FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Saturday, August 31, 2013

ESAT Breaking News Aug 31 2013 Semayawi party


የ“አምላካችሁ ባሮች” የሆናችሁ “ሰላማዊ ሰልፈኞች” ቅድሚ የምትሰጡት ለማን ነው?

(ርዕሰ አንቀጽ)

religious leaders in addis


እርቅን፣ ሰላምን፣ ፍቅርን፣ መቻቻልን ለማውረድ የሃይማኖት አባቶችና ሽማግሌዎች ቁልፍ ሚና አላቸው። በር ዘግተው ይጸልያሉ። ያስታርቃሉ። ይገስጻሉ። ያስጠነቅቃሉ። እንዲህ አይነት ለሌሎች ብርሃን ለመሆን የሚቃጠሉ የሃይማኖት አባቶች ያሏቸው ምንኛ የታደሉ ናቸው?
በተቃራኒው የአምላክ ባሪያዎች፣ የየእምነታቸው ባሪያዎች፣ የምዕመናን መንፈስ መጋቢዎችና ጠባቂዎች፣ ወዘተ አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚወጡ በይፋ ተነገረን። “በተገንጣይ ነጻ አውጪ” ስም እየተጠራጠረና እየተጸየፈ አገራችንን ከሚመራ ከሃዲ ድርጅት ጎን ለመቆም የሃይማኖት መሪዎች መነሳታቸው ለፈረደባት ኢትዮጵያና ለህዝቧ ከዚህ በላይ ሃፍረት የለም!! ችግሩ በውስጥም በውጭም ያለውን ይመለከታል። ይህንን ስንል ምክንያታችንን ህዝብ ይረዳዋል ብለን እናምናለን።
በሰማያዊውም ሆነ በምድራዊው ዓለም “መተፋት” አለ። የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች ከዚህ አስደንጋጭ /ለሚደነግጡት ነው/ የፈጣሪ ቅጣት ይጠበቁ ዘንድ ምን ማድረግ እንደሚገባችሁ በወጉ ታውቁታላችሁና ዝርዝር ማብራሪያና ስብከት ውስጥ አንገባም። ተግባራችንም አይደለም። ግን ልብ ያለው ልብ ይበል! ለማለት እንወዳለን። ከመተፋትና ከመናቅ፣ ብሎም ተጠቅመው እንደሚጥሉት እቃ ከመጣል ይጠብቃችሁ!!
ሰሞኑን የሃይማኖት መሪዎችን ኢህአዴግ ሰብስቧቸው ድርጅታዊ ሥራ እንዴት መሥራት እንዳለባቸው ሲያሰለጥናቸው ነበር። በግልጽ ቋንቋ “ሃይማኖታዊ ካድሬነትን” ሲያስተምራቸው ሰንብቷል ማለት ነው፡፡ ስልጠናው “ጽንፈኝነትን ተቃወሙ” የሚል ነው። የተማሩትን በተግባር ለመፈጸምና ያላቸውን ልዩ ብቃት ለመገምገም እሁድ የሰርቶ ማሳያ ሰልፍ እንዲወጡ ተጠይቀዋል፡፡ በኢህአዴግ ቋንቋ ሰልፉ “ተሞክሮ ማስፋት፣ ማስፋፋት፣ ማስረጽ፣ ማሳለጥ … ” መሆኑ ነው።
ጽንፈኝነትን መቃወምም ሆነ በሃይማኖቶች መካከል ተቻችሎ ለመኖር በህብረት መነሳት ይሁን የሚባልለትና በመርህ ደረጃ ሊደገፍም የሚገባው ጉዳይ ነው። በየትኛውም ደረጃ፣ ማህበር፣ ተቋምና የሃይማኖት ቤቶች ውስጥ የሚጠነሰስን “ጽንፈኛነት” ባግባቡ መቃወም ሃጢያትም የለውም። ዓለም በሙሉ ባንድነት በሰላማዊ ሰልፍ ጽንፈኛነትን ማስወገድ ቢችልና ሰላም ለማውረድ ባንድነት ቢሰሩ ክፋት የለውም። ወደ ኢህአዴግ ሰራሹ የተቃውሞ ሰልፍ ስንመጣ ግን ለሁሉም ወገኖች ጥያቄም፣ ማሳሰቢያም፣ ፍርሃቻም አንዳለን ለመግለጽ እንወዳለን።
የሃይማኖት መሪዎች በሙሉ ኢህአዴግ ራሱ ለፈጠረው በሽታ “ክትባት አለኝና ኑ ልክተባችሁ” ከሚለው ድብቅ አስተሳሰቡ በተለየ እንዴት በነጻ አስተሳሰብ ላይ ይቆማሉ? ብለን ስንጠይቅ መልሳችን ” አይታስብም” የሚል ይሆናል። ምክንያቱን በውጪም በውስጥም ያሉ የሃይማኖት ተቋማት በሙሉ ነጻና “ፈሪሃ አምላክ” የነገሰባቸው እንዳልሆኑ እንረዳለንና!! ከዚያም በላይ የሁሉም ወገን ስጋት ይኸው የሃይማኖት መሪዎች መገሸብ ይመስለናል። ኢህአዴግም እንዳሻው የሚነዳቸው አፈጣጠራቸውንና ጽናታቸውን ስለሚገነዘብ ነው።
ሃይማኖቶች የሰላምና የፍቅር መስበኪያ ቦታዎች ናቸው ቢባልም አንዳንድ ሰዎች በጣም ሃይማኖታቸውን ከመውደዳቸው የተነሳ ዓለም በሙሉ የእነርሱ ሃይማኖት እንዲወድላቸው ከመፈለግ የተነሳ በፍቅር የጀመሩትን እምነት አክርረው የጥላቻ መነሃሪያ ያደርጉታል፡፡ ይህ ደግሞ በተለያዩ ሃይማኖቶች ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት ሲንጸባረቅ የኖረ እውነታ ነው።
