FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Saturday, November 30, 2013

ሰርቆ የሚያውቅ፣ በምልክት ያስራል የወላይትኛ ተረት (ከይሰት ቤእደይ መላት ጐዜስ)

ከዕለታት አንድ ቀን ሶስት ትላልቅ በሬዎች በጣም አባያ ሆነው በየጫካው እየደነበሩ እፅዋቱን እየረመረሙ አገር-ምድሩን እያመሱ አስቸገሩ፡፡ የዱር አራዊቱ ሁሉ በግዙፍነታቸውና በጉልበተኝነታቸው ፈሯቸው፡፡ የደኑ አራዊት አንድ ቀን ተሰበሰቡና 
“እነዚህን በሬዎች ምን ብናደርግ ነው በቀላሉ ልንበላቸው የምንችለው?” ይባባሉ ጀመር፡፡ ሆኖም ሁሉም ፈሩ፡፡ የበሬዎቹ ትላልቅ መሆን ከወኔያቸው በላይ ሆነ፡፡ ስለዚህም ምንም ሳያረጉዋቸው ቆዩ፡፡ 
አንድ ቀን አንድ ብልጥ ጅብ መጣና “ቆይ ግዴላችሁም፤ እኔ እነዚህን በሬዎች እነጣጥልላችኋለሁ” አለ፡፡ ከዚያም ወደ በሬዎቹ ሄደና እንዲህ አላቸው፡- 
“እባካችሁ ተራ በተራ ላናግራችሁ እፈልግ ነበር፡፡ ትፈቅዱልኛላችሁ?” 
በሬዎቹም፤ 
“እንደፈለክ ልታናግረን ትችላለህ” አሉት፡፡ 
አያ ጅቦም በመጀመሪያ ጥቁሩን በሬ ጠርቶ፤ 
“ከእናንተ መካከል የነጩ በሬ ነገር ያሳስበኛል” 
“ለምን ያሳስብሃል?” አለና ጠየቀ ጥቁሩ በሬ፡፡ 
“ጠላቶች ከሩቁ በነጩ ቆዳው ምክንያት ይለዩታል፡፡ ስለዚህም በቀላሉ ስለሚለዩዋችሁ ያጠቋችኋል፡፡ የሚሻለው ገለል ብታደርጉት ነው-ተመካከሩበት” አለው፡፡ 
በሬዎቹ ተመካከሩና ነጩ በሬ ለብቻው ራቅ ብሎ እንዲኖር አደረጉ፡፡ የደኑ አውሬዎች፤ ብቻውን ያገኙትን በሬ አድነው፣ አሳድደው በሉት፡፡ አያ ጅቦ ቀጠለና ጥቁሩን በሬ እንደገና ጠራው፡፡ 
“የዚህ የጓደኛህ የቀዩ በሬ ነገር በጣም አሳሳቢ ሆኖብኛል” አለው፡፡ 
“ለምን አሳሳቢ ሆነብህ?” አለው፡፡ 
“ምክንያቱም፤ ደም የመሰለ ቀይ በመሆኑ፤ ሰዎች ከሩቅ ይለዩታል፡፡ ስለሆነም ባንድ አፍታ የት እንዳላችሁ ይለዩና ይከታተሉዋችኋል! ራቅ አርገህ ብትልከው አንተ እንደዛፍ ወይም እንደዛፍ ጥላ የጠቆርክ በመሆንህ አይለዩህም” አለው፡፡ 
ጥቁሩ በሬም ሄዶ ለቀዩ በሬ ስለተባለው አደጋ አዋየው፡፡ ቀዩ በሬ ተስማማና ራቅ ወዳለ ቦታ ሄደ፡፡ 
ቀዩ በሬ ብቻውን ሲሆንላቸው የዱር አውሬዎቹ አሳደው ሰፈሩበት፡፡ 
በመጨረሻም ወንድም የሌለው ጥቁሩ በሬ በግላጭ ተገኘና የዱር አውሬዎች ሁሉ ተቀራመቱት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አያ ጅቦ “የአፍ-አጣፋጭ” የሚል ስም ወጣለት፡፡  
*   *   *
የባለተራ ደወል የሚለውን አለማሰብ የዋህነት ነው፡፡ አዳዲስ አካሄዳችንን አለማስተዋልም ጅልነት ነው! “እኔ እዚህ መሆኔ በቂ ነው” ከማለት ባሻገር፤ “እገሌ የት ደረሰ?” ማለት ያባት ነው፡፡ የኃይል ሚዛንን አውቆ ማን ምን እያደረገ ነው? ምን ዘዴ እየተጠቀመ ነው? ማለት ደግ ነው፡፡ “የከፋፍለህ ግዛውን መርህ የምንንቀውና የምንሳለቅበትን ያህል፤ ዕውነት ቢሆንስ? ማለት ከማኪያቬሊ ጀምሮ የኖረ ያለ፤ “ደባ” መሆኑን ማስተዋል ታላቅነት ነው፡፡ 
የሀገር፣ የህዝብ እና የተቋም ሚሥጥር ግራ ሊያጋባን አይገባም፡፡ የሚሥጥር ትርጉም ብዙዎችን ቢያወዛግብም፤ የግል - ሚሥጥርና የአገር ሚሥጥር ግን መለየት ይኖርበታል፡፡
ስልክ ወይም ኢሜይል ጠለፋ አዲስ ኃይላዊ ማረጋገጫ (Coerced confession) ነው ይባላል፡፡ አዲስ ሚሥጥር መያዣ ዘዴ ነው፡፡ ዱሮ፤ በጉልበት በማገት የምናደርገውን፤ ዛሬ በሽቦና በኤሌክትሪክ ኃይል ጠለፋ ላይ መፈፀም ማለት ነው፡፡ ይሄ እንግዲህ “ተመርማሪውን ከማስገደድ፣ ቢያስፈልግም በቶርቸት (በወፌ-ላላ)፤ ከማወጣጣት ዶክመንቶቹን ከመውረስ፣ የግል መረጃዎችን ከመውሰድ፣ ቤቱን ሰብሮ ከመግባት ይልቅ፤ ሌላ ዘዴ መተካት ማለት ነው፡፡ ይሄ በዘመናዊ መንገድ ሲታሰብ፣ የኢ-ሜይል መዛግብት መውረስ ማለት ነው፡፡ 
ይሄ ደሞ፤ የኤሌክትሮኒክ መገናኛ ዘዴዎችን የፈጠሩት ሰዎች ራሳቸው፤ የማያውቁት ዘዴ የለም ብለን እንመን እንደማለት ነው፡፡ 
“ፖስታህ ከተከፈተ አለቀልህ፡፡ ገበናህ ተቀደደ፡፡ ፈረሱ ከጋጣው ወጥቷል”
 “ዱሮ ሚሥጥር የቤተ ክህነት ነበር፡፡ ዛሬ ቴክኖሎጂ ወርሶታል፡፡ ነገር ከካህን ወደ ልዑል ካለፈ - ነገር ጠፋ” ይላል - ዘ ኒውዮርከር፡፡ ገዢ የማያቀው ሚሥጥር የለም ነው ቁም ነገሩ፡፡ 
ከግልጽነት ይልቅ ሚሥጥራዊነትን የሚፈልግ ወገን - ባሁኑ ዘመን ቀልጧል፤ የሚል እሳቤ ቢኖረን ይሻላል፡፡ “ሚሥጥር ከኮተኮታችሁ ሁሉ ነገር ተጀመረ፡፡ ጐበዝ! ሚሥጥራዊነት የሤራ መሣሪያ ናት (ጄሬሚ ቤንታም)” በድብቅነትና በሚሥጥራዊነት መኖር አይቻልም፡፡ ከህዝብ የምትደብቀው ሚሥጥር በተለይ፤ ውሎ አድሮ መሸማቀቂያህ ነው!
ድብቅነት ነገ ከነግ - ወዲያ ይገለጣል፡፡ ሚሥጥራዊነት ግን የጥብቅነቱን ያህል ይቆይ እንጂ የሚታወቅ አደጋ ይሆናል፡፡ ሚሥጥራዊነት ብዙ ሽፋን አለው:- የሉዓላዊነት ሽፋን፣ የመንግሥት ደህንነት ሽፋን፣ የተቋም ህልውና ሽፋን፣ ያለመከሰስ መብት ሽፋን…ምኑ ቅጡ! ዜጋ የግል - ሚሥጥሬ ነው ቢል ግን፤ በብዳቤ፣ በኢ-ሜይል፣ በሞባይል፣ በአካል ሊያስጠይቅህ ይችላል የሚባለው ሚሥጥር የመብቱን መገፈፍ አያመላክትም፡፡ 
“መንግሥት ዜጐቹን ላለመሰለል መጠንቀቅ ይገባዋል” ይላሉ ፀሐፍት፡፡ “እኛ ብቻ ነን መሪዎች” የሚሉ ህዝቡን እንዲህ ይላሉ:- “ለማመዛዘንና ለመፍረድ አትችሉም፡፡ ደንቆሮ ናችሁና፡፡ ያም ሆኖ፤ ደንቆሮ ሆናችሁ መቀጠል ይኖርባችኋል - ምነው ቢሉ ማመዛዘንና መፍረድ እንዳትችሉ ይፈለጋልና፡፡” ይላል /ቤንታም/፡፡
ፖስታ እየገለጡ ሚሥጥር ስለሚያዩ ፖስታ ቤቶች፣ ዲዝሬኤሊ እንዲህ ይላል፤ “ደብዳቤዬን ክፈቱ ግን መልስ መስጠት ቻሉ!”
ዋናው ጥያቄ ግን በግል - ሚሥጥር (Privacy)፣ በግልጽነት  (Publicity) መካከል ልዩነት እንዳለ ልብ - ማለት ያሻል የሚለው ነው፡፡ 
ሆኖም እንደ ኤድጋር አላን ፖ - አመለካከት፤ “ሁሉም ድብቅ ነገር (mystery) ነገ ተገላጭ ነው፡፡ ምንም ነገር ተሸሽጐ አይቀርም፡፡ ወንጀሎች መፈታት አለባቸው፡፡ ግርግዳዎች መፍረስ አለባቸው፡፡ መቃብሮች ይፈነቀላሉ፡፡ ፖስታዎችም ተቀደው ይታያሉ” ይላል፡፡
ሙሰኛን፣ ኢፍትሐዊን፣ ሃሳዊ - መሲህን፣ ደካማ - ፖለቲከኛን፣ አድርባይን፣ አሻጥረኛን፣ አስመሳይ ተራማጅን የሚያውቅና የሚከስ፤ በዚህም ሆነ በዚያ ዕውቀቱ ያለው ነው፡፡ “ሰርቆ የሚያውቅ፣ በምልክት ያሰራል” የሚለው የወላይትኛው ተረት ይሄው ነው፡፡   

Thursday, November 28, 2013

ፍትህ የጎደለው ስደት እስከ መቼ!

