችላለሁ። አልዋሸሁም።ይህን ፅሁፍ  ጓደኞቼ ሊያነቡት እንደሚችሉ አውቃለሁና ቢያንስ እነሱ እንዲታዘቡኝ አልፈልግም።ከዚያም በላይ ህሊና አለ። ማንም ጣልቃ የማይገባበት የኤዲቶሪያል ነፃነት አለን። ሥራችንን እና እንግዶቻችንን የምንወስነው  በኤዲቶሪያል ስብሰባችን  በነፃነት እየተነጋገርን፣እየተከራከርን፣እየተሟገተን ነው።   በምን ምክንያት  ካ’ገራችን ተሰደድን?  …… <<አሳልፈን አንሰጥም!>> በማለታችን ምክንያት ለእስር እና ለስደት የተዳረግንበትንና ስንት ያየንበትን መክሊታችንን/ሀብታችንን/ ነፃነታችንን፤ እዚህ ለምን ብለን የምንጥለው ይመስላችሁዋል? ለገንዘብ? ለጥቅም? ወይስ ለዝና?  በፍጹም!!!  እንዳትሣሳቱ።  ቢያንስ ለራሳችን ክብር  አለን።               ሀቁ ይኸው ነው፦  ነፃና ገለልተኛ የሆነ የኤዲቶሪያል ነፃነት አለን። አምላክ ዕድሜና ጤናውን ይስጠን እንጂ – ይህ ሙያዊ ነፃነታችን ተጠብቆ እስከቀጠለ ድረስ ከኢሣት ጋር እንቀጥላለን።እደግመዋለሁ፦ደመወዝ እስከተከፈለን ድረስ ሳይሆን ፤አሁን ያለን ሙያዊ ነፃነት እስከተጠበቀ ድረስ።    በዚህ አጋጣሚ  እንዲህ ያለ ሙያዊ ነፃነቱ የተጠበቀ የሚዲያ ተቋም ለመሰረቱ ሰዎች ያለኝን ታላቅ አክብሮት ሳልገልጽ ባልፍ፤ ንፉግ እሆናለሁ።
እናም… አስተያዬቴን የጠየቃችሁኝ ሰዎች፣ እንደተባለው ግንቦት 7- ለኢሳት ድጋፍ አድርጎ ከሆነ፤ የግንቦት 7 መሪዎችን- በባልደረቦቼና በኢሳት ወዳጆች ስም ከልብ አመሰግናለሁ ከማለት ውጪ ሌላ ምን ልል እችላለሁ?ሌላ ማለት ካለብኝ ልል የምችለው፦  “ ሌሎችም ድርጅቶች ሆናችሁ ግለሰቦች በምትችሉት አቅም በልጅነት ዕድሜ ላይ የሚገኘውን ኢሳትን በመርዳት በአገራችን  ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ታግዙ ዘንድ አደራ!” ነው ።
ኢሣት የኢትዮጵያ ሕዝብ አንደበት፣ ዓይን እና ጆሮ ነው!!!

Wednesday, June 26, 2013

“ምስጢር ካወጣህ ቤተሰቦችህን እንፈጃቸዋለን”

“ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል”
tesfaye


“የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል”
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በዝዋይ እስር ቤት ለወራት ስቃይ የተፈፀመበት
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ይባላል፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ አዳማ/ናዝሬት አድጎ፣ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት የመንግስት ደህንነት ሀይሎች ተይዞ ለ23 ወር በዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ከወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ጋር ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉን፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ማን ነበር ያሰረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በማለዳ ቤቴ ተንኳኳ፤ ተነስቼ ከፈትኩኝ፡፡ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው፡፡ “ና ውጣ፤ ልብስህን ለብሰህ ውጣ” አሉኝ፡፡ እኔ እናቴ ሞታ ሊያረዱኝ የመጡ መስሎኝ “ምነው ቤተሰብ ደህና አደለም? የተፈጠረ ችግር አለ?” አልኳቸው “ዝም ብለህ ናውጣ” አሉኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩኝና ወጣሁ፤ አንቀው መኪና ውስጥ ከተው ወደ ማዕከላዊ ወሰዱኝና 3 ወር አሰሩኝ ከዛም አንድ አመት ከ8 ወር ዝዋይ ማረሚያ ቤት፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- መታሰርህን ለቤተሰብ ተናግረሀል?
ወጣት ተስፋዬ:- ለማንም ሰው እንድናገር አልፈቀዱልኝም፤ መስሪያ ቤቴ አልጠየቀኝም፣ ደሃዋ እናቴ ያለችው ናዝሬት ነው እሷም የምታውቀው ነገር አልነበረም፡፡ አባቴ አቶ ተካልኝ አስተማሪ ነበር አርባ ጉጉ ላይ ነው በ1985 ዓ.ም በነበረው ግጭት ነው የተገደለው፡፡ ማንም ሳይጠይቀኝ፣ፍ/ቤት ሳልቀርብ 23 ወር ታሰርኩ ልብስ ምግብም የሚያመጣልኝ ሰው አልነበረም፡፡ እናቴም መታሰሬን እንኳ አታውቅም መስሪያ ቤቴም ስኮላርሽፕ አግኝቷል፤ ወደ ውጪ ሃገር ሊማር ሊሄድ ነው የሚባል ነገር ስለነበረ አልጠየቁኝም፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የት ነበር ስኮላርሺፕ ያገኘኸው?
ወጣት ተስፋዬ:- የዛሬ 2 ዓመት አካባቢ የራስመስ ሙንደስን ስኮላርሽፕ አግኝቼ ነበር፡፡ ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ካሊፎርኒያና ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ቶክዮ ባሉ ምሁራን ሪኮመንድ ተደርጌ በጣሊያኑ ፌራሪ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ተዘጋጅቼ ነበር፡፡ እንደተፈታሁ ሄጄ ስጠይቃቸው ብዙዎቹ ጓደኞቼ በጣም ደነገጡ፡፡ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ቅማል ተወርሬ … ባካችሁ ተውኝ … ምንም የሌለ ነገር የለም በጣም ተጎድቻለሁ፡፡ ከማረሚያ ቤት እንደወጣሁ እናቴ ጋ ስሄድ በጣም ደነገጠች፣ በሕይወት ያለሁ አልመሰላትም 23 ወር ሙሉ ከቤተሰብ ስለተለየሁ ግራተጋባች፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- በእስር ወቅት የደረሰብህ ድብደባና ማሰቃየት ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኛል፡፡ በኤሌክትሪክ ጀርባዬ ላይ አቃጥለውኛል፣ በብልቴ ላይና በኩላሊቴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ስላደረሱብኝ ሽንት ችዬ አልሸናም፣ ሽንቴን መቆጣጠርም አልችልም፡፡ ኩላሊቴንም በጣም ያመኛል፡፡ ውሃ ውስጥ እየነከሩ በጣም ደብድበውኛል፡፡ አሁን ስናገር ያመኛል ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- እንደው ስታስበው ለእስር ያበቃህ ወይም ከመንግስት ጋር ያጋጨህ አጋጣሚ ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- መስሪያ ቤቴ ውስጥ የኢህአዴግ አባላት ነበሩ፤ በጣም ይከታተሉኛል፡፡ በቢ.ፒ.አር ላይ ስብሰባ በተደጋጋሚ ይጠራ ነበር፡፡ እኔም ሠራተኛ ላይ ተፅእኖ የሚያደርሱ ነገሮች ሲመጡ እኔ አልቀበልም በግልፅ እናገር ነበር፤ ሠራተኛውም እኔን ይደግፋል፡፡ ከመታሰሬ ጥቂት ጊዜ በፊት ገነት ሆቴል ስብሰባ ነበረን፡፡ በዛ ስብሰባ ላይ በጣም ተከራከርኩ፤ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር አቶ ፀጋዬ ማሞ የሚባሉ አሰልጣኝ፣ ከውጭ ጉዳይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲና ከንግድና ኢንዱስትሪም የመጡ ነበሩ ስማቸውን የማላስታውሳቸው ባለስልጣን ነበሩ፤ እዛ ላይ ሀሳብ አንስቼ ተከራክሬ ነበር፡፡ “የሠራተኛን ሀሳብ ዳይቨርት ያደርጋል” ይሉኝ ነበር፡፡ መቼም ግን ሀሳቤን በመናገሬ ይህን የመሰለ ስቃይ ይደርስብኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ “አሸባሪ፣ ግንቦት ሰባት” እያሉ እኔ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ፍርድ ቤት ሳልቀርብ ያለምንም ፍርድ በርሜል ውስጥ ውሃ ጨምረው እያስተኙ አሰቃዩኝ፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- እንደዚህ ያሰቃዩህ ምን አይነት ምንም አይነት መረጃ ሳያገኙ ነው?
ወጣት ተስፋዬ:- እኔን ጥፋተኛ የሚያስደርግ ምንም መረጃ አላገኙም፣ እኔን አስረው ወደ መስሪያ ቤት በተደጋጋሚ ይደውሉ እንደነበር ይነግሩኝ ነበር፡፡ የኢሜይል አድሬሴንም ተቀብለው በርብረዋል ግን ምንም አላገኙም፡፡ እኔ ከማንም ጋር ሊንክ የለኝም ኢሜሌ ላይ የስኮላርሺፕ መልዕክት ካልሆነ በስተቀር ምንም የለውም፡፡ በመስሪያ ቤቴ ሪሰርቸር ነበርኩ፣ በሶሲዮሎጂ ነው የተመረኩት፡፡ ሉሲ የተገኘችበት ሣይት ላይ አፋር፣ ጋምቤላ ብዙ ሳይቶች ሰርቻለሁ፡፡ ከአለቆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ሰላማዊ ነው እነሱ ናቸው ስኮላርሽፕ ሪኮመንድ ያደረጉኝ፡፡ አንደኛው ፕሮፌሰር 25 ዓመት ሙሉ እዚህ አገር ሰርቷል፣ አርዲን ያገኘው እሱ ነው፡፡ ሄነሪ ጊልበርት ይባላል፤ እሱም ሪኮመንድ አድርጎኛል፡፡ እኔ በጣም የሚቆጨኝ ደሃዋ እናቴ አረቄና ጠላ ሸጣ ነው ያስተማረችኝ ምን ብዬ ልንገራት እንደዚህ አትጠብቀኝም ከበደኝ፣ አሁን እሷ የምትሰጠኝ ምግብ ራሱ ደምደም አለኝ… (ረጅም ለቅሶ)፡፡ ልጄ በደህናው አይደለም የጠፋው ሞቷል ወይም መኪና ገጭቶታል ብላ ነበር የምታስበው፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የከመታሰርህ በፊት ፖለቲካ ተሳትፎ ነበረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- 1997 ዓ.ም የቅንጅት ደጋፊ ነበርኩ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበርኩ በ97 የነበረው ሁኔታ ስንት ሰው አለቀ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነበር ታውቃላችሁ ምንም የምናደርገው ነገር አልነበረም ፡፡ በምርጫ አሸንፎ ሥልጣን መያዝ እንደማይቻል ተረዳሁኝ፡፡ ከ1997 ዓ.ም በኋላ የማንም የፖለቲካ ፓርቲ አባል አልሆንኩም፡፡ ከዚህ በኋላ ከምንም ነገር የተገለልኩ ሆኛለሁ፡፡ አንድ ብርጭቆ ሳትሰብር አሸባሪ ስትባል አስብ እንግዲህ አንድ ብርጭቆ እንኳን ሰብሬ አላውቅም ባለኝ እውቀት እንደውም ለእውቀት ነው የምጓጓው እውቀቴን አሳድጌ አገሬን ለመለወጥ ነው የማስበው እኔን ምንም የሚመለከተኝ ነገር የለም አሸባሪም ግንቦት ሰባትም አይደለሁም፡፡ስትደበደብ፣ ስትሰቃይ ያላደረከውን አድርጌያለሁ ትላለህ፤ በርሜል ውሃ ሞልተው ይከቱሃል ያሰቃዩሃል፡፡ አያሳዝንም ይሄ? እንዴት አድርጎ እዚህ አገር ይኖራል? 23 ወር ሙሉ አስረው ማሰቃየታቸው ሳያንስ የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል፡፡ እኔ ግን ከዚህ በላይ ሞት የለም ብዬ ነው የነገርኳችሁ፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- አሁን የት ነው የምትኖረው?
ወጣት ተስፋዬ:- መኖሪያ የለኝም … (ረጅም ለቅሶ)
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝን ለመርዳት የምትፈልጉ አንባብያን ከፍኖተ ነፃነት መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ (ምንጭ ፍኖተ ነጻነት)