ሰሞኑን ኢህአዴግ የሰበሰባቸው የሃይማኖት ድርጅቶችም መስመር ሊወጣ የሚችለውን የአክራሪነት አቋም እንዲያወግዙ ነቅተዋል፤ ሠልጥነዋል፡፡ በጉባዔው ላይ ሼክ ከድር ሙሐመድ “ሃይማኖት ሰላም ነው። አገራችን ሰላም ትፈልጋለች፤ አገራችን ስትታመም መድኃኒቷ እኛ ነን” ብለዋል። ግሩም አባባል ነው።
አቡነ ማትያስ በበኩላቸውም “የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት የሚፈታተኑ የሁላችንም ተቃራኒ ናቸው፤ ይህንን የመቋቋም ኃላፊነትና ግዴታ አለብን፤ … የየእምነታችንን ተከታዮች የአገራችሁን ሰላም ጠብቁ ብለን መስበክ የምንችልበት ሰፊ መድረክ አለን” በማለት ሃሳባቸውን በመሰንዘር ሌሎቹም የሃይማኖት ተቋማት ምን ማድረግ እንዳለባቸው መክረዋል፡፡
ለሃይማኖት መሪዎቹ የምናስተላልፈው መልዕክት ቢኖር ይህንኑ ለአገር ተቆርቋሪነታችሁን እና ሰላም ወዳድነታችሁን “ያልተጠኑት ገጾች” ላይ አስፍሯቸው ነው፡፡ ላለፉት 22ዓመታት ሰላም ሲነፍግና ህዝብን ሲጨቁን፤ ዜጎችን በግፍ እስርቤት ሲከትና በቃላት ሊነገር በማይቻል ሁኔታ ሲያሰቃይ፤ ሲገድል፣ በጅምላ ሲጨፈጭፍ፣ ከመኖሪ ቦታ ሲያፈናቅል፣ ዜጎቹን ለአረብ አገር ለግርድና ሲሸጥና ሲያሻሽጥ፣ ህጻናትን (ወንድ ህጻናትን ጨምሮ) ለወሲብ ንግድ ሲሸቅጥ፤ የአገር ድንግል መሬትን የተፈጥሮ ደን እየጨፈጨፈ በሳንቲም ሲሸጥ፣ የመናገር፣ የመሰብሰብ፣ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ … መብትን ሲነፍግ፣ የመናገርና ሃሳብ የመስጠት መብታችን ይከበር ያሉትን ሁሉ እንደ ወራሪ ኃይል ደረትና ግምባራቸውን በጥይት ሲበሳ፣ የኢትዮጵያ እናቶችን ለዘመናት ሲያስለቅስ፣ … የኖረውን ኢህአዴግን በነካ እጃችሁ “ተው ተመከር፤ ይብቃህ፤ እረፍ!” ስትሉና ስትገዝቱት ባለመሰማታችሁ ምመናን አዝነውባኋል። አሁንም ግን ጊዜ አለና በነካ እጃችሁ ኢህአዴግንም አስጠንቅቁ፣ አውግዙ።
የሃይማኖት አክራሪነትንና ጽንፈኝነትን ብቻ ሳይሆን በነጻ አውጪ ስም የመንግሥት ሥልጣን ይዞ አገርን ላለፉት 22ዓመታት ሲያሸብር የኖረውን አክራሪውና ጽንፈኛውን ህወሃትን ራሱን “እስካሁን የረገጥከው ሰብዓዊ መብት ይበቃሃል” በማለት ሃይማኖታዊ ድርሻችሁን ተወጡ፡፡ የሰላም አስጠባቂ፣ የፍትህና የሰብዓዊ መብት አስከባሪ ካድሬ ሁኑ፡፡ በምድር ላለው ኑሮና ተድላ ሳይሆን ለመጪው ዓለም አማኞች እንዲያስቡ የምትሰብኩትን እስቲ ለአንድ ጊዜ ራሳችሁ ኑሩበትና ይህንን የሕዝብ እሮሮ በማሳወቅ ከዚህ ምድር አስተሳሰብ የላቃችሁ መሆናችሁን አሳዩ፡፡ መስዋዕትነት የሚያስከፍል ከሆነም ምዕመኖቻችሁን እንዳስተማራችሁት እናንተም ለተግባራዊነቱ በዝግጅት ቁሙ!
እሁድ በሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ የአክራሪነትና ጽንፈኝነትን ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብቶች ረገጣንም አብራችሁ ተቃወሙ፤ ይህን የማይገኝ ዕድል ተጠቀሙና ድምጻቸው የታፈነውን ዜጎች ድምጽ አሰሙ፡፡
የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ መግለጫ በእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ሕዝቡ አክራሪዎችንና ጽንፈኞችን “እረፉ” በማለት ያውግዛቸው ብሎ እንዳወጀው ሁሉ፣ በዚያውም ህወሃትንና ኢህአዴግን እንዲሁም ተላላኪዎቻቸውንና ጉዳይ አስፈጻሚ አሽከሮቻቸውን “የእስካሁኑ ይበቃችኋል፤ እረፉ፤ በነጻ አውጪ ስም አገርና ወገን ላይ የምታደርሱትን ግፍ አቁሙ” በሏቸው። እስኪ የሃይማኖት አባትነት ወግ አሳዩን!! እስኪ በታሪክ የሚዘከር ተግባር ፈጽሙ። ከኮሚኒስቶች ጉያና ትዕዛዝ ውጡና በምትሰብኩት አምላክ ፊት ስትቆሙ የማታፍሩ ሁኑ። የ”አምላካችሁ ባሮች” ቅድሚያ ለማን እንደምትሰጡ እወቁ። በሰማያዊውም ሆነ በምድራዊው ዓለም በቁም “መተፋትም” አለና!!