ከሀና ሰመረ (ኖርዌይ)
hannasemere@yahoo.com


የምንሰማውና የምናየው የኛው ከልክ ያለፈ አሳዛኝ ዜና አላስችል ቢለኝ እንደው ትንሽ የውስጤን ሀዘን እና ብሶቴን
ቢገልፅልኝ ብዬ ብዕሬን አነሳው::

እኔ የምላቹ እንደው የሰው ልጅ እንዲህ እንዴት ከፋ? አምላክ በራሱ አምሳል የፈጠረውን ሰውን የሚያህል ክቡር
ፍጡር ለማጥፋት እንዲህ መሯሯጥ ምን የሚሉት ነው? እኛ ኢትዮጵያኖች ለምን ይሆን እንዲህ በየቦታው
ስቃያችን የበዛው? እውነት ግን የምላችሁ ወገኖቼ አያት ቅድመ አያቶቻችን አገራችንን ከወራሪ ጠላት ጠብቀው
ያስከበሩ እና እንዳስከበሩ ሲነገር የቆየው የጀብዱነት ታሪክ በደመ ነፍስ በሚወዛወዘው በወያኔ ድርጅት ከስር
መሰረቱ ለማፍረስ የታለመ ነው:: ይህንን እኩይ ተግባር በቸልተኝነት መመልከት ከታሪክ አጥፊው ጎራ አብሮ
ከመሰለፍ ተለይቶ አይታይም:: ግን እስከመቼ ብለን የጊዜ ቀጠሮ ይዘን ነው አያቶቻችን ደምና አጥንት ከፍለው
ባስረከቡን ሀገር ላይ ነፃነታችንን ተነፍገን ተራ እየጠበቅን የስደትን መራራ ፅዋ የምንጎነጨው ግን እስከመቼ?
ይህንን ጥያቄዬን ልብ ያለው ለራሱ ይመልስ::

ኢህአዴጋውያንን ሳይሆን በመላው አለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ያሳዘነና ያስቆጣው በሳውዲ አረቢያ
የሚኖሩ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ላይ የሚደርሰውን በርካቶችን እስከ ሞት ፤ ሴት እህቶቻችንን እስከ መደፈር
፡ እንዲሁም ወንድሞቻችንን ለከፍተኛ ድብደባ ከዳረገውም በላይ የህወሀት አባላት በሳውዲ አረቢያ ልጅም
ዘመድም ስለሌላቸው ወገኖቻችንን ካሉበት ችግር ለማውጣት የተከፈለ አመርቂ እንቅስቃሴ የለም:: እንዲያውም
በተገላቢጦሽ አረቦቹ በመለስ ዜናዊ ለብዙ ዓመታት በሊዝ የሰጣቸውን መቶ ሺህ ሄክታር የኢትዮጵያውያኑ መሬት
ላይ ህይወታቸውን ላጠፉ ፤ ሰብዓዊ መብታቸውን ለገፈፉ ፡ እንዲሁም ደማቸውን ላፈሰሱት ለሳውዲ አረቢያ
ህዝብ ቀለብ ሩዝ እያመረቱ ነው::

ይህም አልበቃ ብሎ ኢትዮጵያኖች ፍትህን ፍለጋ
በተሰደዱበት ዓለም ሁሉ በሙሉ ነፃነት
የወገኖቻቸውን በደል እልህ በተሞላበት ተቃውሞ
ሲያሰሙ ፤ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ
5:00 ሰዓት በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ
በሚታወቀው አካባቢ ከአይቤክስ ሆቴል
ፊት ለፊት በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ
ደጃፍ ላይ የተቃውሞ ድምፃቸውን ሊያሰሙ
የተሰበሰቡትን በተወለዱበት እና በገዛ ሃገራቸው
የወገኖቻቸውን ስቃይ እንዳይቃወሙ
በፖሊስ የመባረርና ከፊሉም ለእስር ተዳርጓል::

ግን ማን ይሆን ስደትን ሐሴት አድርጎ ቀዬውን ጥሎ በባዕድ ሀገር የሚንከራተት? ፍትህ ቢጓደልበት፤የብልሹ
አስተዳደር ግፍና የጭቆና ቀንበር ከአቅሙ በላይ ቢሆንበት እንጂ፤ ለዚህ ሁሉ ችግሮች ተጠያቂው ለዜጎቹ
ህልውናና ክብር ግድ የለሽ የሆነው መንግስት ተብዬው ነው:: ለነገሩ ወያኔ ብዙ ትንንሽ አድርጎ ከፋፍሎ የወሰነውን
እኛ ካላፈራረስነው ችግራችንም ማብቂያ አይኖረውም የወያኔም አላማ ግብ ይመታለታል ስለዚህ ወገኖቼ “ህዝብ
መንግስትን ሳይሆን መንግስት ህዝብን” አገልጋይ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት እንዲሁም ለዚህ ያበቃንን
ስርዓት ለማስወገድ ድክመታችንን በጋራ መፍታት የትግሉ ቅድመ ሁኔታ መሆን አለበት::

ኧረ ማንን ይሆን እንክርዳዱን ከስንዴው አንጓሎ እንዲያስወግድልን የምንጠብቀው?

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

http://addisvoice.com/wp-content/uploads/2013/11/Hanni-file-21.pdf

Monday, November 25, 2013

ግድ የለሹ መንግስት ተብዬው!

ከሀና ሰመረ (ኖርዌይ)
hannasemere@yahoo.com


የምንሰማውና የምናየው የኛው ከልክ ያለፈ አሳዛኝ ዜና አላስችል ቢለኝ እንደው ትንሽ የውስጤን ሀዘን እና ብሶቴን ቢገልፅልኝ ብዬ ብዕሬን አነሳው::

እኔ የምላቹ እንደው የሰው ልጅ እንዲህ እንዴት ከፋ? አምላክ በራሱ አምሳል የፈጠረውን ሰውን የሚያህል ክቡር ፍጡር ለማጥፋት እንዲህ መሯሯጥ ምን የሚሉት ነው? እኛ ኢትዮጵያኖች ለምን ይሆን እንዲህ በየቦታው ስቃያችን የበዛው? እውነት ግን የምላችሁ ወገኖቼ አያት ቅድመ አያቶቻችን አገራችንን ከወራሪ ጠላት ጠብቀው ያስከበሩ እና እንዳስከበሩ ሲነገር የቆየው የጀብዱነት ታሪክ በደመ ነፍስ በሚወዛወዘው በወያኔ ድርጅት ከስር መሰረቱ ለማፍረስ የታለመ ነው:: ይህንን እኩይ ተግባር በቸልተኝነት መመልከት ከታሪክ አጥፊው ጎራ አብሮ ከመሰለፍ ተለይቶ አይታይም:: ግን እስከመቼ ብለን የጊዜ ቀጠሮ ይዘን ነው አያቶቻችን ደምና አጥንት ከፍለው ባስረከቡን ሀገር ላይ ነፃነታችንን ተነፍገን ተራ እየጠበቅን የስደትን መራራ ፅዋ የምንጎነጨው ግን እስከመቼ? ይህንን ጥያቄዬን ልብ ያለው ለራሱ ይመልስ::

ኢህአዴጋውያንን ሳይሆን በመላው አለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ያሳዘነና ያስቆጣው በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ላይ የሚደርሰውን በርካቶችን እስከ ሞት ፤ ሴት እህቶቻችንን እስከ መደፈር ፡ እንዲሁም ወንድሞቻችንን ለከፍተኛ ድብደባ ከዳረገውም በላይ የህወሀት አባላት በሳውዲ አረቢያ ልጅም ዘመድም ስለሌላቸው ወገኖቻችንን ካሉበት ችግር ለማውጣት የተከፈለ አመርቂ እንቅስቃሴ የለም:: እንዲያውም በተገላቢጦሽ አረቦቹ በመለስ ዜናዊ ለ60 ዓመት ሊዝ የሰጣቸውን መቶ ሺህ ሄክታር የኢትዮጵያውያኑ መሬት ላይ ህይወታቸውን ላጠፉ ፤ ሰብዓዊ መብታቸውን ለገፈፉ ፡ እንዲሁም ደማቸውን ላፈሰሱት ለሳውዲ አረቢያ ህዝብ ቀለብ ሩዝ እያመረቱ ነው::

ይህም አልበቃ ብሎ ኢትዮጵያኖች ፍትህን ፍለጋ በተሰደዱበት ዓለም ሁሉ በሙሉ ነፃነት የወገኖቻቸውን በደል እልህ በተሞላበት ተቃውሞ ሲያሰሙ ፤ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ከአይቤክስ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ የተቃውሞ ድምፃቸውን ሊያሰሙ የተሰበሰቡትን በተወለዱበት እና በገዛ ሃገራቸው የወገኖቻቸውን ስቃይ እንዳይቃወሙ በፖሊስ የመባረርና ከፊሉም ለእስር ተዳርጓል::

ግን ማን ይሆን ስደትን ሐሴት አድርጎ ቀዬውን ጥሎ በባዕድ ሀገር የሚንከራተት? ፍትህ ቢጓደልበት፤የብልሹ አስተዳደር ግፍና የጭቆና ቀንበር ከአቅሙ በላይ ቢሆንበት እንጂ፤ ለዚህ ሁሉ ችግሮች ተጠያቂው ለዜጎቹ ህልውናና ክብር ግድ የለሽ የሆነው መንግስት ተብዬው ነው:: ለነገሩ ወያኔ ብዙ ትንንሽ አድርጎ ከፋፍሎ የወሰነውን እኛ ካላፈራረስነው ችግራችንም ማብቂያ አይኖረውም የወያኔም አላማ ግብ ይመታለታል ስለዚህ ወገኖቼ “ህዝብ መንግስትን ሳይሆን መንግስት ህዝብን” አገልጋይ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት እንዲሁም ለዚህ ያበቃንን ስርዓት ለማስወገድ ድክመታችንን በጋራ መፍታት የትግሉ ቅድመ ሁኔታ መሆን አለበት::

ኧረ ማንን ይሆን እንክርዳዱን ከስንዴው አንጓሎ እንዲያስወግድልን የምንጠብቀው?


ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!