አንዲት የኮንትራት ሰራተኛ በጅዳ ቆንስል በር ታንቃ ሞተች

(ነቢዩ ሲራክ)
ethio maids


በጅዳ መጠለያ አንዲት የኮንትራት ሰራተኛ በጅዳ ቆንስል በር ታንቃ ሞተች
በሪያድ “ኢትዮጵያዊቷ አሰሪዎቿን ለመበቀል የ6 አመት ህጻን ገደለች” የሳውዲ ጋዜጣ ዘገባ
ኮንትራት ስራ መጥተው ተፈናቅለው በጅዳ ቆንስል መጠለያ ከሚገኙት ቁጥራቸው ወደ 80 ከሚጠጉት እህቶች መካከል አንዷ እህት ከሁለት ቀናት በፊት  እሁድ ጁን 23 ቀን 2013 በጅዳ ቆንስል ግቢ በር ራሷን አንቃ መግደሏ ታውቋል። ጉዳዩን ለማጣራት  የዚህችው እህት ሬሳ ከቦታው ሲነሳ በቦታው ነበሩ ወደ ተባሉት በጅዳ ቆንስል የዲያስፖራና ተፈናቃይ ዜጎች ሃላፊ ወደ ሆኑት ቆንሰል ሙንትሃን በስልክ ለማግኘት ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም።
ስለተፈጠረው አሳዛኝ ክስተት አካባቢው ከነበሩ የአይን እማኞች ለማጣራት ባደረግኩት ሙከራ ሟች በኮንትራት ስራ ከወሎ ወደ ሳውዲ አረቢያ መጥታ ከአመት በላይ ከሳውዲ አሰሪዎች ቤት ስትሰራ ከቆየች በኋላ በስራ ብዛት እግሯን ስላመማት ከስራ መፈናቀሏንና ወደ ጅዳ ቆንሰል መጠለያ መጠጋቷን ገልጸውልኛል። ያም ሆኖ በመጠለያው ትኖር የነበረች ይህችው እና የአእምሮ ሁከት ይስተዋልባት ያልነበረው እህት ባልታወቀ ምክንያት ሊነጋጋ ሲል ከቆንስሉ ግቢ በር ታንቃ መገኘቷን እንዳስደነገጣቸው እማኞች በእንባ እየታጠቡ አስረድተውኛል።
“መረጃ ለጋዜጠኛ ከሰጣችሁ ከመጠለያ ትባረራላችሁ!” የሚል ማስጠንቀቂያ ከመጠለያ ሃላፊዎች የተሰጣቸው ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉት እኒሁ የአይን እማኝ ተፈናቃዮች “ታመው የሚሰቃዩት እና እያበዱ የሚመጡት አህቶች ሁከትና ረብሻ የቀረነውን ሊያሳብደን ነው” ሲሉ ያሉበትን አስከፊ ሁኔታ ገልጸውልኛል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሟች ማንነትና ተዛማጅ መረጃዎችን ለማሰባስብ ባደረግኩት ሙከራ ሟች ከመሞቷ ከአስር ቀን በፊት ከቆንሰሉ በመጠለያ ስትጨናነቅ ያገኟት አንድ ኢትዮጵያዊ በጉዳዩ ተቆጭተው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ያነሱትን ምስል አግኝቼ ተመልክቸዋለሁ።  በዚሁ ተንቀሳቃሽ ምሰል ቪዲዮ ላይ ሟች የመጣችው ከወሎ ሃይቅ አካባቢ መሆኑን ያስረዳች ሲሆን አንድ አመት ከሰባት ወር የሰራችበትን ደመወዝ አረቦች ሰጥተው ከመጠለያው ቢጥሏትም ገንዘቧ የት እንደ ገባ እንደማታውቅ በትካዜ ስትገልጽ ትታያለች። የምትፈልጊው ምንድን ነው ብለው ሲጠይቋትም ወደ ሃገሯን ለመግባት ብትፈልግም ሊሳካላት አለመቻሉን ተስፋ ቆርጣ ስታስረዳ የተቀረጸው ተንቀሳቃሽ  ምስል ያሳያል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከበርካታ ወራት በፊት አንድ ወንድም ወደ ቆንሰሉ ግቢ እንዳይገባ ተከልከሎ በቆየበት በር ህይወቱ ማለፉ አይዘነጋም ። አንዲት የኮንትራት ሰራተኛ በቆንስሉ ግቢ አትገቢም ተብላ በመታገዷ ራሷን ስታ እንደነበር ይታወሳል። ይህችው እህት ከቆንሰሉ አካባቢ በሚገኝ ዛፍ ተንጠልጥላ ሶስት ቀናት ከቆየች በኋላ ያለቸበት ሁኔታ ታውቆ ከዛፉ እንድትወርድ ሲያግባቧት አሻፈረኝ በማለት ራሷን ከዛፉ ወደ መሬት ወርውራ መግደሏ ራሷን አጥፍታለች።
ከሳምንት በፊት ታዋቂው የሳውዲ እለታዊ ጋዜጣ ሳውዲ ጋዜጥ ተቡክ ተብሎ በሚታወቀው የሳውዲ ግዛት አንድ ኢትዮጵያዊት ራሷን መግደሏን ማስታወቁን በቁጥር 2 ዝንቅ መረጃየ ላይ ዘግቤው ነበር። በተመሳሳይ ዜና በዚያው ከሳምንት ካሚስ ምሽት ተብሎ በሚታወቅ አንድ የሳውዲ ግዛት አንዲት እህት “ራሷን ገድላለች” ተብሎ ሬሳዋን ወደ ሃገር ቤት ለመላክ በዝግጅት ላይ መሆኑንም መረጃውን አቀብየ እንደነበር አይዘነጋም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በዋና ከተማዋ በሪያድ አንዲት ኢትዮጵያዊት የ26 አመት ወጣት የኮንትራት ሰራተኛ “በአሰሪዎቿ ደረሰብኝ የምትለውን አስከፊ እንግልት ለመበቀል የ6 አመት የአስሪዎቿን ሴት ህጻን መግደሏን አምናለች” የሚል አንገት ሰባሪ ዜና የተሰማው ትናንት ሲሆን ዛሬ የወጡት የሳውዲ ጋዜጦችም መረጃውን ይፋ አድረገዋል።
በኮንትራት ሰራተኞች ዙሪያ ሊሰሙት የሚዘገንን መረጃ መተላለፍ ከጀመረ አመታት የተቆጠረ ቢሆን መንግስት ትኩረት ስላልሰጠበት ችግሩ ሲባባስ ቆይቷል። ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ግን በስደቱ እየሆነ ላለው በሚመለከት ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች በተገኙበት በሚሊኒየም አዳራሽ ዘጋቢ ፊልም ከታየ ወዲህ መንግስት ጉዳዩን ለመቆጣጠር ቁርጠኛ አቋም እንደሚወስድ ቃል መገባቱ አይዘነጋም።
ከኮንትራት ስራ ጋር በተያያዘ በሳውዲ አረቢያና ኢትዮጵያ መካከል የኮንትራት ሰራተኛን በሚመለከት የሁለትዮሽ ስምምነት እንደሌለ የጅዳው ቆንስል አቶ ዘነበ ከበደ በጀርመን ራዲዮ “እንወያይ” ፕሮግራም ተጋብዘው ባደረጉት ውይይት ማስታወቃቸው አይዘነጋም። ከሶስት አመት በፊት በሳውዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 120 ሺህ ገደማ ይገመት የነበረ ሲሆን የኮንትራት ሰራተኞች ያለ ሁለትዮሽ ሰምምነት መምጣት ከጀመሩበት ካሳለፍነው ሶስት አመት ወዲህ የኢትዮጵያውያኑ ቁጥር 500 ሺህ መድረሱ ይገመታል።
(ነቢዩ ሲራክ በፌስቡክ ገጹ “ከዝንቅ መረጃ” አምዱ ካቀረበው የተወሰደ)