ተመስገን እላለሁም ፣ አልልምም !


temesgen


በሰላም አውሎ ላሳደረኝ ፈጣሪ ስተኛም ሆነ ስነሳ ” ተመስገን ፈጣሪየ! ” የምትለዋን ምስጋና ከማቅረብ ተቆጥቤ አላውቅም ። ቸርነቱ የማያልቅበት ፈጣሪ አምላኬ አጉድሎብኝ አያውቅም! ጤና ስጠኝ ስለው ጤናውን ፣ ጥበብ መላ ላጣሁለት መላ ስጠኝ ስለው መላ ብልሃቱን ፣ ጉልበቴን አበርታው ስለው ብርታቱን ፣ ቅን ልቦና ስጠኝ ስለው ርህራሔውን እና የፈለግኩትን ሁሉ አያጓድልብኝም! እናም ዘወትር ተመስገን እለዋለሁ !
ገና ከአልጋየ ሳልነሳ ከአፊ ውስጥ አንድ ቃል ይመላለሳል ፣ ቃሉ ወደ አረፍተ ነገር ሺር በሎ ተቀየረ ! በጨለማ የማያይ አይኔን ወደ ድቅድቁ ጨለማ የመኝታ ክፍል ጣራ አፍጥጦ በምናብ አነበንበዋለሁ … በጀርባየ ተኝቸ ወደ ጣራ ካፈጠጥኩበት ወደ ጎን ግልበጥ እልና እጆቸን ጭንቅላቴ ስር ወሸቅ አድርጌ ከአፊ የማወጣውን አረፍተ ነገር ደጋገምኩ ” ተመስገን ተመስገን ተመስገን አልልም !” … እል ይዣለሁ!
የጋዜጠኛ ተመስገን ድብደባ ሰሞነኛው መነጋገሪያ …
ለምጀዋለሁና እንደቀሩት ቀናት በአርቡ የሳውዲ የእረፍት ቀን መዳረሻ በድቅድቁ ጨለማ ሌሊት ላይ ነቅቸ የሚነበብ የሚታይ ካለ ዳሰስ ዳሰስ አደረግኩ። የሚሞነጫጨር የማለዳ ወግ መነሻ የሚሆነኝ ጉዳይ ከአንድ የፊስ ቡክ ወዳጀ በኩል በውስጥ መልዕክት ደርሶኛል ። ይህው መልዕክት የደረሰኝ የኢቲቪ ዜና አንባቢ ጋዜጠኛ ተመስገን በየነ ተደበደበ በተባለ ቅጽበት ነበር ። መረጃው ሲሰራጭ እኔም በጅዳ ቆንስል ከድብደባ ያላነሰ ግፍ ተፈጽሞብኝ ነበር ። በደል እየተፈጸማቸው ፡ እየታመሙና እያበዱ ስላሉ ወገኖቸ ጉዳይ መፍትሔ ፍለጋና ምክክር ስብሰባ “አትሰበሰብም ፣አትመክርም!” ተብየ የታገድኩበት አጋጣሚ ነበርና የሰማሁትም የሆነብኝም አበሳጭቶኝ አዘንኩ ! የቆንስሉን እገዳ መረጃ በጻፈ እጀ በተመስገን ላይ የተቃጣውን ድብደባ የተሰማኝን ስሜት ሳላንዛዛ በተሰራጨው መረጃ ስር አስተያየቴን እንዲህ በማለት አስቀመጥኩ ” እርምጃው በማንም ይወሰድ በማን ፣ አላስደሰተኝም! ” በማለት …
ይህ ከሆነ በኋላ በውስጥ መልዕክት መቀበያ ሳጥኔ ብዙ የተቃውሞና ድጋፍ መልዕክት ደረሰኝ! የለመድኩት ነበርና ሁሉንም በጥንቃቄ እያነበብኩ አለፍኩት ። ከትናነት በስቲያ ከደረሱኝ መካከል ከላይ የጠቀስኩት መልዕክት እንዲህ ይላል” ሰላም ነብዩ በኢባሲ የደረሰብህ በጣም አሳዝኖኛል አሁን የሰማሁት መረጃክ ስለተመስገን መደብ እጅግ አዝኛለው አንተም ሀቅን እንናገር ስላልክ ከኢባሲክ ከተከለከልክ እደተመስገን አንዳያደርጉህ ተጠንቀቅ ” ይላል መልስ የሚያሻው አስተያየት!… እርግጥ ነው ባለኝ ትርፍ ሰአት መረጃ በማቀበሌ እና ሃሳቤን ባንሸራሸርኩ ፣ ከተቃዋሚ ጽንፈኛ ተብየ እስከ መንግስት ጽንፈኛ ደጋፊዎች የሚሰነዘርብኝ የማስፈራሪያ የዛቻና የ”እንገድልሃለን !” ፉከራ እኔ ለምጀው ባልፍም ብዙዎቹን ያሳስባቸዋል! ከእኒህ ወዳጆቸ መካከል ምክር ለለገሱኝ ወዳጀ ምስጋና ካቀረብኩ በኋላ በሰጠሁት ምላሽ ከጋጠዎጦች ባልተናነሰ እኔንም ሆነ የዜጎች መብት መገፈፍ ያገባናል የምንልን ወገኖች መብት የማያከብሩ ፣ ሰላም የነሱን ፣ መብት ማስከበሩ ቀርቶ የሚገፉን የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ናቸው የሚል መልሴን ሰጠሁ … በዚህ ዙሪያና በተመስገን በምንም ሚዛን ተቀባይነት የሌለው ድብደባ ዙሪያ የማለዳ ወግ አምዴ ልሞነጫጭር ባስብም ድካም የመጻፍ ፍላጎቴን ጎድቶት እንቢ አለኝ !