Sunday, November 24, 2013

ኦባንግ – ከዓለምአቀፍ ተቋማት ጋር እየሠራሁ ነው አሉ

የሳዑዲ ልዑል አንጋቾቻቸውን አወደሱ

obang-o-metho-hearing


በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ፈር የለቀቀ አስነዋሪ ግፍ ዓለምአቀፍ ይዘት እንዲኖረው ለማድረግ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ጋር እየሠሩ መሆናቸውን አቶ ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ተናገሩ፡፡ የሳዑዲ ልዑል ሰብዓዊነት የረገፈበትንና በግፍ የተሞላ የወሮበላ ተግባር የሚፈጸምበትን አሰቃቂ ተግባር የሚከናውኑትን አንጋቾች አሞካሹ፡፡
ያለ አንዳች ልዩነት ኢትዮጵያውያን በኅብረት ድምጻቸውን በማሰማት እየተቃወሙት ያለውን ኢሰብዓዊ ተግባር አስመልክቶ በተለያዩ መንገዶች ይፋ ከሆኑት በተጨማሪ ድብቅ መረጃዎች እየተሰበሰቡ መሆናቸውን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አስታውቀዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ የጋራ ንቅናቄው ከዓለምአቀፍ የመብት ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሰራ ስላለው ዝርዝር ጉዳይ ግን ከሁኔታው ምስጢራዊነት አኳያ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
“አልዘገዩም” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም “አኢጋን ችግር በተከሰተ ቁጥር የሚቋቋምና የሚፈርስ የዕቁብ ይዘት ያለው ድርጅት አይደለም፡፡ ወይም እሣት ሲነሳ ድምጽ እያሰማ እንደሚከንፍ የእሣት አደጋ መኪና የሚመሰል ድርጅት አይደለም” በማለት የጋራ ንቅናቄውን የተጠና አካሄድ በመጠቆም የመለሱት አቶ ኦባንግ ይህ ችግር እንደሚከሰት አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡
ችግሩ አስቀድሞ እንደሚከሰት ቢታወቅም ምላሽ የሚሰጥ ብቃት ያለው አካል ባለመኖሩ አንገት የሚያስደፋና ኃፍረት የሚላብስ፤ “አገር አለኝ ወይ?” የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ በኢትዮጵያ ታሪክ ተሰምቶና ታይቶ የማይታወቅ ኃፍረት ሊደርስብን ችሏል፡፡ “ይሁን እንጂ” አሉ ኦባንግ “ይህ መራር ዜና ከተሰማበት ሰዓት ጀምሮ የጋራ ንቅናቄው የበኩሉን” ሲያደርግ መቆየቱን አመልክተዋል፡፡
“ከተለያዩ ዓለምአቀፋዊ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ አግባብ ካላቸው መንግሥታዊ አካላትና በተለያየ ደረጃ ላይ ከሚገኙ የሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረናል” በማለት አቶ ኦባንግ ተናግረዋል፡፡ ለዓብነት ያህልም የሳዑዲ ም/ጠ/ሚ/ር እና የመከላከያ ሚ/ር፣ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር፣ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚ/ር፣ የፍትሕ ሚ/ር እና ሌሎች ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን የመንግሥት መ/ቤቶችን ጨምሮ በአውሮጳና በሰሜን አሜሪካ የሚገኙትን የሳዑዲ ኤምባሲዎችን እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽነርን፣ የአፍሪካ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ACHPR)፣ ወዘተ ማነጋገራቸውንና በየደረጃውም ምላሽ ማግኘታቸውን አመልክተዋል፡፡
በመላው የመካከለኛው ምስራቅ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ዕረፍት የሚሰጥ እንዳልሆነ የጠቆሙት “ጥቁሩ ሰው” ሳዑዲ ካላትና ከምትከተለው “የበርህን ዝጋ ፖሊሲ” አንጻር በአካል በቦታው ላይ ከመገኘት ይልቅ አቅም ካላቸው ዓለምአቀፋዊ አካላት ጋር በአፋጣኝና በቅርበት መሥራቱ ድርጅታቸው የወሰደው አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሎጂስቲክሱ ጉዳይ መስመር ሲይዝም የጋራ ንቅናቄው ከዚህ በፊት በየአገራቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጉዳይ ሲያስፈጽምበት የነበረውንና በውጤታማነቱ የሚታወቀውን አማራጭ እንደሚተገብር ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ኢህአዴግ አገርን እንደሚያስተዳድር ድርጅት በዜጎቹ ላይ እየደረሰ ያለውን አስነዋሪ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ አለመመከቱ ተቃውሞ አስነስቷል፡፡ ይህንኑ አስመልክቶ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ወገኖቻችንን ድንበር በማሻገርና ኤጀንሲ ከፍተው ወደ አረብ አገራት ሲልኩ የነበሩት ሁሉ ሕግ ፊት ቀርበው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ የተለያዩ ተግባራት” እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
alamudi-ሼክ መሐመድ አላሙዲ የሠራተኛ ኃይል ወደ ሳዑዲ እንዲላክ ከኢህአዴግ ጋር በይፋ ስምምነት ማድረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡ ኢንቨስትመንትን በተመለከተ ከሚፈልጉበት ክልል መሬት ለመውሰድ፣ ከሚፈልጉበት ባንክ ኮሪደር ገንዘብ ለመበደር ገደብ የሌላቸውና በሞቀበት ሁሉ ባለመጥፋት በጀት መድበው በሚያስተዳድሯቸው ሚዲያዎች እንዲሁም አንደበታቸውን በሙስና ላሰሯቸው ባለሥልጣናት “ኢትዮጵያዊ ነኝ” እያሉ በተገኙበት ቦታ ሁሉ ለሚዲያ ፍጆታ የሚደሰኩሩትና ግጥም የሚያስደረድሩት ሼክ መሐመድ አላሙዲ፣ “ወገኔ” የሚሉት ሕዝብ በአባታቸው አገር ወሮበሎች ሲያልቅና ሲጨፈጨፍ ዝም ማለታቸው ኢንቨስትመንቶቻቸውን ጥያቄ ውስጥ ከትቷል፡፡
አንዳንዶች እንደሚሉት ይህ አሰቃቂ ድርጊት መስመር ለቅቆ ከመውጣቱ በፊት የሳዑዲ አረቢያ ዜጎችን ከርስ እንዲሞላ በኢትዮጵያ የተቋቋመው ሳዑዲ ስታር ኩባንያ በገንዘብ እጥረት ሊዘጋ እንደሚችል መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡ በወቅቱ ሪፖርተር ባወጣው ዘገባ ሳዑዲ ስታር በኪሣራ ወደ መዘጋት መድረሱ የኩባንያው “ባለቤት የሆኑትን ሼክ ሙሐመድ አል አሙዲንና የሳዑዲ ዓረቢያን ስም የሚያጎድፍ ከመሆኑም ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ እስኪታክት የተወራለት ይህ ፕሮጀክት መና መቅረቱ ሁለቱን አካላት በሕዝቡ ዘንድ ለከፍተኛ ትችትና ወቀሳ እንደሚያጋልጣቸውም” ጠቁሞ ነበር፡፡
mohammed bin nayef
ልዑል ሞሐመድ ቢን ናይፍ
በአሁኑ ጊዜ “ሕገወጥ ናችሁ” በሚል ሰብዓዊነት የጎደው እርምጃ እየተወሰደባቸው ያለው የበርካታ አገራት ዜጎች በተለይም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጸመውን ሰቅጣጭ ተግባር ሕገወጦችን የማባረር “ዘመቻ” በማለት ያቃለሉት የሳዑዲው አገር ውስጥ ሚ/ር ልዑል ሞሐመድ ቢን ናይፍ ወንጀለኛ ሬንጀር ለባሾችን፣ ፖሊሶችንና ወሮበሎቹን ሸባቦች አደፋፍረዋል፡፡ “ዘመቻው ይቀጥላል … በተወሰነ ጊዜ የተገደበ አይደለም” በማለት “እስክንጨርስ እንጨርሳችኋለን” የሚመስል የማፊያ መሪ መሰል መልዕክት ለአንጋቾቻቸው አስተላልፈዋል፡፡
አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን በሕጋዊነት የሚኖሩትም ጭምር በሳዑዲ ያለው ሁኔታ አሳሳቢነት ወደፊት ችግር ውስጥ ሊከትታቸው እንደሚችል በመገመት ወደ አገራቸው መመለስ ይፈልጋሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት ለከፍተኛ ሰቆቃ የተጋለጡት ኢትዮጵያውያን “ቤት አለን ቤታችን መልሱ” እያሉ የሰቆቃና የድረሱልን ጥሪ በሚያስተላልፉበት ወቅት ሰብዓዊነት የጎደላቸው የኢህአዴግ መሪዎች ይህ ነው የሚባል አፋጣኝ ምላሽ መስጠት አለመቻላቸው “በእርግጥ ኢትዮጵያውያን አገር አላቸው?” ብሎ የሚያስጠይቅ እንደሆነ በርካታዎች የሚጋሩት ነው፡፡
አቶ ኦባንግ በበኩላቸውም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአንድ ሳምንት ሥራውን አቋርጦ እንኳን ቢሆን ስደተኞቹን ባፋጣኝ የማመላለስ ተግባር መፈጸም ይገባው ነበር በማለት ቁጭታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ህይወታቸው እየተቀጠፈ “3ሺህ ዛሬ ገቡ … ድምሩ 10ሺህ ሆኗል …” የሚል የሞላ ጎደለ ቁማር ዓይነት ጨዋታ በትዊተር መጫወት የቴድሮስ አድሃኖምን ዘመነኛነት ሳይሆን ለሰውልጅ ህይወት ያላቸውን ደንታቢስነት የሚያሳይ መሆኑን ሁኔታው ያስቆጣቸው አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አቶ ኦባንግም “ቤቴ መልሱኝ” ብሎ ለሚለምን አንድ ዜጋ የተከፈለው ተከፍሎ ትራንፖርት በማቅረብ ክቡር ህይወትን በአስቸኳይ ለመታደግ አለመቻል ለትውልድ የሚተላለፍ የታሪክ ጠባሳ መሆኑን በአጽዕኖት ተናግረዋል፡፡

Friday, November 22, 2013

ሰማያዊ ፓርቲ፣ የዜጎችን ሰቆቃ እና በደል ችላ ማለት ከግፈኞች ጋር እንደመተባበበር ይቆጠራል!!

ሰማያዊ ፓርቲ በሳውዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎቻችን ላይ የሳውዲ መንግስት እያደረሰ ያለውን እስራት፣ ስቃይ እና ግድያ በመቃወም እና ህይወታቸው ላለፈ፣ ለተደበደቡ እንዲሁም የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ህዝቡ ሃዘኑን እንዲገልጽ በመጪው እሁድ በሚደረገው ታላቁ ሩጫ ላይ የሚሮጡ ተሳታፊዎች ጥቁር ሪቫን አድርገው እንዲሮጡ ጥሪ ማስተላለፉ የሚታወቅ ነው፡፡

ይሁን እንጂ የታላቁ ሩጫ አስተባባሪዎች ይህንን ጥሪ እንደሚቃወሙት እና በፕሮግራሙም ላይ ጥቁር ሪቫን ያሰረ ተሳታፊን እንደተሳታፊ እንደማይቆጥሩ መናገራቸው ፓርቲያችንን እጅግ አሳዝኖታል፡፡ ፓርቲያችን ይህንን ጥሪ ሲያስተላልፍ አላማው ፍጹም ፖለቲካዊ አንድምታ የሌለው ሲሆን ጥያቄውም በዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት እና ግድያ እንዲቆም እና ፍትሃዊ እርምጃም እንዲወሰድ ለመጠየቅ ብቻ እና ብቻ እንጂ ሌላ አላማ እንደሌለው እየታወቀ የታላቁ ሩጫ አስተባባሪዎች ግን ጉዳዩ ከፖለቲካ ጋር ለማያያዝ መሞከራቸው የሚያስተዛዝብ እና ህዝባዊ ወገንተኝነታቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው፡፡
ስፖርት ሰላማዊ ነገር የሚሰበክበት እንዲሁም እኩይ ተግባራት የሚወገዙበት መድረክ ነው፡፡ በአለማችን ላይ በተለያዩ ጊዜያት በተከሰቱ አሰቃቂ ሰው ሰራሽ አደጋዎች በተለያዩ ስፖርታዊ ዝግጅቶች ላይ ሲወገዙ እንዲሁም ለሰለባዎች ሃዘን የመግለጽ ስነ ስርዓትና የህሊና ጸሎት ሲደረግ መመልከት የተለመደ ነው፡፡ ታዲያ በጠራራ ፀሀይ በአደባባይ እናት ልጆችዋ ፊት እንዲሁም ሴት ልጅ ቤተሰቦችዋ ፊት ስትደፈር ከማየት የዘለለ ምን እኩይ ተግባርስ ሊኖር ነው? ታዲያ ስፖርት ይህንን ካላወገዘ ምንን ሊያወግዝ ነው?
በመጨረሻም የታላቁ ሩጫ አስተባባሪዎች የፓርቲውን ጥሪ መቃወማቸው ፓርቲያችንን ያሳዘነ እና ያስቆጣ መሆኑን እየገለጽን አሁንም ፓርቲያችን በድጋሜ በዝግጅቱ ላይ ተሳታፊዎች ጥቁር ሪቫን አድርገው እንዲሮጡ እየጠየቀ ጥቁር ሪቫኖችን ማግኘት ለማትችሉ በሰማያዊ ፓርቲ ጽህፈት ቤት ተገኝታችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
ክብር ለዜጎቻችን ይሁን!!

Thursday, November 21, 2013

ወደ ተግባር (ከአንተነህ መርዕድ እምሩ)