ምነዋ ! ማንዴላችን ? !

(ነብዩ ሲራክ)
mandelaa


ምነዋ ! ማንዴላችን ? ! 
ድምጽህ ቁርጥ ቁርጥ  አለ አመመህ
ምነው ደከመህ በማረፊያህ ?
አፍሪካን ከአንባገንን ልጆቿ ጸድታ ሳታይ
ምነዋ መድከም ማሸለብህ ?
የኢትዮጵያን ስርየት ሳይበሰር
ምነዋ የመለየት ጉዞን መጀመርህ
ኢትዮጵያ ከደዌ ተላቃ ሳትጎበኛት
ምነዋ አትቀስቅሱኝ አልክ አንቀላፋህ ?
ምነዋ መልአከ ሞት ከበበህ
የስንብት መርዶ ጽልማሞት ግርማውን አለበሰህ
ምነዋ ጠንካራውን ጉልበትክን ፈተነብህ
የእማማን አፍሪካን ድህነት ማየቱ ታከተህ !
ምነዋ ማንዴላ?. . .
(ይህ ከግጥሙ ተቀንጭቦ የተወሰደ ሲሆን ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
ነቢዩ ሲራክ

በረከት ስምኦን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየዶለቱ ነው - (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ሊቀመንበርንት ከሚመራው ግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ በረከት ስምኦን የሚመሩት የመንግስት አካል በምስጢር እየዶለተ መሆኑን ምንጮች ጠቆሙ። በቅርቡ በአንድ ድረገፅ ላይ የወጣውን የዶ/ር ብርሃኑን ንግግር በማስረጃነት ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉት አቶ በረከትና ተከታዮቻቸው በአገር ውስጥ እየተንቀሳቅሰ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ « ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው፤ ከግንቦት ሰባት የገንዘብ ድጋፍ ይደረግለታል» በሚል እነበረከት ድምዳሜ ላይ መድረሳቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የፓርቲውን አመራሮች «ከሽብረተኛ ቡድን ጋር በመገናኘት» ብለው ለመክሰስ ሴራ እያበጃጁ መሆኑን አስውታውቀዋል። የፓርቲው አመራሮችን ከማሰር ባለፈ «ሰማያዊ ፓርቲ በሽብርተኛ ድርጅት የሚረዳ ነው» በሚል በአገር ውስጥ የሚኖረውን የፓርቲው ቀጣይ ህልውና ለማክሰም ጭምር እየዶለቱ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። ከበረከት በተጨማሪ ደብረፂዮን ይህንን ሴራ በበላይነት እየመከሩበት እንደሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ ለሚገኝ አንድ ጋዜጠኛ ከገዢው ባለስልጣናት ዳጎስ ያለ ገንዘብ እንደተላከለት የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። መጀመሪያ 250.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) ፣ በማስከተል 50.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ሃዋላ እንደተደረገለትና ባጠቃላይ 300.00 (ሶስት መቶ ሺህ ብር) በዶላር ተመንዝሮ በእጁ እንደደረሰው ምንጮቹ ጠቁመዋል። ገንዘቡ ከነበረከት በኩል በምስጢር የተላከ መሆኑን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚሁ መሰረት ጋዜጠኛው ለሕወሐት/ኢህአዴግ ማገልገል መቀጠሉንና በተለይ አሁን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየተሸረበ ያለው ሴራ መነሻው ይህ ሰው እንደሆነ አያይዘው ገልፀዋል።

በቤተመንግስት ግቢ ዙሪያ አንድ ሰው ተገድሎ ተገኘ

ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሀሙስ ከጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ጽህፈት ቤት ጀርባ ሁለተኛው በር ከ150 እስከ 200 ሜትር ባለ ርቀት ላይ አንድ ጎልማሳ አንገቱ ተቆርጦ  መገኘቱን የአይን እማኞች ለኢሳት ገልጸዋል።  
እማኞች እንደሚሉት  ሟቹ እድሜው ከ45 እስከ 53 የሚጠጋ ጸጉር አልባ ጎልማሳ ነው። የሟቹ የራስ ቅል ባእታ ክሊኒክ አቅራቢያ ባለ አንድ ቦታ ላይ ተጥሎ መገኘቱን የጠቆሙት ነዋሪዎች፣ ፖሊስ በአካባቢው ተገኝቶ አስከሬኑ እንዲነሳ ከአደረገ በሁዋላ ለአስከሬን ምርመራ ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል እንዲወሰድ አድርጓል።
የአይን እማኞች ” አካባቢው 24 ሰአት ሙሉ በስለላ ካሜራዎች የሚጠበቅ በመሆኑ ድርጊቱ በቤተመንግስት ጠባቂዎች ካልተፈጸመ በስተቀር በሌሎች ዜጎች ተፈጽሟል ብሎ  ለማመን አስቸጋሪ ነው” ይላሉ።
በጉዳዩ ዙሪያ የሚኒሊክ ሆስፒታልንና አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ለማነጋገር ላለፉት 5 ቀናት በተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም የሚኒሊክ ሆስፒታል ዛሬ መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ ሲሆን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር፣ የህዝብ ግንኙነት እና የወንጀል ምርመራ ክፍሎች ስልኮች አይነሱም። ሚኒሊክ ሆስፒታል የአስከሬን ምርመራ ውጤቱን በተመለከተ መውሰድ የሚችለው ፖሊስ በመሆኑ ፖሊስን መጠየቅ አለባችሁ የሚል መልስ ሰጥተዋል።
የአካባቢውን ሁኔታ በደንብ የሚያውቁ አንድ ሰው እንደገለጹት አስከሬኑ በተገኘበት አካባቢ፣  በምሽት  ሰዎች እንደሚይዘዋወሩ ገልጸው ግድያው የተፈጸመው ምናልባትም በጠባቂዎች ሊሆን ይችላል ብለዋል። ያም ካልሆነ ግን መንግስት በመገናኛ ብዙሀን መረጃውን ይፋ ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል ግለሰቡ ።