ዛሬ ሌሊት ….
በድቅድቁ ጨለማ በነቃሁ ሰአት ይህንን እያሰላሰልኩ መረጃዎችን መፈተሽ ይዣለሁ … በኢቲቪ ጋዜጠኛ በተመስገን በየነ ላይ ደረሰበት የተባለውን ድብደባ ተከትሎ የቅርብ ወዳጆቹ ፣ አድናቂዎቹና የኢቲቪ ጋዜጠኞች የሰጧቸው አስተያየቶች ተበራክተዋል ። ይህን ሁሉ ቃኝቸ ተመልሸ ገደም እንደልኩ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ አለ !
በማለዳው ግን ተነሳሁ … እናም ሰሞነኛው ተመስገን አልለቀቀኝም “ተመስገን አልልም ” እያስባለ ያሚያንሰላስለኝን ሃሳብ ከተጋደምኩበት ቀና ብየ መጻፍ ጀመርኩ ! ግጥም ሆነ …
ተመስገን ማለቱ ክፉ ነው ባልልም
ስጋቱ ተገፎ ስላላየሁ ዛሬም
ተመስገን ተመስገን ተመስገን አልልም !
የቱ ነው እውነቱ የዝብርቅርቁ አለም ?
ሰው ያለ ሃጢያቱ ከቶ አይወነጀልም ?
ወህኒ አይወረወር አይደበደብም ?
ፍትህን ተነፍጎ ከቶ አይገደለም ?
ለዚህ የሚያስደስት ዛሬ መልስ የለኝም!
ስል በስሜት መነጫጨርሙ … ቀጠልኩ …
ተመስገን ተመስገን ተመስገን ባልልም
ድብደባ ግድያን ፍጹም አልደግፍም !
… አልኩና አንገቴን አቅንቸ በኩራት ተሞልቸ ተመስገን ተመስገን አልልም ስል የቅርብ ሩቁን ፣ ግራ ቀኙን የነፍስ ማጥፋት እኩይ ምግባር አጠየቅኩ … ምክርም መክሬ ፍላጎት ምኞቴን እንካችሁ አልኩ …
በጠራራ ጸሃይ በሚንቀለቀለው
“ኢትዮጵያዊ ክብሬ” ስላለ ቢከፋው
ቆፍጣናውን መምህር ያን አሰፋ ማሩን ከቶ ማን ገደለው ?
ያንን ጋዜጠኛ ተስፋየ ታደሰን ማነው ያጋደመው?
በምሽት ጨረቃ ድምቅ ፍንትው ባለው ?
ጀኔራል ሃየሎም ማነው የደፈረው ?
በጥይቱ ባሩድ ከእኛ የለያየው ?
ማለዳው ጸሃይ ጸጥ ረጭ ባለው
የደህንነቱን ሰው ክንፈን ገብረ ማን አጠፋው ?
አመት እንኳ ቀርቶ መንፈቅ ባልደፈነው
ወሎ ሰማይ ስር ረግቶ በሚታየው
በምሽት ጨረቃ ሸሁን በጭካኔ ማነው ገዳያቸው?
አልኩና ውጋት ህመም የምለውን ፣ ምክር ዝክር ይሆናል የምለውን ገጣጠምኩትን ! ከሙሉው ግጥም ግጥሜን በቀነጨብኳት ስንኝ ውጌን ልቋጭ …
ችግሩን ለማጥፋት ከሆነ የምናልም
ለድብደባ ፣ እስራት ፣ ለተበራከተው የሰው ልጅ ግድያም
መፍትሄ ፍለጋ ከሆነ ምንሻው እንዳይደጋገም
“ምንድነው ሰበቡ ” ብሎ ማጠየቁ ሳይጠቅም አይቀርም !
ህግ ባለበት ሃገር ግፉ ተበራክቶ ፣ ልዩነቱ ከሰፋ
ችግሩን እንመርምር ያለ መቁረጥ ተስፋ
ፍርድን አናዛባ ፣ ግፉንም አናብዛ ሰውን አናስከፋ
ሃገር አናሰድብ ሰሟን አናስጠፋ
ሰላምን አናውርድ ልዩነቱ ይጥበብ እንድንኖር በተስፋ
ይህን ሳናሟላ ፣ በልዩነት ሰበብ ሰውን አንበድለው
ሰው ከሃገሩ በምድሩ ክብሩን አናሳጣው
መብት በጠየቀ አሸባሪ አንበለው !
ይህን ካደረግ ሰውን ካከበርነው
ማግለልን ካቆምን በዘር በቀለሙ ብሎም በእሳቤው
ያኔ ነው ቀናችን ድብደባ ግድያ የሚጠፋውማ
ያኔ ነው ቀናችን ተመስገን መባያው
እልል የሚባለው ሰለም የሚኖረው!
ጥላቻን አጥፍተን ፣በእርቅ በይቅርታ ደምቀን ስንታይ ነው
ተመስገን ፣ ተመስገን ፣ ተመስገን የምንለው !
ከእንቅልፍ አንቅቶ ያብተከተከኝን ሙሉ የስንኝ ቋጠሮ በወግ አሰናድቸ እስካቀርበው ለዛሬ የማለዳ ወግ ይህችን ታክል ካወጋን አይከፋም ! ለእናንተ ለወዳጆቸ መልካም ቀንን ተመኝቸ አንድየን አመስግኘ እንለያይ ! ፈጣሪ ሆይ አንተን አልፋና ኦሜጋ እናመሰግንሃለን ! ተመስገን !
ሰላም
ነቢዩ ሲራክ
ከወይና ደጋው ሳውዲ በአንዷ ከተማ