ከአንተነህ መርዕድ እምሩ

ኢትዮጵያውያን እንደ አሁኑ ተገፍተን ገደል ጠርዝ የቆምንበት ጊዜ ያለ አይመስለኝም። እስከ አሁን ትንንሽ መሸሻ ስለነበረን ፍርሃታችንን እንኳን ከሰው ከራሳችንም ደብቀን ስናፈገፍግ ኖረናል። ፈሪነታችንን ባባቶቻችን ጀግንነት፣ ውርደታችንን ባባቶቻችን ኩራት እያለበስነው መጓዝ የማያዛልቅ ለመሆኑ ከሰሞኑ የበለጠ ምስክር ምን አለና።
ያጋጠመን ብሄራዊ ውርደት ከፊሎቻችንን ከእንቅልፋችን ገና ሲያባንነን ብዙዎቻችንን አጥንታችን ድረስ ገብቶ ተሰምቶናል። አባቶቻችን “ሞት ሲዘገይ የቀረ ይመስላል” እንዳሉት ባንዳንዶች ላይ የደረሰው ውድቀት እኛን ስላልነካን የሚቀር መስሎን ነበር። በገዥዎቻችን በየለቱ በምትወረወረዋ ከፋፋይ የቤት ስራ ተጠምደን ግዙፉ ህልውናችን አዳጋ ላይ መሆኑን እንኳ ማየት ተስኖን ነበር።Police in Ethiopia have arrested dozens of people outside the Saudi embassy
የአገርን አንድነት የሚያስጠብቅ እድሜ ልኩን ቀበሮ ጉድጓድ የኖረ ሰራዊት ሲበተን፣ የጥርሱ ወርቅ በመዶሻ ሲወልቅ፣ መሳርያውን አስረክቦ ቤተሰቡ ዘንድ መድረሻ ትራንስፖርት ሲለምን ምን አድረረግን?
በአገሪቷ አንጡራ ሃብት የተማሩ ምሁራን ከብቸኛው ዩኒበርስቲ አርባዎቹ ሲመነጠሩ፤
አማራው እንደዋና ጠላት ተቆጥሮ ገደል ሲጣል፣ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው የጮሁት ፕሮፌሰር አስራት እስር ቤት ሲበሰብሱ፣ ብሎም በግፍ እንዲሞቱ ሲደረግ፤
ኦሮሞው የተለያየ ስም እየተሰጠው ሲገደል፣ እስር ቤቱን ሲያጣብብ፤
አኝዋኩ ከገዛ መሬቱ ተነቅሎ ለሳውዲና ለህንድ ሃብታሞች እንዲለቅ ለማድረግ እንዳውሬ ሲታደን፤
መምህሩ ስርዓተ ትምህርቱ እንዲሻሻልና መብቱን በመጠየቁ ማህበሩ ሲበተን መሪዎቹ ሲታሰሩና አሰፋ ማሩ በጠራራ ፀሃይ ሲገደል፤
ነጋዴው ከሙያው ተፈናቅሎ በወያኔ ኩባንያዎች በሞኖፖል ሲታፈን፤
ህዝቡ በነጻ የመረጣቸው ወኪሎቹ ሲታሰሩና የምርጫ ኮሮጆ ሲገለበጥ፤
በሰላም ተቃውመው የወጡት የአጋዚ ኢላማ ሲሆኑ፤
ጋዜጠኞች እውነትን በመዘገባቸው ሲገደሉ፣ ሲታሰሩ፣ ሲታገዱና ሲሰደዱ፤
የኦርቶዶክስ አማኞች ሆኑ ገዳማት ሲደፈሩ ፤
ሁለት ዓመት ሊሞላው ያለ የእስልምና ተከታዮች እንቅስቃሴ ሲቀጠቀጥ፤
ተቃዋሚዎች መሪዎችቸው ባሸባሪነት ክስ ወህኒ ወርደው ሲማቅቁና ያሉትም ከእስር ባልተናነሰ እንዲኖሩ ሲገደዱ፤
የት ነበርን?? ይህ ሁሉ ሲፈጸም የት ነበርን?? እያልን መጠየቁ ጅል የሚያስመስል ቢሆንም፤ ምን ያህል እንደተኛንና ለዚህ ሁሉ ውድቀት ከአገሪቱ ጠላቶች ያላነሰ ስህተት መፈጽማችንን ያስገነዝበናልና። ዛሬ በእህቶቻችን ጩኸት ምክንያት እንባ ባረጠበው ዐይናችን ትናንትን አሻግረን ማየት ግድ ይለናል። የጠላቱን ምንነት ብቻ የሚያውቅና የራሱን ድክመትና ጥንካሬ ያልተገነዘበ ለድል አይበቃምና።
ይህ ሁሉ ተራ በተራ በስልት ሲፈጸም አንድ ሆነን መነሳት አቅቶን ዛሬ ጽዋው ሞልቶ መፍሰስ ሲጀምር የነቃን ይመስላል።
ዛሬም መንቃታችን አልዘገየም። ንቃታችን በቅጡ ሊያዝ ግን ይገባዋል። የብሄራዊ ውድቀታችን ጥልቀቱ ጎልቶ የወጣው በሳውዲ ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው ግፍና ይባስ ብሎ የወያኔ ኢህአዴግ መንግስት ያሳየው እብሪተኝነት ነው። ወያኔ ባስቀመጠልን ትንንሽነት ተወስነን ስንባላና ስንነታረክ ብዙ ወርቅማ ጊዜ አሳልፈናል። የሚቆጨው ግን ካሁን በኋላ የምናሳልፈው ከንቱ ጊዜ ካለ ነው።
በሳውዲ አሸዋ ላይ የፈሰሰው የወገኖቻችን ደም የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የትግሬ፣ የሶማሌ፣ የክርስቲያን፣ የእስላም፣ የኦነግ፣ የግንቦት ሰባት፣ የኢህአፓ ወዘተ..ብለን የምንለየው አይደለም። ሬሳቸው የተጎተተው፣ የተደፈሩት፣ የታጎሩት ከውሻ ያነሱ ሆነው የታዩት በኢትዮጵያዊነታቸው ነው። ዛሬ በሲቃ “አድኑን” እያሉ የሚጮሁት ወገኖቻችን “ኢትዮጵያውያን ድረሱልን” እያሉ ነው። “የኢትዮጵያ ህዝብ እንጂ መንግስት የለንም” ብለዋል በድምጻቸው።
ለሳውዲዎች ስጋና ፍራፍሬ፣ አበባና ማዕድናት፣ ገረድና እቁባት የሚሆኑ ህጻናት እየመለመሉ በማቅረብ በሃብት የደለቡ የወያኔ ባለስልጣናት ይደርሱልናል የሚል ብዥታ የላቸውም። ህገወጦች ላይ እርምጃ የመውሰድ መብት አላቸው የሚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ወንድም እህቶቻችን ላይ የሚፈጸመው ግፍ ይቁም ያሉ የሰማያዊ ፓርቲ ሰዎችን ለምን ሳውዲዎችን አወገዛችሁ ብሎ የሚቀጠቅጥ መንግስት የኛ ነው ብለው አይቀበሉትም።
አድኑን ብለው የጠየቁት እኛን ነው።
ማዳን ያለብን ዛሬ ባደባባይ የሚጮሁትን ወገኖቻችንን ብቻ አይደለም። ማዳን ያለብን አገራችንንና እራሳችንን ካለንበት ውርደት ነው።
መታገል ያለብን ለዚህ ያበቃንን ስርዓት ብቻ ሳይሆን፣ ይህንን ጨቋኝ ስርዓት በጸጋ ለመሸከም ያበቃንን ድክመታችንንም ነው። ያ ደግሞ ያንድ ሰሞን ሰላማዊ ሰልፍና ግርግር የሚመልሰው አይደለም። ደጋግሞ ከሚያጠቃን ስሜታዊነት መላቀቁ የትግሉ ቅድመ ሁኔታ መሆን አለበት።
ወያኔዎች የለመዱንና አሁንም ተስፋ የሚያደርጉት ያንድ ሰሞን ጫጫታችን እንደጉም ተኖ ወደነበርንብት የየግል ቁዘውማ እንድንገባና እነሱ ባቀዱልን ክፍፍል ስንፋጅ የዘረፋና ዘረኛ አገዛዛቸውን በሰፊው ለበቀጠል ነው። አቦ ፀሃይ የሞቀውን እውነት በመደጋገም ላሰለቻችሁ አልፈልግም። “ወሬ ቢበዛ በአህያ አይጫንም” ተብሏልና ምን እናድርግ ወደሚለው እንሻገር።
በዚች አገር ለውጥ ለማምጣትና ካለንበት ብሄራዊ ውድቀት ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመውጣት የተወሰነ ቡድን፣ ድርጅት ሆነ ግለሰብ ሃላፊነት አይደለም። ሁላችንም የራሳችንን ሃቅምና ችሎታ እየመረመርን በየት ብሰለፍ የበለጠ አስተዋጾ አደርጋለሁ የሚለውን ካወቅን በኋላ የማንንም ጎትጓችነት ሳንጠብቅ መንቀሳቀስ ነው። ሁሉም ለዚች አገር ማድረግ የሚችለው ትንሽ ነገር አለው። ያም ትንሽ ነገር ሲጠራቀም ነው ትልቅ ብሄራዊ ሃቅም የሚሆነው። እስቲ በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንጀምር።
ምሁራን፡ አገሪቷ በሌላት አቅም አስተምራን በአገር ውስጥና በዓለም ተበትነን እንገኛለን። ለዚይች ድሃና ኋላ ቀር ለምንላት አገር ምን ያህል እንደሰራንላት ራሳችንን እንጠይቅ። እስካሁን ለውጥ ለማምጣት እየተማገዱ ያሉትንና ከባዱን መስዋዕት የከፈሉትን ዋጋቸውን ሳንረሳ ሌሎቻችን አንድም ምን ማድረግ እንደምንችል ባለመገንዘብ ሌላም በመማራችን ያገኘነው መልካም እድል እንዳይደናቀፍና እንዳይጓደል እያየን እንዳላየን ተኝተን ቆይተናል። ምኝታው ይብቃን። የያዝነው ሳይጓደል ጭምር ብዙ አስተዋጾ ማድረግ ስለሚቻለን ከልብ የበኩላችንን እናድርግ። በዩኒቨርስቲ ምኩራቦች፣ በትላልቅ ዓለም አቀፍና አገር አቀፍ ድርጅቶች፣ በልዩ ልዩ ዘርፍ ተደላድለን ሌሎችን በሽሙጥ ብንወርፍ ወይም እንደሰጎኗ ራሳችንን ብንቀብር ምን ጥቅም አለው። ቢያንስ ቢያንስ ምናችሁም ሳይነካ ህዝቡን በማሳወቅ ለመስራት እንዳሁን የተመቸ የቴክኖሎጂ ጊዜ የለም። ያወቀ ህዝብ ሃያል ይሆናል። በዚህ ዙርያ ተሳትፎውን ቀድማችሁ የጀመራችሁም ለማን እንደምትጽፉ አስተውሉ። ለአሜሪካኖች፣ ለፈረንሳዮች አይደለም ለኢትዮጵያውያን መሆን አለበት። በቀላል ኢትዮጵያዊ ቋንቋ ጻፉ ካልሆነም ስራችሁ ተተርጉሞ እንዲደርሰው አድርጉ። ለተማረውና የነገር መላላጫ ሲያወጣ ለሚውለው ክፍል ከሆነ ስራችሁ ኢላማውን ስቷል።
ፖለቲከኞች፡ ጊዜአችሁንና ሃቅማችሁን የራሳችሁን ዓላማ በማስረዳትና ደጋፊ በማጠናከር እንጂ ሌላውን ጥላሸት በመቀባት አትዋትቱ። እስካሁን ጠንክሮ ያለመውጣታችሁ ትልቁ ችግር የወያኔ ዱላ ወይንም የህዝቡ ቸልተኝነት ብቻ አይደለም። የዓላማ ጥራትና ጽናት ጉድለት ነው። ዓላማችሁ ጠርቶ ከታወቀ፣ በዚያም ጸንታችሁ የምትታገሉ ከሆነ ከምትፈልጉት በላይ ኃይል ይከተላችኋል። እንደሰርገኛ ላንድ ሰሞን ግርግርና ሞቅ ሞቅ አድርጓችሁ የሚሸሸው ከናንተ የሚያገኘውን ስላጣ ነው። አርቲፊሻል አበባ ላይ ማር አገኛለሁ ብሎ የሚሰፍር ንብ የለም።
በቀለምና በጊዜያዊ መአዛ ሳይሆን በይዘታችሁ ማር የሚቆረጥባችሁ ሆናችሁ እስካልተገኛችሁ ድረስ መጠውለግ የራሳችሁ ውጤት ነው።
ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፡ እስካሁን በየቦታው የሚደረገውን ሰባዊ መብት ጥሰት በማጋለጥ የተጫወታችሁት ሚና ቀላል ባይሆንም ከመሰል ግርጅቶችና ግለሰቦች ስራችሁን በማቀናጀት ሚዛናዊ የሆነውን ሪፖርት ለህዝቡና ለሚመለከተው ክፍል ሁሉ በማቅረን ትጉ። መረጃዎችም የሚሰባሰቡበት የዳታ ማዕከል ፍጠሩ። ተመራማሪዎች፣ የታሪክ ሰዎች፣ ፍርድ ሰጪ አካላት፣ አጠቃላይ ህዝቡ በቀላሉ የሚያገኛቸው ይሁኑ።
የሃይማኖት አባቶች፡ የሃይማኖት መሰረታዊ ተልዕኮ ለፍትህ መቆም ነው። ፍትህን የማይሰብክና ለፍትህ የማይቆም እምነት ፈጣሪ ከሰጠው ተልዕኮ ውጭ ነው። ፖለቲካን አይደለም ፍትህን ስበኩ። በደልን ማንም ይፈጽመውማን ማውገዝ አለባችሁ። ከዚያ የዘለለ ከናንተ አይጠበቅም። የታላላቅ ሃይማኖቶች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ ፍትህ ሳይኖራት ሃይማኖቷ ምን ፋይዳ ይኖረዋል።
ጋዜጠኞች፡ ሃሳብን በነፃነት መግለጽ ባልተለመደባት አገራችን ባለፉት ጥቂት ዓመታት የህዝብ ድምጽ ለመሆን የታገሉት በርካታ ቢሆኑም፣ ብዙዎቹ በእስር ቢማቅቁም፣ ከፊሎቹ ቢሰደዱም ትግሉ አልሞተም። መስዋዕቱ የከፋ ቢሆንም አሁን ካለንበት በበለጠ እንድንታገል እንጂ እንድንዘናጋ የሚያደርግ ሁኔታ ስለሌለ ትግላችን በእጥፍ እንዲጎለብት እንነሳ። በተለያየ መንገድ ትክክለኛ መረጃ ለህዝቡ እንዲደርስ መሻትና መታገል የጊዜው አብይ ጥያቄ ነው። የዘመኑ ቴክኖሎጂ በፈቀደልን ሁሉ መንገድ መጠቀምና ሃቅምን አስተባብሮ መስራት ውጤቱ ትልቅ መሆኑን አይተናልና እንቀጥልበት።
ዲያስፖራ፡ ይህንን ክፍል ለይቼ ያነሳሁን ያለምክንያት አይደለም። ለትግሉ ወሳኝነት ባይኖረውም ተጽዕኖው ከባድ ስለሆነ ነው። በግድም በውድም አገሩል ለቆ የሄደው ኢትዮጵያዊ ቁጥር ቀላል አይደለም። የማይገኝበት የዓለም ክፍልም የለም። የኤኮኖሚ ሃቅሙና ዕውቀቱ ደግሞ በሚገባ ከተያዘ አገሪቱን ካለችበት የድህነት አዘቅት ከሚያወጧት ሰፊ ሃብቶች ትልቁ በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ነው። እስከ አሁን የገንዘብ አቅሙን ወያኔ ለድሜው ማራዘምያ በስልት ተጠቅሞበታል። ይህ ሊያበቃ ይገባል። ዲያስፖራ በነጻነት ከወያኔ ተፅዕኖ ውጭ ስለሚኖር ምንም ጉዳት ሳያገኘው ህዝቡን ለነፃነት የሚያበቃ ትግል ውስጥ መሳተፍ ይችላል። በድህነት የሚማቅቁ ቤተሰቦችን መቶና ሁለት መቶ ዶላር በየጊዜ በመወርወር ከችግር ማላቀቅ አይቻልም። ስርዓቱን በመለወጥ በነፃነት ሰርተው የሚኖሩባት አገር መፍጠሩ ዘላቂነት አለው። ሳይዘገይ ፈጥኖ መድረሻው አሁን ነው።
ሌላው ኢትዮጵያዊ፡ ቀሪው ኢትዮጵያዊ ዳር ቆሞ ከሌሎች ተአምር ከመጠበቅ ራሱን ባመነበት አቅጣጫ አሰልፎ መንቀሳቀስ ያስፈልገዋል። ከላይ የተጠቀሱትን የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሰባዊመብት ተሟጋች ተቋማት፣ የሃይማኖት ድርጅቶች፣ ማስሚድያዎች፣ የሲቢክ ተቋማት እንዲጠናከሩ አባል ሆኖ እውቀት፣ ጉልበትና ገንዘብን ማበርከት የመከራውን ጊዜ ያሳጥራል። በሳውዲና በሌሎችም የአረብ አገሮች የሞቱና የሚሰቃዩ ኢትዮጵያውያን ድምፅ ገንፍለን እንድንወጣ ያደረገን ሁሉ ተመልሰን ወደወትሮው ምሽጋችን አንግባ። ተጋድሎአችን በተግባር ነፃነት እስኪገኝ መቀጠል አለበት። ጽዋው ሞልቶ ፈስሷል። ብሄራዊ ወርደታችን ገደል ጫፍ አድርሶናል። ከዚህ በላይ መገፋት የሚያመጣው ውጤት ማንነታችንን ማጣት ነው የሚሆነው።
ሰልፉ፣ ጩኸቱ፣ ለቅሶው ይቁም ባይባልም ተጨባጭ ወደሆነ ተግባር ይቀየር።
ኢትዮጵያ ወደ እውነተኛ ክብሯ ትመለስ!
ዜጎቿ ከብሄራዊ ውርደት ይዳኑ!
በደልን የመታገል እንጂ የመሸከም ጽናት አይኑረን!
ፍቅርና መተባበር በሁሉም ኢትዮጵያዊ ይስፈን!!
ጸሃፊውን በ amerid2000@gmail.com ማግኘት ይችላሉ