Monday, June 24, 2013

“አሜሪካ አቋማን የምትፈትሽበት ወቅት ላይ ናት” ክሪስ ስሚዝ

"አሸባሪነትን መዋጋት የግፍ ማከናወኛ ሽፋን አይሆንም"
gear 1


ኢህአዴግ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ስም ከአሜሪካ ጋር የመሰረተውን ግንኙነት አስታክኮ የሚፈጽመው ኢሰብዓዊ ድርጊት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ተገለጸ። አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምትከተለውን ፖሊሲ የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች ተባለ። ኢህአዴግ ጸረሽብርተኝነትን ለአፈናና ለበጀት ማሟያ እየተጠቀመበት እንደማይቀጥል ተመለከተ።
አሜሪካና ሌሎች ለሰብአዊ መብት መከበር ዋጋ የሚሰጡ አገሮች በሙሉ በ”አዲስ አበባው” አገዛዝ ላይ ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ያለ አንዳች ማወላወል ማሳየት እንደሚገባቸው እንደራሴ (ኮንግረስማን) ክሪስ ስሚዝ ያስታወቁት ሽብርተኛነትን አስመልክቶ ጠንካራ ማሳሰቢያ በማስቀመጥ ነው።
እንደራሴ ስሚዝ የኢትዮጵያ ጉዳይ የተደመጠበትን የምክክር ሸንጎ ከዘጉ በኋላ በተለይ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት “አሜሪካ በኢህአዴግ ላይ ያላትን አቋም የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች” ብለዋል።
አሜሪካ ከሰብአዊ ርዳታ ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግና በተለይም ኢትዮጵያና አሜሪካ አሸባሪነትን በመዋጋት በኩል አብረው እንደሚሰሩ ያመለከቱት እንደራሴው፣ “ሽብርንና ሽብርተኛነትን የመታገል ትብብር ግን የዜጎችን ሰብአዊ መብት ለመርገጥ ፍቃድ ማግኛ አይደለም። የመብት ረገጣ ሽፋን ሊሆን አይገባም” በማለት የኢህአዴግና የመሪዎቹን ተግባር ኮንነዋል።
“አንድ አገር ገና ለገና ሽብርተኛነትን ለመዋጋት ከአሜሪካ ጎን ስለቆመ ብቻ የህዝብ ሰብአዊ መብቶችና የዴሞክራሲ አተገባበር ላይ ዝም ሊባል አይገባም” በማለት አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት ስሚዝ፣ ሽብርን መዋጋት የኢትዮጵያ የራስዋም ፍላጎት አንደሆነ አመልክተዋል።
“ስለዚህ” አሉ ክሪስ ስሚዝ፣ “ስለዚህ የአሜሪካ መንግስትም ሆነ ሌሎች የምራብ አገራት፣ ኢህአዴግ ኢትዮጵያዊያን ላይ እየፈጸመ ያለውን ተግባር በመረዳት አቋማቸውን በግልጽ ማስቀመጥ ይገባቸዋል”
“ለሰብአዊ መብት መከበር ዋጋ የሚሰጡ አገሮች በአዲስ አበባው መንግስት ላይ የማያወላውል ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ማሳየት አለባቸው” ሲሉ የተደመጡት ክሪስ ስሚዝ “ከዚህ ቀደም አርቅቄ፣ አስተዋውቄ፣ ለውይይት አቅርቤው የነበረውን ኤች አር 2003 ህግ እንደገና በማሻሻል ለድምጽ አቀርበዋለሁ” ብለዋል።
“የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ህገደንብ” የሚል ስያሜ ያለው ህግ፣ ኢትዮጵያን የሚመራው ኢህአዴግ ከአሜሪካ መንግስት ለሚፈልገው ማናቸውም ድጋፍ መሟላት የሚገባቸውን የሰብአዊና የዴሞክራሲ መብት ግብአቶችን በቅድመ ሁኔታ የሚያስቀምጥ ነው። እንደራሴ ክሪስ እንደገና ለድምጽ እንደሚያቀርቡት ደጋግመው የገለጹት ይህ ህግ ኢህአዴግ በከፍተኛ ደረጃ ገንዘብ አፍስሶ በአሜሪካን ጎትጓቾች (ሎቢዪስቶች) ዘመቻ ያካሄደበት ነው።
መለስን ”አሮጋንት/ዕብሪተኛ/“ በማለት የገለጹት ክሪስ ስሚዝ “ከመለስ ሞት በኋላ ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ አቅጣጫ ታመራለች” የሚል እምነት እንደነበራቸው በመናገር “የሰማሁት ምስክርነት ከዚህ የተለየ፣ ተስፋ ከተደረገው ተቃራኒ ነው” ብለዋል። እሳቸው ብቻ ሳይሆኑ “ብዙዎች” ሲሉ በጥንቃቄ የገለጹዋቸው አካላት ከመለስ ሞት በኋላ በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ መንግድ ታመራለች የሚል እምነት እንደነበራቸው ሳይሸሽጉ ተናግረዋል። በውል የታየው ነገር ኢትዮጵያዊያን ወደ ባሰበት ችግርና የመብት ረገጣ የመዘዋወራቸው ጉዳይ እንደሆነ አመልክተዋል። ይህም አሳሳቢ እንደሆነ ጠቁመዋል።
በማብቂያቸውም “አሁን ፖሊሲያችንን ዳግም የመፈተሽያ ጊዜ ላይ ነን። ቁም ነገሩ ከተጨቆኑት ወገኖች ጋር መቆሙ ላይ ነው። ከተጨቆኑት ወገኖች ጋር እንቆማለን” የሚል ከተለመደው የአሜሪካ አቋም የተለየ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አቶ ኦባንግ ሜቶና ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የተገኙበትን የምክክር ሸንጎ ተከትሎ እስካሁን ድረስ የኢህአዴግ አቋምና ምላሽ አልታወቀም። ይሁን እንጂ ቀደምሲል ኤች አር 2003 ህግ ሆኖ እንዳይጸድቅ ኢህአዴግና ወዳጅ ባለሃብቶች ተመሳሳይ ተግባር ለማከናወን ሩጫ መጀመራቸው ተሰምቷል። በተጨማሪም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የዲፕሎማሲ ጅምናስቲክ መጀመሩ ታውቋል።
የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በተለያየ ወቅት መለስ በሽብርተኛ ትግል ሰበብ አሜሪካንንና የምዕራቡን ዓለም እያምታቱ እንደሆነ በተደጋጋሚ መገለጹ ይታወሳል። ሆን ተብሎ በተሽከርካሪዎች ላይ የተቀነባበረ የፈንጂ ማፈንዳት፣ ህዝብን የማሸበር ተግባር እንደሚፈጸም በማመልከት ተቃዋሚዎች ሲጮሁ ሰሚ አልነበራቸውም። የሹልክዓምድ (ዊኪሊክስ) መረጃ ይህንኑ ይፋ ማድረጉና ኢህአዴግ ራሱ ፈንጂ አፈንድቶ “አሸባሪዎች ፈንጂ አፈነዱ” በሚል እንደሚያምታታ ማጋለጡ ይታወሳል።
አቶ መለስ አሜሪካና ምዕራባዊያን ሰብአዊ መብትን፣ ምርጫንና የዲሞክራሲ መብቶችን አስመልክቶ ጥያቄ ሲያቀርቡላቸው “ጦራችንን ከሶማሊያ እናስወጣለን፣ ቀጠናው ቢተራመስ ተጠያቂ አይደለንም” የሚል ምላሽ  እየሰጡ ያስፈራሩ እንደነበር የሚጠቁሙ የጎልጉል ምንጮች “ኢህአዴግ ብር ሲፈልግና ካዝናው ሲጎድል ዘወትር የሚያነሳው የሽብርና አሸባሪዎችን የመታገል ውለታ ድርጎ ነው” ብለዋል። በ1997 ምርጫ ወቅት የተሸነፈው ኢህአዴግ በወቅቱ አሜሪካን ጫና ልታደርግ ስትሞክር “ሰራዊታችንን ይዘን ወደ ክልላችን እንገባለን። ተቃዋሚዎች ጦር የላቸውም። በቀጣናው ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂ አይደለንም” በማለት አቶ መለስ አሜሪካን ጫናዋን አቁማ ከህወሃት ጎን እንድትቆም ማድረጋቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ይናገራሉ። ያም ሆነ ይህ እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ኢህአዴግ የውጪውን ዓለም የሚጋልብበትን የፖለቲካ “ጆከሩን” ወይም “ሽብርን መታገል” መርጠው ” ካሁን በኋላ በዚህ ሂሳብ መጫወት አይቻልም” ማለታቸው ቀጣዩን የፖለቲካ ጨዋታ እንደሚያከረው ተገምቷል።

Saturday, June 22, 2013

አቶ ኦባንግ ሜቶ እስራኤል ገቡ

israel


የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል ባደረገላቸው ጥሪ መሰረት አቶ ኦባንግ ሜቶ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር በ21/06/2013 እስራኤል በሰላም ደርሰዋል፡፡ በወቅቱም የማህበሩ አባላት በቤንጎሪዮን አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
በ22/06/2013 የሚካሄደውን ጉባኤ አጠቃላይ ስነ ስርአት የያዘ ዘገባ በተከታታይ የምንልክ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡
የአቀባበሉ ሥነስርዓት ምስል ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ
ከሰላምታ ጋር
ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ
የኢትዮጵያ እናድን አንድነት ማህበር ሊ/መንበር

የትኛው አማራጭ ለአሜሪካ?