ከስልጣን የተነሳው የደህንነት ሹም፣ እስር ቤት ተወረወረ!!

(ኢ.ኤም.ኤፍ) የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በህይወት በነበረበት ወቅት፤ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ምክትል የደህንነት ሹም ሆኖ ይሰራ ነበር። ወልደስላሴ የህወሃት ታጋይ የነበረ ሲሆን፤ በትግላቸው ወቅት… ወንድ እና ሴት ታጋዮችን “ፍቅር ስትሰሩ ተገኝታችኋል” በማለት ብዙዎችን በመረሸን  ይታወቃል። ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ፤ የመለስ ዜናዊ ክርስትና እናት ልጅ የሆነው፤ ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ የቤተ መንግስቱ ዋና ኃላፊ፣  ወልደስላሴ ደግሞ የቀድሞው ደህንነት ሃላፊ ክንፈ ገብረመድህን ረዳት ሆኖ እንዲሰራ ተደርጎ ነበር።
….
አሁን ጌታቸው አሰፋ በፌዴራል መንግስት ደረጃ ያለውን ስልጣን እያደራጀ የመጣ ይመስላል። ከስር ሆኖ የሚያዘው ወልደስላሴ እስር ቤት ገብቷል። ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ ከቤተ መንግስት እየደወለ ት እዛዝ እና መመሪያ አይሰጠውም። ጌታቸው አሰፋ አሁን ነጻ ሰው ነው። ይህ ነጻነቱ የሚቆየው ግን ቀጣዩ የህወሃት/ኢህአዴግ ስብሰባ እስከሚደርስ ይሆናል። እስከዚያው ድረስ ግን እነ ኢሳያስን በአይነ ቁራኛ መጠበቅ አለበት። አዜብ መስፍን ከኢፈርት ስልጣንዋ ወርዳ፤ ስለመለስ ፋውንዴሽን ብቻ እያወራች እንድትኖር እድል ሰጥቷታል። ቢሆንም ግን ህወሃት ውስጥ ሌሎች የጌታቸው አሰፋ ጠላቶች አሉ። እስከሚቀጥለው የህወሃት ስብሰባ እና ሌላ ውጥንቅጥ ድረስ፤ ድራማውን ከዳር ሆነን እናያለን።