በ1997ቱ የኢትዮጵያ ምርጫ ታዛቢ የነበሩት አና ጐሜዝ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው


Photo: © Europen Parliament/P.Naj-Olearipietro.naj-oleari@europarl.europa.eu


በ1997 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫና ምርጫውን ተከትሎ ተከስቶ በነበረው የፖለቲካ ውዝግብ አካል የነበሩት የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ አና ጐሜዝ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው፡፡
በኢትዮጵያ በ1997 ዓ.ም. ተካሂዶ የነበረውን ምርጫ በአውሮፓ ኅብረት ተወክለው ምርጫውን በዋና ታዛቢነት የመሩትና የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ አባል የሆኑት አና ጐሜዝ፣ ምርጫውን አስመልክቶ ባወጡት ሪፖርት ኢሕአዴግ ከሚመራው መንግሥት ጋር ጥልቅ የሆነ ግጭት ውስጥ ገብተው ነበር፡፡
አና ጐሜዝ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በምርጫው ሳቢያ ውዝግብ ከገቡበት ጊዜ አንስቶ የኢሕአዴግን ፖለቲካ በተለይም የሰብዓዊ መብት አያያዙን ከመተቸት ተቆጥበው አያውቁም፡፡ ይሁን እንጂ ከምርጫው በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አያውቁም፡፡
በሚቀጥለው ሳምንት በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የአፍሪካ፣ የካረቢያንና የአውሮፓ ኅብረት አገሮች የጋራ የፓርላማ አባላት ጉባዔ ላይ ለመገኘት በአገሮቹ ከተወከሉ ግለሰቦች መካከል አና ጐሜዝ እንዳሉበት በኢትዮጵያ በኩል anaየጉባዔው አስተባባሪ ከሆነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምንጮቻችን ለመረዳት ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለፖርቹጋላዊቷ የፓርላማ ተወካይ አና ጐሜዝ ቪዛ ሰጥቶ ይሁን ከልክሎ ለማወቅ ያደግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ ይሁን እንጂ ግለሰቧ በቲዊተር ገጻቸው ላይ በአዲስ አበባው ጉባዔ ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል፡፡ አና ጐሜዝ በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ምርጫ ትዝብት ሪፖርታቸው፣ ምርጫው ነፃና ፍትኃዊ እንዳልነበር ሪፖርት በማድረጋቸው ሪፖርቱ የውዝግቡ ምንጭ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሪፖርቱን ከማጣጣል አልፈው ግለሰቧን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ መዝለፋቸው ይታወሳል፡፡
አና ጐሜዝ በበኩላቸው እስከቅርብ ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የዕርዳታ ማዕቀብ እንዲጣልበት እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ ‹‹ዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ በተለይም የእንግሊዝና የአሜሪካ መንግሥታት በኢትዮጵያ ዜጎች ላይ መንግሥት የሚፈጽመውን በደል እያዩ እንዳላዩ፤ እየሰሙ እንዳልሰሙ ችላ ብለዋል፤›› በማለት ከዓመት በፊት የሰላ ትችት በመሰንዘር የአውሮፓ ኅብረት ለኢትዮጵያ የሚደረገውን ዕርዳታ እንዲያቆም ተከራክረዋል፡፡ (ሪፖርተር)

Sunday, November 17, 2013

መቋጫ ያጣው የወገኖቻችን ስቃይ እና በደል በሳውዲ አረቢያ አሁንም ቀጥሏል!


ethio saudi 10


ትላንት አመሻሹ ላይ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፉሃ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን አገርሽቶ በዋለው ተቃውሞ የሞተ ባይኖርም ኢትዮጵያውያኑ ድምጻቸውን ከፍ አድረገው አማራው አንድነን … ትግሬውም አንድነን … ጉራጌው አንድነን … መብታችን ይከበር … እኛም ሃገር አለን ወዘተ… በሚል መፈክር ታጅበው ብሶታቸውን ሲያሰሙ መዋላቸውን የሚገልጹ የአይን እማኞች የሳውዲ የጸጥታ ሃይሎች ተቃውሞውን ለመበተን በከፈቱት ተኩስ አካባቢውን ወደ ጦርነት አውድማ ለውጦት ማምሸቱን ይገልጻሉ።
የጸጥታ ሃይሉ በ10 ሺህ የሚቆጠሩ አውቶማቲክ የጦር መሳሪያ የታጠቁ ተጨማሪ ልዩ ፈጥኖ ደራሽ፡ ኮማንዶዎች በመታገዝ የኢትዮጵያውያኑን ተቃውሞው መግታት ተችሏል ብለዋል። እነዚህ ምንጮች ትላንት ተቀስቅሶ በነበረው ሁከት ጥቂት ተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን በማውሳት ሰሞኑን የሳውዲ አረቢያ መንግስት በውጭ ሃገር ነዋሪዎች ላይ ያወጣው ህግ የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን ተከትሎ የሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች በኢትዮጵያውያኑ ላይ እየወሰዱ ባሉት የተናጠል እርምጃ አያሌ ወገኖቻችን ወደ ሃገሩ ለመመለስ ከየመኖሪያ ቤቱ ነቅሎ አደባባይ ቢወጣም ወደ ሃገር መግባት የሚያስችሉት ነግሮች በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ባለመመቻቸቱ ከሳውዲያኑ ወረበሎች አሰቃቂ ግድያ ተርፈው ወደ እስርቤት የተጓጓዙ ከ20 ሺህ የሚበልጡ ወገኖቻችን በምግብ ውሃ እና የመጸዳጃ ቦታ እጦት ቁም ስቅላቸውን እያዩ መሆኑ ተግልጾል።
ለሰው ልጅ መሰረታዊ የሆኑ ነገሮች ያልተሟሉበት ማጎሪያ ውስጥ 4 ቀናቸውን እንዳስቆጠሩ የሚነገርላቸው ኢትዮጵያዊያን እና ሪያድ መንፉሃ ጅዳ እና መካ እስከነ ልጆቻቸው በየመንገዱ ላይ ወድቀው ለመንገድ ላይ አዳሪ የተዳረጉ በመቶሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን ብሶት ለማድመጥም ሆነ ለማየት ከሃገር የመጣ የመግስት ባለስልጣን አለመኖሩ ታውቋል። ይህ በዚህ እንዳለ ዛሬ ጅዳ ከተማ ውስጥ ኢትዮጵያውያኑ የሚኖሩበት አካባቢ በሳውዲ የጸጥታ ሃይሎች እና በኢትዮጵያውያን መሃከል በተነሳ ግጭጥ 76 ሰዎች መቁሰላቸውን የሚገልጹት ምንጮች በዛ ቀውጢ የተኩስ እሩምታ በጥይት ተደብድቦ የተገደለ ኢትዮጵያዊ ሊኖር እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
ተቀማጭነታቸው ሪያድ እና ጅዳ ከተማ በሆኑት በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያው አምባሳደር እና የቆንስላው ጽ/ቤት ዲፕሎማቶች ላይ ተስፋ የቆረጠው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ወገናችንን ለማየት በኢትዮጵያ መንግስት መገናኛ ብዙሃን ወደ ሳውዲ አረቢያ ተጉዘዋል የተባሉት የልኡካን ቡድን አባላት እሰከአሁን ምንም አይነት የሚጨበጥ ነገር መስራት ባለመቻላቸው ኢትዮጵያውያኑ ለከፋ አልቂት በመዳረግ ላይ መሆናቸው ተገልጾል።
ሰሞኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ኢትዮጵያውያኑ በሳውዲ አረቢያ እየተፈጸመባቸው ያለውን የጅምላ ግፍ እና በደል ይሄን ያህል የሚጋግነን እና ቦታ የሚሰጠው አለመሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ትላንት ምሽት መንፉሃ አካባቢ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ከ17 በሚበልጡ አውቶብስ ተጭነው እንደተወሰዱ የሚነገርላቸው ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ህጻናት ሴቶች አረጋውያን የሚገኙበት አያሌ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ከሪያድ የ6 ሰአታት ጉዞ በኋላ ያልታወቀ ምድረ በዳ የሆነ አካባቢ እንዲወርዱ መገደዳቸውን እና እስካሁንም ያሉበት ሁኔታ በውል እንደማይታወቅ ተገልጾል።
(Ethiopian Hagere ከጅዳ በዋዲ ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በፌስቡክ በኩል የላኩት)