“ኢህአዴግን ምን እናድርገው? ንገሩን!”



hearing3አሜሪካ ከመቼውም ጊዜ በላይ ደንግጣለች። ኦባንግ እንዳሉት ለህዝባቸው “ሬት” ለምዕራባውያንና “ማር” (የቤት ቀጋ፤ የውጭ አልጋ) የነበሩት አምባገነን በድንገት እንደ ተነቀለ ቡሽ ተስፈንጥረው ከሲስተም መውጣታቸው አሜሪካንን አስጨንቋታል። በተለይም እሳቸው አፍነው የያዙት የስርዓቱ “ክፉ ጠረን” አሁን እነርሱ (አሜሪካውያኑ) ደጅ የደረሰ ያህል መፍትሄ ለመፈለግ የወሰኑ ይመስላሉ። አውቀውና ፈቅደው ሲታለሉ የቆዩበትን ጊዜ አስልተው መንገዳቸውን የማስተካከል ስራ የጀመሩት ዛሬ አይደለም። አንዳንድ ምንጮች እንደሚሉት ከመለስ ሞት በኋላ አሜሪካ በምስራቅ አፍሪካ ላይ ሚዛኗን ሊያስታት የሚችል ውድቀት የሚደርስባት ኢትዮጵያ ላይ ያላትን አቋም ማስተካከል ሲያቅታት ብቻ እንደሆነ ይናገራሉ።
“… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮት ዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ ያላት አገር ቤተሰብን የመምራትና የማስተዳደር ተሞክሮ የሌላቸው፣ አገርን መምራትን የሚያክል ታላቅ ሃላፊነት ማሸከም ለኔ ከአእምሮ በላይ ነው …” የዛሬ 22ዓመት ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ ከተናገሩት፡፡
“አሜሪካኖች ነጻ እንድታወጡን አንጠይቃችሁም። የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ነጻ እንደሚወጣ ያውቃል። እናንተ ግን በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑብን፤ (የነጻነት መንገዱን አትዝጉብን)። ከመንገዱ ላይ ገለል በሉ … እስካሁን ያልተሞከረ መንገድ አለ … እሱም እርቅ ነው … ከመንግሥትም ሆነ ከተቃዋሚው በኩል ዓመኔታ የሚጣልባቸው አሉ … ” አቶ ኦባንግ ሜቶ፡፡
“የሚታየኝ ጦርነት ነው፣ የርስ በርስ ግጭት ነው። የርስ በርስ ግጭት በኢትዮጵያ የመነሳቱ ጉዳይ የማይቀር ነው። አገሪቱ ላለፉት 21 ዓመታት በተጓዘችበት መንገድ አትቀጥልም። … ሕዝብ በጭቆና አገዛዝ እየተገዛ ዝም ብሎ የማይኖርበት ደረጃ ላይ ደርሷል … ዝም ብሎ ግን አይቀመጥም … ይፈነዳል … ይህን እንድትገነዘቡ እፈልጋለሁ” ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፡፡
አቶ መለስ “አሮጋንት /እብሪተኛ/፤ የፈለገውን ነገር በፈለገው ጊዜ የሚያደርግ ሰው … እንደነበር አዲስ አበባ ሄጄ ባነጋገርኩበት ወቅት አረጋግጫለሁ” ክሪስ ስሚዝ፡፡
“እድሜ ልካችሁን አትገዙም ብለን መክረናቸዋል” ዶናልድ ያማሞቶ፡፡
 hearing1የምክክሩ መድረክ
“ኢትዮጵያ ድኅረ መለስ፤ የዴሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶች የወደፊት ዕጣ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ፤ ከኢትዮጵያ ሁለት ተናጋሪዎች ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ ኦባንግ ሜቶ፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር የአፍሪካ ጉዳዮች ተጠባባቂ ጸሐፊ ዶናልድ ያማሞቶ፣ የአሜሪካ የዓለምአቀፍ የልማት ተራድዖ የአፍሪካ ቢሮ ረዳት አስተዳዳሪ ኤሪል ጋስት፤ የማይክል አንሳሪ የአፍሪካ ተቋም ዳይሬክተር ዶ/ር ፒተር ፓሃም እንዲሁም በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የመንግሥት ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አዶቴ አክዌ የተጋበዙበት የምክክር ሸንጎ ላይ የቀረቡት ሃሳቦች በርካታ ጉዳዮችን የዳሰሱ ነበሩ። ሰብሳቢው በአሜሪካ የተወካዮች ምክርቤት በአፍሪካ፣ በዓለምአቀፍ ጤናና ሰብዓዊ መብቶች እንዲሁም ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ንዑስኮሚቴ ሰብሳቢ ክሪስቶፈር ስሚዝ ደግሞ ኢህአዴግ ከፍተኛ ገንዘብ አፍስሶ ያኮላሽው ኤችአር2003 የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ረቂቅ ህግ ከሟቹ ዶናልድ ፔይን ጋር በማዘጋጀት በምክርቤት ለማስወሰን ያስቻሉ ነበሩ።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ፣ እንዲሁም በበክኔል ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት የግንቦት 7 ሊቀ መንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እንደ እምነታቸው ንግግር አድርገዋል። ለተጠየቁት ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል። በምክክር ሸንጎው ላይ ከተጋበዙት መካካል ኢህአዴግ በቀጥታ ባለመወከሉ “ያለመመጣጠን (ያለመወከል)” ችግር አልነበረም፡፡ ኢህአዴግም ተገኝቶ ቢሆን ኖር ሊናገረው ከሚችለው በላይ ተናጋሪና ተከራካሪ ስለነበረው የኢህአዴግ መኖር አስፈላጊ አልነበረም የሚል አስተያየት ስብሰባውን በአካል ተገኝተው ከታዘቡና በቀጥታ ስርጭት ከተከታተሉ ወገኖች  ተደምጧል።
ያም ሆኖ ግን ምክክሩ ከመካሄዱ ቀደም ብሎ በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የበላይ ሰው ክሪስ ስሚዝ ቢሮ በመገኘት አሉ የሚሏቸውን መከራከሪያዎች አቅርበው ነበር። የጎልጉል ምንጮች ለማረጋገጥ እንደቻሉት ኢህአዴግ ምክክሩን ተከትሎ ኤች አር 2003 ረቂቅ ሕግ እንዳይጸድቅ የተጠቀመበትን መንገድ ገና ካሁኑ በድጋሚ ጀምሯል።
ለኢትዮጵያውያን ሁሉ እያደር የእግር እሳት ሆኖ ያለፈውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ ወደ ኢትዮጵያ በማምራት ከኢህአዴግ መሪ አቶ መለስ ጋር በርካታ ዲፕሎማቶች ተነጋግረዋል። አንዱ ከኒውጀርሲ ጠቅላይግዛት የአሜሪካ ም/ቤት ተወካይ ክሪስ ስሚዝ ነበሩ። “ኢትዮጵያ ከመለስ በኋላ” በሚል የተዘጋጀውን የምክክር ሸንጎ በመሪነታቸው ሲከፍቱ አቶ መለስን “አሮጋንት /እብሪተኛ/፤ የፈለገውን ነገር በፈለገው ጊዜ የሚያደርግ ሰው …” በማለት ነበር የገለጹዋቸው። የርሳቸው ገለጻ ታዲያ ከሁለት ዓስርተ ዓመታት በፊት ኢህአዴግ እንዲነግስ ሲወሰን ከቃል በላይ እሳት እየተፉ ንግግር ያደረጉትን ኢትዮጵያዊ አስታወሰ – የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ!
“… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮት ዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ ያላት አገር ቤተሰብን የመምራትና የማስተዳደር ተሞክሮ የሌላቸው፣ አገርን መምራትን የሚያክል ታላቅ ሃላፊነት ማሸከም ለኔ ከአእምሮ በላይ ነው …” ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ የትንቢት ያህል፤ ሳግ እየተናነቃቸው የኢትዮጵያን ተላልፎ መሰጠት በዚሁ በሰኔ ወር ከ22ዓመት በፊት አስረግጠው በማስረጃና በማስጠንቀቂያ በመቃወመ፣ በማሳሰብ፣ እንደማይሆን በመምከር፣ አድሮ እንደሚያቃጥል በማስጠንቀቅ፣ ላቀረቡት ንግግር የክሪስ ስሚዝ ገለጻ በማረጋገጫነት የሚቆም እውነት ይሆናል።
አሜሪካ ራስዋ ቀብታና ባርካ በትረ ሹመት የሰጠቻቸውን ሰዎች ከ22ዓመት በኋላ መልሳ “ገምግሙልኝ” ማለቷ አስገራሚ የሚሆንባቸው ጥቂት አይደሉም። ሰብሳቢው በመግቢያቸው የተናገሩት የኢትዮጵያ መንግስት ወቅታዊ መገለጫ፣ ቀደም ሲል ሚ/ር ያማሞቶን በመጥቀስ ዊኪሊክስ ይፋ ያደረጋቸውን መረጃዎች ለተከታተሉ “አሜሪካኖቹ ምን የማያውቁት ነገር አለና ነው የሚጠይቁት ያሰኛል” በሚል የሚገረሙ በርካታዎች ናቸው።
obang at hearingለዚህ ይመስላል የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ታሪካዊውን የኮሎኔል ጎሹ “ትንቢትና የኢትዮጵያ ህዝብን የሚወክል የምልጃ መቃተት” በማስታወስ ቀዳሚ የሆኑት። አስከትለውም “አሜሪካኖች ነጻ እንድታወጡን አንጠይቃችሁም። የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ነጻ እንደሚወጣ ያውቃል። እናንተ ግን በነጻነት መንገዱን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑበት። (ከመንገዱ ላይ ገለል በሉ)” የሚል መልክት አስተላለፉ።
የጋራ ንቅናቄው መሪ በድርጅታቸው መርህ ላይ ተመሥርተው በሰጡት የምስክርነት ቃል “ህወሓት እስካሁን በነጻአውጪ ስም አገር እየመራ እንደሆነ፤ መለስ ለህዝባቸው “ሬት” ለምዕራባውያንና “ማር” (የቤት ቀጋ፤ የውጭ አልጋ) ዓይነት መሪ እንደነበሩና የኢትዮጵያ ሕዝብ ላለፉት 22ዓመታት በመከራ ውስጥ ያለና የዛሬ 8ዓመት በዚሁ ቦታ ላይ ያማሞቶ ኢትዮጵያ በአቋራጭ መንገድ (ክሮስሮድ) ላይ እንደምትገኝ” መናገሩ አቶ ኦባንግ ካስታወሱ በኋላ “መቼ ነው መንገዱን የምናቋርጠው? ከስምንት ዓመት በኋላ አሁም አንሻገርም ወይ፤ አናቋርጠውም ወይ” በማለት ተሰብሳቢውን ያስደመመ ለሰብሳቢዎቹ ግልጽ ጥያቄ ጠይቀዋል፡፡
አቶ ኦባንግ ሲቀጥሉም “ኢትዮጵያውያን የምንጠይቀው በጣም ቀላል ጥያቄ ነው፤ አሜሪካኖች የሚመኩበትን ሰብዓዊ መብት እኛ ተነፍገናል፤ የራሳችን ክሪስ ስሚዝ ይኑሩን ብቻ ነው የምንለው” ካሉ በኋላ በኃይለሥላሴም ሆነ በመንግሥቱ ጊዜ ኢትዮጵያውያን ዕድላቸውን እንደተነፈጉ አስታውሰዋል፡፡ በወቅቱም በዚሁ ም/ቤት የዛሬ 22ዓመት በወርሃ ሰኔ ኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ የዛሬዋን ኢትዮጵያን መተንበያቸውን አቶ ኦባንግ በንግግራቸው አስታውሰዋል፡፡ አሁንም የኢትዮጵያውያንን ቁርጠኛ አቋም ምን እንደሆነ ለአሜሪካውያኑ ግልጽ አድርገዋል “አሜሪካ እንድታድነን አይደለም የምንጠይቀው፤ ራሳችንን ማዳን እንችላለን፤ በነጻነት መንገዳችን ላይ ግን ዕንቅፋት አትሁኑብን፤ ራሳችንን ነጻ እናወጣለን፤ ኦባማ ለፕሬዚዳንትነት ሲወዳደር በርካታ ኢትዮጵያውያን ከሚያገኙት ጥቂት ደመወዝ ለምርጫው ዘመቻ ረድተው ነበር፤ ከኦባማ ግን የሰማነው ነገር እስካሁን ምንም የለም፤ ነጻነታችንን እየለመንን አይደለም፤ ራሳችንን ነጻ እናወጣለን” በማለት የበርካታ ኢትዮጵያውያንን የነጻነት መንፈስ የቀሰቀሰ ንግግር አድርገዋል፡፡
በመጨረሻም አሜሪካ ለኢትዮጵያ መንግሥት የዴሞክራሲ ለውጥ 300 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ ሰጥቻለሁ እንደሚል ከጠቀሱ በኋላ “ይህ ሁሉ ገንዘብ የት ነው የገባው፤ የት ነው የሄደው” በማለት ኢህአዴግ ከቀበሌ ጀምሮ እስከላይ ሥልጣኑን እንደተቆጣጠረ፤ ሙስሊሙ መሪውን እንምረጥ ሲል አሸባሪ ተብሎ እንደሚፈረጅ ነገር ግን እኛ ኢትዮጵያውያን ከሙስሊም ወገኖቻችን ጋር አገርና መሬት ብቻ ሳይሆን የምንጋራው በደም የተሳሰርን መሆናችን አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ አንድ ጊዜም እንኳን ጦርነት ሰብከውም ሆነ መሳሪያ አንስተው የማያውቁ መሆናቸውን የተናገሩት ኦባንግ፤ በኢትዮጵያ መንግሥት “አሸባሪ” መባላቸውን በመናገር የኢህአዴግን አሸባሪነት አጋልጠዋል፡፡ እስካሁን በአገራችን ላይ የፈሰሰው ደም በቂ እንደሆነ የጠቆሙት የጋራ ንቅናቄው መሪ፤ በኤድስና ምግብ በማጣት የረደሰብን ዕልቂት በቂ እንደሆነና ከእንግዲህ ወዲህ መጋደል እንደሌለብን ሆኖም ከኢህዴግም ሆነ ከተቃዋሚ በኩል አመኔታ የሚጣልባቸው ሰዎች ስላሉ እስካሁን ያልተሞከረውን የዕርቅ መንገድ (ሥራ) በኢትዮጵያ መከናወን እንዳለበት አቶ ኦባንግ ሜቶ በሚመሩት ድርጅት መርህና በሚታገሉለት የማዕዘን ሃሳብ ላይ ተተርሰው ሃሳባቸውን አጠቃልለዋል፡፡
በምክክር ሸንጎው ላይ የተገኙት የግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው የንግግራቸውና የማሳሰቢያቸው ማሳረጊያ ሊባል የሚችል መልዕክት አስተላልፈዋል። ዶ/ር ብርሃኑ “አስተውሉ፣ ልብ ብላችሁ ተገንዘቡ” በማለት ያሳሰቡት ዛሬ ኢትዮጵያን የሚወዱ ሁሉ የሚጠበቡበት፣ እንዲከሰት የማይፈልጉትን የመጨረሻው ስጋት ነው።nega