Thursday, August 29, 2013

ESAT Daliy News Amsterdam Aug 28 2013 Ethiopia


ሰማያዊ ፓርቲ በሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ላይ ተቃውሞ አቀረበ

ፓርቲው ከ33ቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ ጋር ተለያየ




በግንቦት ወር 2005 ዓ.ም. የመጀመሪያውን የተቃውሞ ሠልፍ ያካሄደው ሰማያዊ ፓርቲ፣ በመጪው እሑድ በሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሠልፍ ላይ ተቃውሞ አቀረበ፡፡
ሁለተኛውንና በርካታ ሰዎች እንዳሚሳተፉበት ሲገልጽ የከረመውን ሰላማዊ ሠልፍ የሚያካሄደው ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደነበር ፓርቲው አስታውቆ፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በተደራቢነት በዕለቱ ሠልፍ እንደሚያደርግ ያስተላለፈው ጥሪ ትክክል አይደለም ብሏል፡፡
yiliqalየሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ያስተላለፈውን፣ ‹‹አክራሪነትና ጽንፈኝነትን እናውግዝ›› የሚል የሠልፍ ጥሪ የተቃወመው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ከአንድ ወር በላይ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ሲያስተዋውቅና ጥሪ ሲያደርግ መክረሙን ገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርግ ቀድሞ ማሳወቅ ለሚገባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በደብዳቤ ማስገባቱን፣ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌታሁን ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
‹‹እኛ በጠራነው ሰላማዊ ሠልፍ ላይ ሌላ ሠልፍ እንዲጠራ መፍቀድ መንግሥት በትንሹ የከፈተውን ቀዳዳ ለመዝጋት ፈልጐ ነው፤›› የሚሉት ሊቀመንበሩ፣ በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ሰላማዊ ሠልፍ መጥራት ለምን እንዳስፈለገ ግልጽ እንዳልሆነላቸውና መንግሥት የጉባዔውን ሠልፍ እንዲሰርዝ ጥያቄ ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት የተጠሩ ሁለት የተለያዩ ዓላማና ይዘት ያላቸው ሰላማዊ ሠልፈኞች ሲገናኝ ወደ ግጭት ሊያመሩ ስለሚችል፣ መንግሥት ፓርቲው ቀድሞ መጥራቱንና ለሚመለከተው አካል ማሳወቁን በመገንዘብ ዕርምጃ እንዲወስድ፣ ፓርቲው ነሐሴ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. አስቸኳይ ስብሰባ በማድረግ መግለጫ ማውጣቱን ኢንጂነር ይልቃል ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል ሰማያዊ ፓርቲ ለበርካታ ወራት አንድነት ፓርቲን ጨምሮ ከ33 ፓርቲዎች ስብስብ ጋር ኅብረት ፈጥሮ ሲሠራ የቆየ ቢሆንም፣ ሰሞኑን ከስብስቡ እንዲወጣ መደረጉ ተሰምቷል፡፡ ከ33ቱ ፓርቲዎች ስብስብ መገለሉን በሚመለከት አስተያየታቸውን ለሪፖርተር የሰጡት ኢንጂነር ይልቃል፣ ‹‹የሚያግባባን ነገር ሲገኝ በጋራ ሆነን ለመሥራት ተስማማን እንጂ፣ ማንም ተባራሪና አባራሪ የለም፡፡ መሰብሰባችን በስምምነት እንጂ የሕግ ድጋፍ ኖሮት የተደረገ ስምምነት አይደለም፤›› ብለዋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሲሰጡ፣ ‹‹ለኢትዮጵያ ሕዝብና ፖለቲካ የሚመጥን የፖለቲካ ፓርቲ አለ ብለን አናምንም፤›› ማለታቸውና ሰማያዊ ፓርቲ እየጣረ ያለው ክፍተቱን ለመሙላት መሆኑን መናገራቸው ሌሎቹን ማስከፋቱ ይነገራል፡፡
የ33 ፓርቲዎች ስብስብ፣ ‹‹እንዴት እንደሌለን እንቆጠራለን?›› የሚል ጥያቄ አንስቶ እንደነበር መስማታቸውን የተናገሩት ሊቀመንበሩ፣ ለምን እንደተናገሩ ጠርተው ሳያናግራቸው ስንቶቹ ተሰብስበውና በስንት ድምፅ ወስነው አብረው መቀጠል እንደማይችሉ ሳይገለጽላቸው ስለመለያየት ማውራት፣ ለእሳቸው የልጆች ጨዋታ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ‹‹እኛ ከወጣን ከ33 ፓርቲዎች ስብስብ ውስጥ ሰው የሚያውቀውና ስሙ የሚታወቅ ፓርቲ ይኖራል እንዴ?›› ሲሉም ጠይቀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እውነትን በአደባባይ መናገር ስላልተለመደ እንጂ ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹ለምን ተናገረ?›› በሚል አብሮ አለመሥራትን ማወጅ፣ ሕዝቡን ተስፋ ከማስቆረጥ ያለፈ ጥቅም እንደሌለው ኢንጂነር ይልቃል ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