Thursday, November 14, 2013

ከካሌብነት ወደ ከልብነት

በእውቀቱ ሥዩም

ethio saudi6


ኢትዮጵያ እመ-መከራ
የግዜር መመራመሪያው የስቃይ ቤተ-ሙከራ
መውደቅማ ነበር ያባት
እንደ ያሬድ እስከ ሰባት
እንደ በላ ብላቴና፣ የእንክርዳድ ሙልሙል እንጎቻ
የትውልዴ እጣ ፋንታ ፣ መውድቅ መውድቅ መውድቅ ብቻ…
አጤ ካሌብ የተባለ የኢትዮጵያ ንጉሥ ባንድ ወቅት በቅድመ-እስልምና የመን የሚኖሩ ክርስቲያኖች ባንድ ያይሁድ ገዥ መዳፍ ስር መማቀቃቸው አስቆጥቶት ቀይ ባሕርን ተሻግሮ ተበቅሎላቸዋል። የዛሬውን አያድርገውና፣ እንኳን ለቤት ለጎረቤት ጥቃት የሚቆረቆር ንጉሥ ማፍራት ችለን ነበር፤ አንኳን ለቤት ለጎረቤት እርዳታ የሚበቃ ጉልበት ማካበት ችለን ነበር። ዛሬ ግን ጊዜ ከካሌብነት ወደ ከልብነት ደረጃ አውርዶናል። (“ከልብ” በግዕዝ ውሻ ማለት ሲሆን በአማርኛ ዘይቤ አንድ ሰው ያለ ካሳ ያለ ጉማ ደሙ ፈሶ ሲቀር ደመ ከልብ ሆነ ይባላል)።
አቅመ-ቢስ ሕዝቦች በጉልቤ ሕዝቦች መዳፍ ስር ገብተው መከራ ማየታቸው በታሪክ ብርቅ አይደለም። እኔን የሚገርመኝ በፋንታችን መከራ ማየታችን አይደለም፤ እኔን የሚገርመኝ ከዚህ ሁሉ መከራ በሁዋላ ከመከራ የሚታደገን የኑሮ መላ አለማፍለቃችን ነው። ከመከራ መደራረብ በሁዋላ ያፈለቅነው የስልጣኔ ፍሬ የሙሾ ግጥም ብቻ መሆኑ ያስደንቃል።
አይሁድ በሁለተኛው ያለም ጦርነት ግፍ ከደረሰባችው በሁዋላ አንሰራርትው በርትተዋል፤ እንደ ኒቼ “ጨርሶ የማያጠፋኝ ሁሉ ያበረታኛል” ብለዋል። ዛሬ በነዳጅ መስክ ላይ የበቀሉ አረሞችን (አረቦችን) ያርበደብዳሉ ። ጀርመኖች በሁለተኛው ያለም ጦርነት ማክተሚያ ላይ በጠላቶቻቸው ከስክስ ጫማ ደቀዋል። ግን በአጭር ጊዜ አንሰራርትው ሃይላችውን እንደ ንስር አድሰዋል፤ እኛስ ይሄን ማድረግ ያቅተናል? አያቅተንም። ያገራችን አስተዳዳሪዎች፣ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ሀያል መንግስቶች ከመከራ ዶፍ የማይታደጉን ነዳላ ጃንጥላ መሆናችውን አይተናል። የራሳችን አዳኞች ራሳችን መሆናችንን አንርሳ፤ ጎበዝ የዳይኖሰርን ፈለግ ከመከተላችን በፊት ትንሽ መላ እንምታ::
- በእውቀቱ ሥዩም ፌስቡክ የተወሰደ (November 11, 2013)

Wednesday, November 13, 2013

“ለኢትዮጵያውያን በችግሩ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጥ እንጠይቃለን”


saudi ethio3


ሰሞኑን በሳውዲ አረቢያ በተለይ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለው እንግልት፣ ድብደባ፣ ግድያና ለህይወት አስጊ በሆነ ሥፍራ ማጎር ከኢሰብአዊነትም በላይበኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ የተሰነዘረ ጥቃት ነው፡፡
ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ!
በአባቶቻችን ደም ታፍራና ተከብራ የኖረችው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በገዢው ፓርቲ ቸልታ፣ የፖሊሲ ችግርና የሀገር ፍቅር ማጣት የተነሳ ዜጎቿ በውርደት እንዲኖሩ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ዛሬም መገለጫችን ስደት፣ ጦርነት፣ በዜግነታችን ክብር ማጣትና ሞት ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ሀገራዊ ውርደትና ሞት ከተበላሸ ሥርዓት የሚወለድ፣ ካልተስተካከለ የኢኮኖሚ ፖሊሲ የሚፈጠር ነው፡፡
ፓርቲያችን የተሻለ ኢኮኖሚ ፍለጋ፣ የተሻለ ማህበራዊ ፍትህ ለማግኘትና አሰቃቂ የሆነውን ፖለቲካ ሽሽት ኢትዮጵያውያን ዜጎች ሀገራቸውን ጥለው እንደሚሰደዱ ያምናል፡፡ የመልካም አስተዳደር እጦትና ሥራ ፍለጋ የሚያንከራትታቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር የትየለሌም ነው፡፡ ጋሎፕ የተባለ አለማቀፍ ጥናት እንደሚያመለክተው በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ጎልማሶች መካከል 46% የሚሆኑት ከሀገራቸው በመሰደድ ወደ ሌላ ሀገር ሄደው ለመኖር ይፈልጋሉ፡፡ ይህ የሆነው የተስተካከለ ስርዓት ባለመፈጠሩ ነው፡፡
ሰሞኑን በሳውዲ አረቢያ በተለይ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለው እንግልት፣ ድብደባ፣ ግድያና ለህይወት አስጊ በሆነ ሥፍራ ማጎር ከኢሰብአዊነትም በላይ በኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ የተሰነዘረ ጥቃት ነው፡፡ ዜጎቻችን ዋስትናና ከለላ አጥተው በሳውዲ ፖሊስ በየጎዳናው ሲፈነከቱና ሲገደሉ ከማየት በላይ አሰቃቂ ነገር የት አለ? በሳውዲ በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመው ወንጀል የሀገር ሉዓላዊነትም ጉዳይ ነው፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያን መንግሥት የዲፕሎማሲ ደካማነትና በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ባህላዊ ግንኙነቶች ላይ ተጽእኖ መፍጠር ያልቻለ መሆኑን ያስረዳናል፡፡ ደካማ መንግሥት፣ ደካማ አስተዳደርና የራሱን ስልጣን ብቻ የሚያዳምጥ ፓርቲ ዜጎቹን ያስደፍራል፣ ሉዓላዊነትን ያስነካል፣ ኢትዮጵያዊ ክብርን ያዋርዳል፡፡
አንድነት ፓርቲ የሰቆቃ ዘመናችን የሚያጥረው ለሀገር የሚያስብ የተስተካከለ ሥርዓት ሲፈጠር ብቻ ነው ብሎ ያምናል፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያውያንን ሰብአዊ ክብር ማስጠበቅ የተሳነው መንግሥት ላይ ጫና ማድረግና በሠላማዊ ትግል መቀየር ወሳኝ ነው፡፡ አንድነት የሳውዲ አረብያ መንግስት በዜጎቻችን ላይ የፈፀመውን ድርጊት ተከትሎ ያለውን አቋም እንደሚከተለው ያቀርባል፡፡
1. የሳውዲ መንግሥት በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈፀመ ያለውን የሰብአዊ ክብር ገፈፋ፣ እስር፣ ግድያና ማዋከብ በአስቸኳይ እንዲያቆም፡፡
2. ለፈፀመው ሰብአዊ ጥፋት ተጠያቂ እንዲሆንና ለተጎጂዎች ካሳ እንዲከፍል፡፡
3. የኢትዮጵያ መንግስት ለተጎጂዎች አስቸኳይ ርዳታና ለችግራቸው መፍትሔ እንዲሰጥ፡፡
4. የኢትዮጵያ መንግሥትም ይህንን በፈፀመው የሳውዲ መንግሥት ላይ ጠንካራ አቋም እንዲይዝና ለኢትዮጵያውያን በችግሩ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጥ እንጠይቃል፡፡
በተጨማሪም በዜጎች ላይ የተፈፀመውና እየተፈፀመ ያለው ግፍ የገዢው ፓርቲ የዲፕሎማሲ ድክመት ያመጣው መሆኑንና እንዲሁም የአምባሳደርነት ሥልጣን የሚሰጠው በችሎታ ሳይሆን በፓርቲ ታማኝነት እንደሆነ ያሳየን ነው፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግሩን ከሥሩ ለማድረቅ የሚያስፈልገው የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማሻሻያ መሆኑ ታውቆ ህዝቡ የተስተካከለ ሥርዓት የመፍጠር ትግሉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ እያቀረብን በተከታይ የምንውደውን ርምጃ ለህዝቡ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ዘላለማዊ ክብር ለኢትያጵያና ኢትዮጵያዊነት!!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
ህዳር 2 ቀን 2ዐዐ6 ዓም

በሳዑዲ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት ለማውገዝ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

በዓለም ዙሪያ በተለያዩ ቦታዎች ሰልፍ ተጠርቶዋል!

ethio saudi5


ከጥቅምት 26 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በሳዑዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን የኃይል ጥቃት ለማውገዝ በአዲስ አበባ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ ተጠራ።
ethio saudi houstonየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) አባል ፓርቲዎች ትናንት በመድረክ ጽ/ቤት በስራ አስፈፃሚ ደረጃ ባካሄዱት አስቸኳይ ስብሰባ በሳዑዲ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሳዑዲ ፖሊስ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት መፈፀሙን፣ አልፎ ተርፎም እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን በመግለፅ ሁኔታውን አውግዟል።
የችግሩ ክብደትና አሳዛኝነት በመቀጠሉ ድርጊቱን በመግለጫ ከማውገዝ ባለፈ ሁኔታውን በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ከመድረክ የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በኋላ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንዳረጋገጡት መድረክ የጉዳዩን አሳሳቢነት በመረዳት ከሚያወጣው የተቃውሞ መግለጫ ጎን ለጎን ሰላማዊ ሰልፍ እንዲጠራ መወሰኑን ተናግረዋል። ሰልፉን ለማካሄድ ለአዲስ አበባ የሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ክፍል ለማሳወቅ ደብዳቤ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልፀዋል። ኅብረተሰቡም ድርጊቱን ለማውገዝ ከፓርቲዎቹ ጎን በመቆም የተቃውሞ ድምፁን እንዲያሰማ ጥሪ አድርገዋል። የሰልፉ ቀንና ቦታ በአጭር ቀናት ውስጥ ለሕዝቡ እንደሚገለፅም አያይዘው ገልፀዋል:: የሰንደቅ ዜናዎች (በዘሪሁን ሙሉጌታ)
ethio saudi torontoethio saudi swiss1ethio saudiswiss

“Are Ethiopians without a country?”

SMNE holds KSA and EPRDF accountable!