በምክሩ ላይ በቀዳሚነት ምልከታቸውን ያብራሩት ዶ/ር ብርሀኑ ኢህአዴግ የዘረጋው የአፈና ስርዓት ያስመረረው ህዝብ፣ ኢህአዴግ ሆን ብሎ የሚያንኮታኩታቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሆን ብሎ የሚተናኮለው ህዝብ፣ ያለው ብቸኛ አማራጭ ብረት ማንሳት ብቻ እንደሆነ አመልክተዋል። በቅርቡ የኢህአዴግ የአፈና ስርዓት ፈተና እንደሚገጥመው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አለመረጋጋት ቀጣናውን በሙሉ እንደሚረብሽና የአሜሪካንን ጥቅም በእጅጉ እንደሚጎዳ ዶ/ር ብርሃኑ በግልጽ በማስረዳት አሜሪካ ገንዘቧን በተገቢው ቦታ ላይ ማዋል እንዳለባት ምክር ሰጥተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የተቃዋሚ ኃይሎች አማራጭ ከማጣት የተነሳ ብረት ማንሳታቸውን የጠቆሙት የግንቦት 7 ሊቀመንበር፤ ሕዝብ ዝም ብሎ በአስከፊ አገዛዝ ሥር እየኖረ እንደማይቀጥል አስጠንቅቀዋል፡፡ በመሆኑም አማራጭ ሲጠፋ ባገኘው መንገድ ሁሉ መብቱን ወደማስጠበቅ እንደሚገፋና በአሁኑ ወቅትም የተቃዋሚ ኃይሎች በመተባበር በኢህአዴግ ላይ ጥቃት መሰንዘር የሚስችላቸውን ብቃትና ኅብረት እንደፈጠሩ ጠቁመዋል፡፡ ይህ ሊሆን የቻለውም ኢህአዴግ በምንም መልኩ የማይሰማና በሰላማዊ መንገድ ሥልጣን ለማስረከብ የማይችል መሆኑን በተለይ በ1997 ምርጫ ካስታወቀ ወዲህ በግልጽ የሚከተለው መርህ በራሱ ማስረጃ እንደሆነ ዶ/ር ብርሃኑ በጥያቄ መልክ ለቀረበላቸው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የኢህአዴግ የደምሥር የውጭ ዕርዳታ እንሆነ የተናገሩት የግንቦት 7 መሪ አሜሪካ ከአውሮጳውያን ጋር በመተባበርና ለእያንዳንዱ የተሃድሶ ዕርምጃ ቀነ ገደብ በመሥጠት በተሰጠው ገደብ ውስጥ እስረኞች ካልተፈቱ፤ የምርጫ ኮሚሽን ካልተቀየረ፤ ወዘተ በማለት ዕርዳታው እንደሚቆም በማስጠንቀቅ አሜሪካውያኑ ለኢህአዴግ መመሪያ ቢሰጡ ለገንዘብ ሲል ኢህአዴግ ሊታዘዝ እንደሚችል አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም በድጋሚ የሰብሳቢውን ስም በመጥራት ትኩረት የጠየቁት ዶ/ር ብርሃኑ “የሚታየኝ ጦርነት ነው፣ የርስ በርስ ግጭት ነው። የርስ በርስ ግጭት በኢትዮጵያ የመነሳቱ ጉዳይ ነው። አገሪቱ ላለፉት 21 ዓመታት በተጓዘችበት መንገድ አትቀጥልም። ይህን እንድትገነዘቡ እፈልጋለሁ” ብለዋል።
ከክሪስ አንደበት
ሰብሳቢው ክሪስ ስሚዝ በምክርቤት ስብሰባ ላይ ድምጽ መስጠት በሚገባቸው ረቂቅ ህጎች ላይ ሲሳተፉ ስለነበር ምክከሩ የጀመረው ከታቀደው ሰዓት 1፡30 ያህል ዘግይቶ በመሆኑ ይቅርታ በመጠየቅ ነበር መንበራቸው ላይ ተሰይመው ንግግር ጀመሩት። የምክክሩ ሊቀመንበር አቶ መለስ የዘረጉት አገዛዝ የሰብዓዊ መብት ረገጣ ልዩ ባህሪው እንደሆነ የተለያዩ ማስረጃዎችን በመጥቀስ ምክከሩን ከፈቱ። ምክክሩ በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ የሰብዓዊ መብቶችና የዴሞክራሲ ጉዳይ ላይ እንደሚያተኩርና የአሜሪካ መንግሥት ምን ማድረግ እንዳለበት የሚያመላከት ምክር የሚካሄድበት እንደሆነ አስገነዘቡ።
ኢትዮጵያ እስላማዊ አሸባሪነትን በቀጣናው በመዋጋት የአሜሪካ ደጋፊ አገር ሆና መቆየቷን፣ ሆኖም ግን በተመሳሳይ መልኩ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሚፈጽመው ተደጋጋሚ የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ የአሜሪካ መንግሥት የኢትዮጵያን መንግሥት ተጠያቂ ማድረግ እስካሁን አለመቻሉን ሳይሸሽጉ ተናገሩ።smith3
የፖለቲካ ድርጅቶች በነጻነት መንቀሳቀስ አለመቻላቸውን፣ መንግስታዊ ባልሆኑ የግብረ ሰናይ ድርጅቶች (መያዶች) ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ፣ ጋዘጠኞች እንደሚታሰሩ፣ በርካታ ዜጎች ከመሬታቸው እንደሚፈናቀሉ ወዘተ በመዘርዘር አስረዱ።
የአሜሪካ የዕርዳታ ድርጅት – ዩኤስኤይድ እንደሚለው ከሆነ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ግልጽ ግንኙነት ማድረግ ወደፊት የዴሞክራሲና የለውጥ ሂደቶችን ለማሳካት ይረዳል ተብሎ ቢታሰብም፣ በክሪስ ስሚዝ አመለካከት ግን እምነቱ ሊተገበር የሚችል ቢመስልም እስካሁን ምንም ፍሬ እንዳላመጣ ሳይሸሽጉ ተናግረዋል።
እንደ አምነስቲ ኢንተርናሽናል መረጃ መሠረት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ስልታዊ አፈናና የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ለሌሎች አገራት መጥፎ ምሳሌ እየሆነ መሄዱን ሊቀመንበር ስሚዝ ጠቅሰዋል፡፡ ንጹሃን ዜጎች ስቃይ፣ ድብደባ እንደሚደርስባቸው፣ በኤሌክትሪክ እንደሚጠበሱና የግዳጅ ወሲብ እንደሚፈጸምባቸው፣ የአምነስቲ ሪፖርት መዘገቡን ክሪስ ስሚዝ በእማኝነት ተናግረዋል፡፡
ራሳቸው ክሪስ ስሚዝ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ረቂቅ ህግ አዘጋጅተው እንደነበርና በወቅቱ የነበረው የጆርጅ ቡሽ አስተዳደር ግን ኢትዮጵያን በአሸባሪነት ላይ ወዳጅ በማድረጉ ምክንያት በነበረው ቸልተኝነት የተነሳ ተፈጻሚ ሳይሆን መቅረቱን አስታውቀዋል። ሚ/ር ስሚዝ እነዚህን ጉልህ ህጸጾች በመጠቆም ምክክሩ ላይ ተናጋሪ እንዲሆኑ የተጋበዙትን ክፍሎች በየተራ በማስተዋወቅ ጋብዘዋል። ከንግግሩ በኋላም ጥያቄዎችን ጠይቀዋል። ሌሎች ተሳታፊዎችም ጥያቄ በመሰንዘር ማብራሪያ እንዲወስዱ ተደርጓል።
ያማማቶ ምን አሉ?
ያማሞቶ በመግቢያ ንግግራቸው መለስን አወድሰዋል። አፍሪካን በዓለም መድረክ ከፍ እንድትል ያደረጉ መሪ በማለት አመስግነው ኢትዮጵያ ተሰሚነቷ እንዲጨምር ያደረጉ፣ ተሟጋችና ጎበዝ ተናጋሪ እንደነበሩ መስክረዋል። ኢኮኖሚውን አሳድገዋል፣ ኢትዮጵያን በቀጣናውና በዓለም ታዋቂ አድርገዋል፣ በሶማሊያ ተሟጋች፣ በሱዳን አስታራቂ፣ በአፍሪካ የአየርንብረት ጉዳይ ደግሞ አንደበተ ርዕቱ አፈቀላጤ ነበሩ በማለት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ከሚደረድረው በላይ ቃል አከማችተው ምስጋና ቸረዋቸዋል።
ያማማቶ በማያያዝ እንደ አምባሳደርነታቸው በኢትዮጵያ ያለውን የፖለቲካ ምህዳር መጥበብ አስመልክቶ አቶ መለስን ማነጋገራቸውን ጠቁመዋል። በሰብዓዊ መብቱን መጓደል ዙሪያም በተመሳሳይ መነጋገራቸውን  አክለዋል።