በመስቀል አደባባይ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ እያወዛገበ ነው

‘‘ቀድመን ሰልፍ የጠራነው እኛ ነን’’ ሰማያዊ ፓርቲ
‘‘የቀደምነው እኛ ነን’’ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ
‘‘ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ የሚያካሂደው ሰልፍ ህገ-ወጥ ነው’’ የአ.አ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍ፣ የስብሰባና የማኀበራት ፈቃድ ጽ/ቤት
በመጪው እሁድ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በማወዛገብ ላይ ነው። ቀደም ሲል ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ ሰልፍ እንደሚያካሂድ ቢያስታውቅም፤ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት በበኩሉ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው መግለጫ በተመሳሳይ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ይፋ አድርጓል።
ይህንን ተከትሎ በፓርቲው እና በአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መካከል የቀደምኩት እኔ ነኝ በማለት በመወዛገብ ላይ ሲሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የስብሰባ ማሳወቂያ ጽ/ቤት በበኩሉ፤ ሰልፍ እንደሚካሄድ ቀድመው ያሳወቁት የሃይማኖት ተቋማቱ በመሆኑ በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ የሚካሄድ ከሆነ ህገወጥ ነው ብሏል።
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ጉዳዩን በማስመልከት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደተናገሩት ፓርቲው ከወር በፊት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂድ በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ ማድረጉን በማስታወስ ፓርቲያቸው ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ በቅድሚያ ጥያቄ ማቅረቡን ተናግረዋል።semayawiparty
እንደ ፓርቲው ሊቀመንበር ገለፃ ፓርቲው አስቀድሞ ቀን መቁረጡንና በተባለውም ቀን ሰልፉን ለማካሄድ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍ፣ ስብሰባና የማኀበራት ፈቃድ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ ጭምር የማሳወቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ተናግረዋል። በወቅቱ ጽ/ቤቱ ደብዳቤውን ለመቀበል ፍላጎት ባያሳይም በህጉ መሠረት ማሳወቅ ብቻ በቂ በመሆኑ ደብዳቤውን በጽ/ቤቱ አስቀምጠው መመለሳቸውንና በኋላም ጽ/ቤቱ በፖስታ ቤት በኩል በሬኮማንዴ ለፓርቲው ሰልፍ የት እንደሚያካሂድ፣ ምን ያህል ሰው እንደሚሳተፍ ማብራሪያ በመጠየቁ ፓርቲው በበኩሉ ለጽ/ቤቱ ወዲያውኑ ምላሽ መስጠቱን ተናግረዋል። ሆኖም ጽ/ቤቱ በህጉ መሠረት በ48 ሰዓታት ውስጥ ምላሽ መስጠት ሲገባው ዝምታን በመምረጡ፣ ዝምታው ደግሞ ሰልፉ እንደተፈቀደ የሚጠቁም በመሆኑ በሰልፉ ዙሪያ ፓርቲው ዝግጅት ማድረግ መቀጠሉን አስታውቀዋል።
ከጽ/ቤቱ እስካሁን (ነሐሴ 21 ቀን 2005 ዓ.ም) ምላሽ ባለመገኘቱም ፓርቲው በዕለቱ የጠራውን ሰለማዊ ሰልፍ ከማካሄድ ወደኋላ የሚመልሰው የህግ መሠረት ባለመኖሩ ሰልፉን እንደሚያካሂድ አስታውቀዋል። ፓርቲው ከነገ ሐሙስ ጀምሮ በአምስት ተሽከርካሪዎች በአስሩም ክፍለ ከተማ መጠነ ሰፊ ቅስቀሳ ለማካሄድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በመላ ከተማዋና በአካባቢዋም በመቶ ሺህ የሚቆጠር ወረቀት እንደሚበተንና ሰልፉም ካለፈው ሰልፍ ልምድ በማግኘት ከፍተኛ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ይሁን እንጂ ባለፈው ሰኞ (ነሐሴ 20 ቀን 2005) በዋና ጽ/ቤቱ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ያስታወቀው የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የቦርድ ሰብሳቢ ርዕሰ ደብር በሪሁን አርአያ በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት በዕለቱ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን እንደማያውቁና ጽ/ቤታቸውም ቀደም ብሎ ሰልፉን ሲያዘጋጅ መቆየቱን ተናግረዋል።
ምንም እንኳ ርዕሰ ደብር በሪሁን አርአያ የሃይማኖት ጽ/ቤቱ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ያሳወቀበትን ቀን ለመናገር ባይፈልጉም በዕለቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በሰጡበት ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ በ10ሩም ክፍለ ከተሞች እና በ116 ወረዳዎች በተካሄደ ሕዝባዊ የሰላም ኮንፈረንስ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ ጋር በመተባበር በከተማ ደረጃ ነሐሴ 15 እና 16 ቀን 2005 ዓ.ም በተዘጋጀው ማጠቃለያ የሰላም ኮንፈረንስ የተለያዩ ሃይማኖት መሪዎችና ተከታዮቻቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተማችን እየታየ ያለው የአክራሪነትና የፅንፈኝነት እንቅስቃሴ የሀገራችንን ልማት የሚያውክ፣ በሰላም አብሮ የመኖር እሴቶቻችንን የሚያናጋ እና የሃይማኖት መልክ የሌለው የጥፋት እንቅስቃሴ ከመሆኑም በላይ በሕገ-መንግስታችን የተደነገገውን የኃይማኖት እኩልነትና የእምነት ነፃነት የሚፃረር ስለሆነ በሰላማዊ ሰልፍ ተቃውሞአችንን እንግለፅ በማለት የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች መንግስት ሁኔታዎችን እንዲያመቻች፣ የኃይማኖት ተቋማት የጋራ ጉባኤም እንዲያስተባብር መወሰኑን ተናግረዋል።
ከዚህ መግለጫ መረዳት የሚቻለው የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት ሰልፉን ለማካሄድ ጥያቄ ያቀረበው ነሐሴ 15 እና 16 በኋላ መሆኑን መረዳት ይቻላል። በአንፃሩ ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 16 ቀን 2005 ዓ.ም የማሳወቂያ ደብዳቤ ማስገባቱን አመልክቷል።
የአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማርቆስ ብዙነህ ጉዳዩን በተመለከተ የእውቅና ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚ የነበሩት የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት በመሆናቸው ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ ሰልፍ እንዲያካሂድ አልተፈቀደለትም ብለዋል። ሰልፉ የሚካሄድ ከሆነም ህገወጥ ነው ከማለት ውጪ ሁለቱም ወገኖች የሰላማዊ ሰልፍ ያሳወቁበትን ቀን እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን ከመናገር ተቆጥበዋል። (ምንጭ: ሰንደቅ)