ethio saudi


Press Release
Washington, DC, November 11, 2013
SMNE Calls on the Saudi government to stop this brutal and inhumane treatment of the Ethiopian migrant workers immediately And on the TPLF/ERPDF regime to Protect Ethiopian Citizens in Saudi Arabia
The Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE), a non-political and non-violent social justice movement of diverse people that advocates for freedom, justice, good governance and upholding the civil, human and economic rights of the people of Ethiopia, without regard to ethnicity, religion, political affiliation or other differences, is highly disturbed by reports, pictures and video footage of the violence being perpetrated against Ethiopian migrant workers in Saudi Arabia. Please take a look at the video links here,here and here.
saudi ethioSince the November 3, 2013 deadline in Saudi Arabia, which marked the end of the amnesty period during which all undocumented foreign workers were required to legalize their status or face deportation, Ethiopians working in the Kingdom of Saudi Arabia (KSA) have faced beatings, torture, rape, and serious injury.
Please take a look at the pictures here. Although many of the over 16,000 migrants who have been arrested are Ethiopians, workers from other countries, such as the Philippines, are also represented.
Graphic pictures of blood, injury and death are circulating on websites and in the social media. We in the SMNE have received countless phone calls, emails, pictures, videos and messages telling about and showing Ethiopians who have been victims of these crimes. One was a heartbreaking picture of a young Ethiopian man who was shot dead on the street, the blood from his wounded body flowing onto the pavement. Eyewitnesses to his murder report that this man was shot in the head as he tried to run away. He may have feared arrest or the brutal treatment at the hands of Saudi police. In one reported case, a handcuffed man, already contained, was still beaten by the police. In another video clip, Saudi civilians can be seen beating up other men. According to reports to the SMNE from Ethiopians in Saudi Arabia, a total of 7 Ethiopians have been killed, 218 have been injured and over 368 are missing. This brutality is outrageous.
We call on the Saudi government to stop this brutal and inhuman treatment of these migrant workers immediately and to hold those who have committed these crimes accountable, including those in uniform as well as civilians. If the KSA seeks to deport undocumented workers, it is your right to carrysaudi ethio1 out your laws; however let it be done in a civilized and respectful manner. These people, most of whom entered the country legally with visas, should not be treated as criminals, beaten up and tortured for not having papers or not having the right papers.
A number of the injured have not received any medical care. Those arrested are taken by authorities without leaving any information of their whereabouts with family or friends. One young girl told of how she was raped on the street by a civilian mob of Saudi men who attacked and gang-raped her.
Another young girl reported being inside a house where she was staying with two other women and two men. She reports: “Saudi police in uniform broke down the door to our house and rushed in. They ordered all of us to lay flat on the floor and to give them our papers. We obeyed immediately. One of the other girls told the police that we were not illegal, saying, ‘We have papers.’ In response, one of the police kicked her in the head and demanded that she hand over the papers. When she gave them to him, he took them and tore them apart. She asked why and the police started beating everyone. Two police officers took the men in our group to some unknown place and left us girls with the five remaining police officers. Immediately, they started touching us inappropriately. We started screaming and then they forced us to do what they wanted to do with us.”
At this point in the story, she broke into tears and said she did not want to say any more, finally saying, “These people are treating us like animals. Even now, I don’t know where these men have been taken. One of them is my husband. The girl, whose papers were destroyed, was taken away by the police and I don’t know what has happened to her. They [the authorities] are saying that the law was put into place for those who do not have papers [undocumented workers] but we had all the proper papers and they are still treating us like this.”
saudi et1In another report, an Ethiopian man spoke of how he was providing safe shelter for nine women because it was so dangerous for young women to go outside. He stated that due to the absence of any law and order and civilian mobs prowling the streets for migrant workers, the possibility of these women being raped was extremely high. He had been in the country for over ten years and was running a business.
Men are also at risk for being beaten or tortured, which has happened in cases where they were not even asked to produce documentation of their status. Instead, it appears that non-Saudis are attacked at will for simply not being native-born. Compliance with the law does not seem to make a difference.
One man reported, “Several days ago, a mob of Arab men came to the place where we were staying and began to beat us. We started fighting back because whether you obey the law or not, you can still be beaten, tortured or killed. It leaves us no option but to take the law into our own hands to protect ourselves since no one here will protect us. Those in uniform are no different than the mobs in this respect. If they attack, we will fight back.” This is what is happening on the ground according to reports we have received from eyewitnesses.
One man said, “These same brutal attackers may be eating food grown in Ethiopia. Not only that, but some of the Ethiopians who have been beaten up like this may be here in Saudi Arabia seeking opportunity because they have been evicted from their land and their land has been given to Saudi investors.” This is very, very disturbing. Saudi Arabian investors have been leasing large sections of fertile, well-watered land in Ethiopia to grow food on mega-farms for export to Saudi Arabia while they are mistreating Ethiopians here. This should be exposed.
After receiving many desperate calls from Ethiopians in Saudi Arabia and in the Diaspora, starting on Tuesday, November 5, we in the SMNE called the United Nations High Commissioner for Refugees (UNHCR) in Geneva on Friday, November 9 to ask for help in addressing this mounting manmade crisis. They told us that it was not part of their mandate because these people were not refugees, but instead were migrant workers. When they were asked who would be the right organization to help, they suggested calling the International Labor Organization (ILO) or the International Organization for Migration (IOM), both of which are part of the United Nations.
We called IOM first and were told there was not much they could do about it because again, it was not part of their mandate because Saudi Arabia, as a sovereign country who had passed a law requiring undocumented workers to leave their country, it was considered an internal national issue.
Contact was then made with ILO. They said they were aware of the problem and did document such things but that there was not much they could do about it. They said the best group to deal with this would be the government of the country where the immigrants had originated—Ethiopia.
The next call was to the Ethiopian Embassy in Saudi Arabia where an Ethiopian official there answered the phone. He was not helpful, nor was he particularly sympathetic to the plight of the migrant workers, but instead he put the blame on the workers saying that they were given seven months to get papers and should have done so a long time ago. He was then told that there were numerous cases where these Ethiopian workers had the right paperwork, but that the papers were destroyed or ignored by the authorities or civilian groups. This embassy official was told that what has been done to “your own citizens” was wrong and that it was the responsibility of the embassy to take care of these Ethiopians like other countries are doing. It was also emphasized that the Ethiopian embassy should not just sit by, doing nothing, instead of trying to do more when Ethiopians were suffering like this. He became very irritated with this suggestion; saying he had nothing more to say and abruptly hung up the phone.saudi ethio2
We call on the international community, human rights organizations and the international media to expose the mistreatment and human rights abuses of these migrant workers in the KSA and take whatever action they can to protect these vulnerable people, including helping them to leave the country.
We call on Ethiopians, wherever they are, to make appointments at Saudi Arabian Embassies throughout the world to tell them to stop the torture, rape and brutality being waged against these migrant workers and to hold those who have committed the crimes accountable. As they have already made it clear, they do not want these migrant workers in their country and want to deport them, but at the very least they should still treat them with civility. This advocacy work is something Ethiopians should do in multiple places. Also, if Ethiopians have family or friends in Saudi Arabia who have been affected by these actions, get accurate details and give the information to the media.
These evil deeds thrive best in the darkness, so let the light shine on what happened. We commend those who have already done a remarkable job of exposing the truth through their eyewitness accounts, pictures and videos. Let the world know. However, the root solution to the plight of these migrant workers is for Ethiopians to have a government that cares for the welfare of all Ethiopians. Instead, many Ethiopians run to other countries for opportunities denied to them in their own country.
In the early eighties, the regime under Mengistu Hailemariam was known for the starvation of its people, but today the current regime under the TPLF/ERPDF is known for the constant flood of Ethiopians to other places in the world. Many do not ever make it and others suffer tragedy in other countries like they now are experiencing in Saudi Arabia.
Are Ethiopians people without a country? When will the government of Ethiopia be a government that cares about its people? Why should Ethiopians have to go in every direction for help except to their own government?
The heart of Ethiopia cries for its lost children who are dying abroad because their own country has become so inhospitable to life that they take huge risks that often end badly. No wonder they are the fifth largest group of people in the world subjected to human slavery.
Great numbers are also subjected to mistreatment, hardship and death as they fall into the open and greedy hands of human and sexual traffickers; dying in places like the Red Sea, Egypt, Yemen, Saudi Arabia, Kenya, Tanzania, Malawi, South Africa, Central America, and in a shipwreck offshore from the Italian island of Lampedusa. All of this is happening because of the lack of a government who cares for its citizens.
We call on all Ethiopians to find solutions to this urgent crisis in Saudi Arabia, but we cannot simply go from crisis to crisis. We must demand long term solutions. It is clear now that the only way Ethiopians can be respected as a people is to establish a government in their own country that sees all of them as precious human beings, putting humanity before ethnicity rather than the unhealthy system of the TPLF/ERPDF based on ethnic favoritism at the expense of everyone else. Ethiopians deserve a home where they can live freely and flourish, where people do not undertake horrendous risks for basic opportunities that should be theirs from the start.
We in the SMNE will continue to monitor the situation, but believe the TPLF/ERPDF regime should take immediate responsibility to resolve this current crisis by sending airplanes to bring their own citizens back home and to make the Saudis accountable for those who have been killed or injured. If the Saudis do not respond, Ethiopia should close down their embassy in KSA as a sign of strong condemnation for the barbaric mistreatment committed against the Ethiopian people. Furthermore, the TPLF/ERPDF should seek a moral solution to the longstanding problems within Ethiopia. How can the problem of mass migration be sustainably solved without deep and meaningful reforms, the restoration of justice and reconciliation?  None of us will be free until all of us are free.
May God protect these Ethiopian brothers and sisters in Saudi Arabia and give our diverse and beautiful people the strength and humility to come together as we struggle to create a more just, united, reconciled and hospitable Ethiopia for all.  =============================
For more information or media enquiries please contact:
Mr. Obang Metho,
Executive Director of the SMNE
910- 17th St. NW, Suite 419
Washington, DC 20006 USA
E-mail: Obang@solidaritymovement.org
Website: http://www.solidaritymovement.org
CC To:
Kingdom of Saudi Arabia Ministry of Foreign Affairs
Ministry of justice Kingdom of Saudi Arabia
Ministry of Interior Kingdom of Saudi Arabia
Saudi Embassy in Addis Ababa
Saudi Embassy in London, United Kingdom
Saudi Arabian Embassy in Canada
Saudi Arabian Embassy in Washington, D.C.
The office Prime Minister of Ethiopia
Addis Ababa, Ethiopia
American Embassy in Addis Ababa, Ethiopia
Ambassador Patricia M. Haslach
European Union
Ambassador Mr. Xavier MARCHAL
Head of Delegation
A24MEDIA
All Africa
BBC AFRICA
Bloomberg News
NCNB Africa
CNN
INDIAN OCEAN NEWSLETTER
REUTERS AFRICA
The East Africa
African Review
VOA Ameharic
VOA-English
U.N. High Commissioner for Human Rights
Human Rights Watch
UNHCR-
Amnesty International,
IOM
ILO

ታላቅ ሀገራዊ የተቃውሞ ጥሪ!! ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ!!!

ከወገኖቻችን ጐን በመቆም ብሄራዊ ክብራችንን እናስመልሳለን

ሰሞኑን የሳውዲ አረቢያ መንግሥት በኢትዮጵያዊያን ላይ እየፈፀመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ጥሪ አስተላልፏል፡፡በመሆኑም በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ኢሰብዓዊ ድርጊት ለማስቆምና የዜጐችን ህይወት ለመታደግ እንዲሁም ዜጐቻችን በአፋጣኝ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ መንግሥት እንዲያመቻች እና በተጨማሪም በዜጐቻችን ላይ ለደረሰው የአካል መጉደል፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈርና የህይወት መጥፋት ኃላፊነቱን የሚወስዱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ፤ ለተጐዱ ወገኖቻችንና ቤተሰቦቻቸውም አስፈላጊው ካሳ እንዲደረግላቸው ፓርቲያችን አበክሮ እያሳሰበ፤ የብሄራዊ ክብርና የወገኖች ስቃይ የሚያሳስባቸው አካላት በሙሉ በዚህ ታላቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡Ethiopia's Semayawi party (blue party)
የተቃውሞ እንቅስቃሴ አፈፃፀም፡-
1. በዜጐቻችን ላይ የአካል መጉደል፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈርና የህይወት መጥፋት ያደረሰው የሳውዲ አረቢያ መንግሥት ኢምባሲ በሚገኝበት ቦታ አርብ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ጀምሮ የሚደረግ የተቃውሞ ሰልፍ፣
2. ከአርብ ጠዋት ጀምሮ እስከ እሁድ ማታ ድረስ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሀዘን ልብስ (ጥቁር ልብስ) በመልበስ በግፍ ለሞቱና ለተንገላቱ ወገኖቻችን ሀዘናችንን መግለፅ፣
3. የእምነት ተቋማት አርብ በመስጊድ በጁምአ ሥነ ሥርዓት ላይ እና ቅዳሜና እሁድ በአብያተ ክርስቲያናት የፀሎት ሥነ ሥርዓቶች ላይ ወገኖቻችንን በፀሎት እንዲታሰቡ፣
4. ቅዳሜ በሚደረገው የኢትዮጵያና የናይጄሪያ የእግር ኳስ ጨዋታ ላይ ተጫዋቾቻችን ጥቁር ሪቫን በክንዶቻቸው ላይ አጥልቀው እንዲጫወቱ፣ እንዲሁም መላው ደጋፊ ጥቁር ጨርቆችን በመያዝ ወይም ልብስ በመልበስ ሀዘኑንና ቁጭቱን እንዲገልፅ፣
በፓርቲው የተወሰነ በመሆኑ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ሲቪክ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዓለም አቅፍ ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ መላው ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ወዳጆች በጠራነው የተቃውሞ ሰልፍና እንቅስቃሴዎች ላይ በመገኘት ከግፉአን ወገኖቻችን ጐን መቆሙን እንዲያረጋግጥ በአፅንኦት እንጠይቃለን፡፡
♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦
የወገኖቻችን ሰቆቃ እስኪያበቃ በፅናት እንታገላለን!!!
Blue Party Protest in Addi

የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ በዋሽንግቶን ዲሲ ሳውዲ አረብያ ኤምባሲ!