ካሊፎርኒያ ሎሳንጅለስ “ትንሿ ኢትዮጵያ” ወረዳ ተወካይ የምክርቤት አባል ሚስዝ ባስ፤ ያማሞቶን መስቀለኛ ጥያቄ አቅርበውላቸው ነበር። ጠያቂዋ “የኢህአዴግ መንግሥት ዋናው ችግር ምንድነው? ለምንድነው ይህንን ሁሉ መከራና አፈና የሚያካሂደው” በማለት የመገረም የሚመስል ጥያቄ ጠይቀዋል። ያማሞቶ እንደ መንተባተብ ሲሉ “ችግሩ ምንድ ነው?” በማለት ባስ በድጋሚ ጥያቄያቸውን ወረወሩ። “ችግሩ እንዳለ ነው” ሲሉ ደግመው መልስ የሰጡት ያማሞቶ “ጠቅላይ ሚ/ር ሃይለማርያም አፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ላይ እንዳሉት ነው፣ የዴሞክራሲ እሴቶች አስፈላጊ ናቸው፣ መጥፎ ህጎች መወገድ አለባቸው፣ እንስራ፣ እንሞክር ብለዋል” አሉና መለሱ።
ኮንግሬስማን ሜዶውስ በኢትዮጵያ ኢህአዴግ ሁሉን ተቆጣጥሮዋል፤ እኛ አሜሪካኖች ምን ልናደርግ እንችላለን? እንዴት ነው ልናስተካክለው የምንችለው? የሚል ጥያቄ ለያማሞቶ ወረወሩ። ያማሞቶም  “ከምርጫው በኋላ ደስተኞች አለመሆናችንን ተናግረናል፡፡ ከበስተጀርባና በፊትለፊት እየሰራን ያለነው ነገር አለ፡፡ ጊዜ የሚወስድ ነው፡፡ ለምሳሌ በሴቶች ላይ የሚደረግ የመብት ጉዳይ አለ እናም ይህንን ከዩስኤድ ጋር እየሰራን ነው” አሉ፡፡
ሜዶውስ የረኩ አይመስልም “እና ያለው ፍርሃት ምንድርነው?” ሲሉ በድጋሚ መልስ መፈለጋቸውን አመለከቱ። “ነግረናቸዋል ፣ ለዘላለም ልትገዙ አትችሉም። ስለዚህ የተቃዋሚውን ተሳትፎ ማበረታታት አለባችሁ ። እነዚህ ተቃዋሚዎች አንድ ቀን መንግሥት ይሆናሉ። ስለዚህ ዝግጅት መደረግ አለበት ብለናቸዋል” የሚል የደፈና መልስ ከያማሞቶ ተሰጠ።
ጋንት፤ የዩኤስ ኤይድ ረዳት ዳይሬክተር
የሴፍቲኔት ፕሮግራም እየተካሄደ መሆኑንና በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ እየተረጋጋች እንደሆነ፣ ከዚህም ጋር በማከል ኢኮኖሚው እያደገ እንደሆነ ልክ የኢህአዴግ ወኪል መስለው ተናገሩ። ሰብሳቢው ስሚዝ “ቶርቸር በየቦታው አለ እና ይህንን እንዴት ነው ለማስታረቅ ወይም ለማቆም የሚቻለው?” ሲሉ ማብራሪያ ጠየቁ። ሚ/ር ጋንት “አስቸጋሪ ነገር ነው። ቶርቸር እንዳለ እናውቃለን ግን ዋናው ሥራችን መልካም ነገሮችን ለማበረታታት ነው የምንሞክረው” የሚል ምላሽ ሰጡ።
በሚ/ር ጋንት ንግግር ላይ ተንተርሰው ተጨማሪ ጥያቄ ያቀረቡት ክሪስ ስሚዝ፣ ኢትዮጵያ ትምህርትን አስመልክቶ የሚሊኒየም ጎል ተሳክቷል ማለታቸውን ጠቅሰው “ጋንት ግን እኮ ጥራቱ በጣም የዘቀጠ እንደሆነ ነው ሪፖርቱ የሚያሳየው” ሲሉ ሞገቱዋቸው። የዩኤስ አይዲው ዳይሬክተር ጋንት “አዎ ችግር አለ ግን በርካታ መምህራን ተሰማርተዋል በትምህርቱ በኩል ዕድገት አለ” የሚል መልስ መመለሳቸው ለግንዛቤ ያህል የሚጠቀስ ሆኖ አግኝተነዋል።
ያማሞቶና ጋንት ያቀረቡትን ንግግርና ምስጋና ያደመጡ፣ በአካል ተገኝተው የተከታቱተሉ እንዳሉት በምክክሩ ላይ ኢህአዴግ ቢገኝም የሚጨምረው ምንም ነገር ሊኖር እንደማይችል አመልክተዋል።
ዳግም HR2003
የዛሬ አስር ዓመት፤ ኤች አር 2003 በምክር ቤት ደረጃ ከፍተኛ የሸንጎ (ኮንግሬስ) አባላትን ድጋፍ ካገኘ በኋላ የሕግ መወሰኛ ም/ቤት (ሴኔት) አጽድቆት በፕሬዚዳንቱ ተፈርሞ ፖሊሲ ሆኖ እንዲጸድቅ ባለመደረጉ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ጉዳዮች መከኑ። የህጉ መርቀቅና እንዲጸድቅ የተጀመረው እንቅስቃሴ ያስበረገገው ኢህአዴግ ጡረተኛ የሴኔት አባላት ከሚመሩት ዲኤልኤ ፓይፐር ከተባለ የጎትጓች (ሎቢ) ቡድን ጋር ከፍተኛ በጀት በጅቶ ታገለ። ባፈሰሰላቸው መጠን ጎትጓቾቹ ባልደረቦቻቸውን ጠመዘዙና ህጉ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምትከተለው አዲስ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት ህግ እንዳይሆን ተደረገ። ይህንኑ ህግ በማዘጋጀት ከሟቹ የምክርቤት አባል ዶናልድ ፔይን ጋር በወቅቱ ብዙ ደከሙት ክሪስ ስሚዝ የወቅቱን የቡሽ አስተዳደርን በንዝላልነት መድበው አሁን ይሀንኑ ህግ ተግባራዊ የሚደረግበትን አግባብ እንደሚገፉበት አመልክተዋል።
እንዴት እዚህ ተደረሰ?
የኢህአዴግን የአገዛዝ ዘመን ተቃዋሚዎችን አጃቢ አድረጎ የህግ ሽፋን በመስጠት የሚያራዝመው ዋና ተቋም ምርጫ ቦርድ፣ የፕሬስ ነጻነት፣ የመናገርና የመሰብሰብ ነጻነት፣ የህግ የበላይነት፣ ሕግን የማክበርና የማስከበር ሃላፊነት፤ ወዘተ በኢትዮጵያ ነጻ ከሆኑ ኢህአዴግ ከፊትለፊቱ ካለው ምርጫ የመዝለል አቅም እንደሌለው ይታመናል። ስለዚህም ለድርድር አያቀርባቸውም። ኢህአዴግ ከጅምሩ በህዝብ የማይታመነውና እውቅና የሚነፈገው ራሱን በነጻ አውጪ (ህወሓት) የሰየመ መንግስት ስለሆነ ነው። ነጻ አውጪ እየተባለ አገር መምራቱ አቅዶ፤ ተልሞና መድረሻውን አስልቶ የሚጓዝ ስለመሆኑ ያሳብቅበታል። ለዚህም ይመስላል ስርዓቱ በሙስና የሸተተ፣ በግፍ የገለማ፣ የሚመራውን ህዝብ የሚገል፣ የሚያስር፣ የሚያሰቃ፣ መንግስት ሆኖ  የሚሰርቅ፣ ብሔራዊ ክብርን የሚጠላ፣ ህብረትንና አንድነትን የሚጠየፍ፣ ጎሳና ጠባብ አመለካከት ላይ የተቀረጸ፣ በተራና በወረደ ተግባሩ ለመንግስትነት የማይመጥን መሆኑን የተረዱት አጋሮቹ አሁን ያመረሩበት ደረጃ ስለመዳረሳቸው ምልክቶች እንዳሉ አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል ተናግረዋል።
ይህ የምክክር ሸንጎ እንዴት ሊዘጋጅ ቻለ ለሚለው ጥያቄ በርካታ ጥረቶች መካሄዳቸውን በመግለጽ ዝርዝር ያላቀረቡት አቶ ኦባንግ ሐሙስ በተካሄደው ምክክር በመካከል ላይ ሚ/ር ስሚዝና ሌሎቹ ተወካዮች በምክርቤት ድምጽ መስጠት ስለነበረባቸው ምክክሩ ተቋርጦ እንደገና ሲጀመር ያልታዩበትን ምክንያት ተናግረዋል። ምክክሩ በተባለው ሰዓት ተጀምሮ ያልቃል የሚል እምነት ስለነበራቸው ሌላ ተደራራቢ የጉዞ መርሃግብር አመቻችተው እንደነበር አመልክተዋል።
“አሁን ስራ ላይ ነኝ” ያሉት አቶ ኦባንግ “እስራኤል አገር ለሁለት ከፍተኛ ጉዳዮች መጓዝ ነበረብኝ። አንዱ የወገኖቻችን ጉዳይ ነው። ሌላኛው ደግሞ የአገራችን ጉዳይ ነው። ከጉዞዬ በኋላ ማብራሪያ ለመስጠት እችላለሁ” በማለት ሁለተኛው ስብሰባ ሲካሄድ እርሳቸው ወደ እስራኤል ለሥራ እየተጓዙ እንደነበር አስታውቀዋል።