ቀን ፡- ኖቨምበር 14, 2013 ዕለተ ሐሙስ ከጥዋቱ 9 ሰዓት በኤምባሲው ፊት ለፊት ይጀምራል።
አድራሻ፡- 601 New Hampshire Avenue NW, Washington DC 20037
Public trasport:- Foggy Bottom metro station – Blue and Orange line
የሰልፉ አንገብጋቢነት፣ መነሻና አላማ፡- ሰሞኑን በተለያዩ የብዙሃን መገናኛዎች እንደተገለፀው ሁሉ በሳውዲ ዓረቢያ በተለያዩ ከተሞች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰውና አሁንም በባሰ መልኩ እየተፈፀመ ያለው አስነዋሪ፣ አሳዛኝ፣ አሳፋሪና አስደንጋጭ የሆነ ኢሰብኣዊ ድርጊትን በመቃወም፡- [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]
Protest at Saudi Arabia Mission to United Nations!

Monday, November 11, 2013

በሳዑዲ አረብያ የመከራ ማጥ ውስጥ ላሉት ወገኖቻችን ሲባል ፈጥነን እንነሳ!

ዳኛቸው ቢያድግልኝ

እንደ ሰው አንድ የሚያደርገን ባሕርይ፣ እንደ ኢትዮጵያዊነትም ሁላችንንም የሚመለከተንና የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት የማይነጣጥለው በደል በሳዑዲ አረብያ ግዛት እየተፈጸመ ነው። የጥቃት ዒላማዎቹ ኢትዮጵያውያን ናቸው። የጥቃቱ ልክ የለሽነትና አሰቃቂነት ደግሞ ይበልጥ የጎላው በሴት እህቶቻችን ላይ ነው። ይህ ዛሬ በሳዑዲ አረብያ የሚደረገው ጥቃትን ማስቆምና ቁጣችን መቆምያ እንደማይኖረው ማሳየት ለነርሱ ብቻ ሳይሆን ለራሳችን ደህንነትም ጭምር የምናደርገው ነው። ምክንያቱም ነገ ተመሳሳይ ጥቃትና በደል በመላው አለም ይስፋፋል። በአፍሪካ ሀገሮች የተበተኑ ኢትዮጵያን ከሶማሌና ኤርትራ ከሚሰደዱት በተለየ ይዘረፋሉ፣ ይደፈራሉ ይዋረዳሉ። እንደ አገር ልጅ አብረው እንዳይቆሙ በዘር በሀይማኖትና በፖለቲካ አቋም ምክንየት የተበተኑ ናቸው። ለሰላሳና አርባ አመት አምባገነኖች ያደረጉት ጭፈጨፋና በደል ፍርሃትን ሰማይ ጥግ አውጥቶታል። እናም ኢትዮጵያዊ በየተበተነበት ሁሉ ተኛ ሲሉት የሚተኛ አውልቅ ሲሉት እርቃኑን የሚቆም ፈሪ እንዲሆን ተደርጓል። ሲቸግረው የሚጮኸውን ያህል ሲመቸው ለወገን የሚደርሰው ጥቂቱ ነው። ይህ ሊቀጥል አይገባም!Protest at Saudi Arabia Mission to United Nations!
ቀደም ባለው ጊዜ አንድ ኢትዮጵያዊ ጥቃት ቢደርስበት ባገኘው መሳርያ ዘነጣጥሎም ቢሆን ይገድል ስለነበር ማንም አይደፍረውም ነበር። በዘመነ ኮሎኒያሊዝም ኢትዮጵያውያን በሄዱበት ሁሉ አንገት የማይደፉና ክብራቸውን የማያስነኩ ነበሩ። ዛሬ ጠቁመው የሚያስይዙ፣ ወገናቸውን የሚያሻሽጡና የሚሰልሉት ሁሉ ኢትዮጵያውያን ናቸው። የዚህ ጽሁፍ መነሻም ሆነ መድረሻው የድሮውን አሁን እየሆነ ካለው ጋር ማወዳደር አይደለም። ለዚህ የሚሆን የቅንጦት ጊዜም የለንም። ዓላማው አሁን እየደረሰብን ያለውን በደል በቁርጠኛነት አንታገለው ነው። ይህ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ከዳር እስከዳር ማስነሳት ካልቻለና ቁጣቸውንም ለመላው አለም ማሳየት ካልቻለ እውነትም አገራችን እያበቃላት ነው ማለት ይቻላል።
የዱር አውሬ እንኳን ከዚህ የተሻለ ክብር አለው። እነዚህ እጅግ ኋላ ቀር የሆኑ አረመኔዎች ከእንስሳ እንኳን አንሰው አንዲት በፍርሃት ነብሷን የሳተችን ሴት አስር ሆነው የሚደፍሩትን እያየን የተደፈሩት ህጋዊ ናቸው ህገወጥ የሚል የሕግ አንቀጽ መረጣ ውስጥ ልንገባስ እንዴት ይቻለናል? በመላው አለም ያለ የሳዑዲ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ ሊደረግና የሳዑዲ ወሮበሎች በወጣት ሴቶች ላይ እያደረሱ ያለው ግፍ በመረጃም ተደግፎ በበራሪ ወረቀትም ተዘጋጅቶ ለአለም ሕዝብ ሊበተን ይገባዋል። ተፈጥሮ ዘይትን ስትቸራቸው አእምሮ ግን እንደነፈገቻቸው ከዚህ በላይ መረጃስ ከየት ይመጣል?
እንደ ትውስታ ከወሰድነው በኬንያ ያሉ ስደተኞች ላይ በደል ይደርስ በነበረበት ወቅት ያ በጨካኝነቱ የሚታወቀው መንግሥቱ ሀይለማርያም እንኳን “ኢትዮጵያውያኑ የተሰደዱት የምናራምደውን ፖለቲካ እንጂ ሀገራቸውን ጠልተው አይደለም…” በሚል ኬንያን ማስጠንቀቁን መስማቴ ትዝ ይለኛል። በየወሩ 40 ሺህ ሴቶችን እንልካለን እያለ እንደ እንቁላል በየአረብ ቤቱ ሲያከፋፍል የነበረው መንግስት ዛሬ ዜጎቹ እንዳይሆን መጫወቻ ሲሆኑ ዝም ብሎ መመልከቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው። ኢትዮጵያውያኑ ምናልባትም ኤምባሲውን ራሱን መቆጣጠር የሚገባቸው እስኪመስል ያስቆጣል።
በኢትዮጵያዊነት ላይ የተነጣጠረን ክፋት እንደ ሀገርና እንደ ሕዝብ ካላስቆምነው በሳዑዲ የተጀመረው መረን የጥላቻ ሰደድ ሊቀጣጥል የሚችልና የየሀገሩ የፖለቲካ ኪሳራ ማስተንፈሻ የሚሆነው አገር አጥቶ የተሰደደው ኢትዮጵያዊው ላይ ሁሉ ይሆናል። ይህንን በአስቸኳይ ለመቃወም ያሉ የትግል መንገዶች ሁሉ ክፍት ሊሆኑ ይገባል። እኔ አዘጋጀሁ እኔ ጠራሁ የሚል ደካማ የፖለቲካ ትርፍ ፍለጋ መንቀሳቀስ ሳይሆን ለሰብዓዊ ክብርና የመከራ ማጥ ውስጥ ሆነው የወገን ያለህ ለሚሉት እህት ወንድሞቻችን የድረሱልን ጥሪ ምላሽ እንስጥ። በጣም የሚያሳዝነው አብዛኞቹ ለስራ የሚሄዱት ወጣቶች የትምህርት ደረጃቸው አነስተኛ የሆነና በድህነት ውስጥ ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት የሆነው ይሁን ብለው ከቤታቸው የወጡ ናቸው። አንዳንዶቹም ግሩም እድል አንደሚገጥማቸው በደላላዎች እየተነገራቸው ከቤት ወጥተው የቀሩ ናቸው። ለኒህ አጋር መሆን ለሀገር እንኳን ደንታ ባይኖረን ለነብስ የሚበጅ ስራ ነው። የኢትዮጵያ ኮሙኒቲዎች፣ በኢትዮጵያ ስም የተቋቋሙ የሀይማኖት ማዕከላት፣ ሲቪክ የፖለቲካ ድርጅቶች በሙሉ ለዚህ ዓላማ ቢቻል አደራጆች ካልተቻለም ዋንኛ ተሳታፊዎች ሊሆኑ ይገባል። ይህ በደል እጅ ለእጅ ሊያስተሳስረንና አንድ ላይ እንድንቆም ሊያደርገን የሚችል የጋራ ጉዳይ ነው። ዛሬ ነገ ሳንል በተደራጀና አለም አቀፍ ትኩረት ሊኖረው በሚያስችል አቅሙ እንነሳ ለወገንም አንድረስ።የመከራ ቀናችንን ለማሳጠር እንደ ሕዝብም ከአንገታችን ቀና እንድንል በያለንበት እንትጋ!
biyadegelgne@hotmail.com

Sunday, November 10, 2013

በውሸት የሚያሸብረው አሸባሪ መንግስት!

እለቱን ባላስታውሰውም ግንቦት 20ቀን1983ዓ.ም ወያኔ አዲስ አበባ ሲገባ በቦታው ሆኘ ያለውን ቆራጥነት ለዚያች ቀን መብቃታቸውን ለህዝቡ ጥሩ ነገር ይዘው ይመጣሉ ብዬ ባላስብም ግን ጽናትና ብርታታቸውን ግን ከሚያደንቁ አንዱ ነበርኩ‘። እውነተኞች ውሸት የሌለባቸው ሌብነት የሚጸየፉም ሆነው ሲቀርቡ ይበል አልን እንጂ የተቃወመም አልነበረ ፤ እዲያውም እዲያውም ከማስታውሰው መርካቶ ተክለሃይማኖት አካባቢ ግልጽ መኪና ላይ ሆነው ሰው ከቦ ሲያወራቸው ከመኪናው ላይ ኩንታል ስኮር ተሰርቀው ዋይ ዋይ ሲሉ ምስኪኖች ብዬ ስቄ ነበር ። ከዚያም በመቀጠል ሌባ ሲሰርቅ ከተያዘ ይገደል ሲሉ እረ ጎበዝ ይህ ነገር ተባለ፤ ግና በሌባው አጀብ የሚፈልጉትን በማስወገድ  ሌብነቱና  ውሸቱም ተያይዞ ቀጠለ።                                

ይቅርታ ብዙም እዳልዘባርቅ እንዲያው ለመንደርደሪያ ብዬ እንጂዛሬ እዲያው ያአሸባሪው ታሪክና አካሄዱ የሚያስቅ የውሸት ድራማ ላወጋችሁ ነው ። ባለፈው ጊዜ የኢትዩጵያ ብሔራዊ ቡድን ከናይጀሪያ አቻው ጋር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ቀን በቦሌ ክፍለ ከተማ አሸባሪወች በስታዲየም ባሉ ንጹሀን ዜጎች ላይ ፈንጂ ለማንጎድ ሲዘጋጁ በራሳቸው ላይ ፈንድቶ  አሸባሪወች በፍንዳታው ሰውነታቸው በቃጠሎ አረው ሲሞቱ በቤቱ ላይ ከፍተኛ ቃጠሎ ተነስቶ ንብረት እንደጠፋ ወያኔ እደፈለገ የሚአደርገው ቴሌቨዝንና ሬድዮ ሲናገር ተከትሎም የፌደራል ፖሊስ መግለጫው ስታዲየም ገብተው ሊያፈነዱ እደነበረ ከቤቱም የኢትዮጵያ ባንዲራ እዳገኙና ሁለቱም የሱማሌ ዜጎች እንደሆኑ ነገሩን ውሸት ይላሉ………እንደዚያ ነው ባንዲራው ከምን ተሰርቶ ነው ሳይቃጠል የቀረው አንድ አትሉም ፤ አሁን ደግሞ በቤንሻንጉል ክልል አሸባሪዎች የቀበሩት ፈንጂ መለስተኛ አውቶቡስ በላዩ ላይ ቆሞ ነው አደጋው የደረሰው ነው ያሉን ? ይገርማል የነሱን የድንቁርና አባባል ህዝብ ይሰማናል ማለታቸው፤ ፈንጂ ላይ የቆመ መኪና አካሉ ይቆራረጣል፤ ይፈናጠራል ቢያንስ የቆመበት ጎማ ይበተናል በሚዲያ ተለቆ ያየነው ምስል የሚያሳው ከመኪናው ውስጥ ቃጠሎ እንደሆነ በትክክል ያሳያል ሃያ አመት ውሸት የተማረን መንግስት እውነት እንዴት ይቀበላል ነው የምትሉት ታዲያ??
Terror in Ethiopia