የእኛ “መንግስት” (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)


“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡Journalist Temasegan Dasaleg
እናም የስርዓቱን የአስተዳደር ዘይቤ ያለፍርሃት አደባባይ ካዋልነው የቀድሞ ገዥዎቻችን የተጓዙበትን ጎዳና እየተከተለ መሆኑን ለመተንተን የምሁራንን ጥናት መጠበቅ ግድ አይለም፤ ምክንያቱም ለዓመታት የተመለከትነው እውነታ የሚነግረን የአመራሩን እና በዙሪያው የሠፈሩ የጥቅም ተጋሪ ግለሰቦችን ብልፅግና ታሳቢ ያደረገ፣ ከታግሎ መጣል ህግ የተቀዳ፣ የራስ ሀገርንና የራስ ሕዝብን በምርኮ ያስገበረ ፖለቲካ መንበሩን ነው፤ ገብር፣ ገብር፣ ገብር…!!
ዛሬ መንገድ ዳር ረሀብ አዙሮ የጣለው ወንድምህ ስቃይ እንደ ጥላ የሚከተልህ፤ ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ በጠኔ ተሸንፈው መመልከቱ የሰርክ አሳዛኝ ክስተት የሆነብህ ከሰው ሰራሽ ችጋር፣ ከሰው ሰራሽ የቀዬ ፍንቀላ፣ ከሰው ሰራሽ እርዛት… የመነጨ መርገምት እንጂ የሰማይ ቁጣ አይምሰልህ፤ እመነኝ መለስም ሆነ ተተኪዎቹ ስኬት አድርገው የሚሰብኩትም ይህንን ነው፤ ‹ሀገር አቀናን!› የሚሉትም ይህንን ነው፤ ሰሞኑን የሚያሰለቹህ ተረኛ ምሁራንም ‹‹ትምህርትና ጤናን በተመለከተ መለስ ‹እልል› የሚያስብል ሥራ ሰርቷል›› የሚሉህ ጣራና ግድግዳ እየቆጠሩ ነው፤ ይህ አይነቱ መደዴ ሙገሳም ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ሪፖርት ለማዘጋጀት ከሚረዳ ቁጥር የዘለለ አበርክቶ አንደማይኖረው አትዘንጋ፡፡
እውነት እውነት እልሀለሁ፡- ይህ የሆነበት ብቸኛው ምክንያት መንግስት በስልጣን ላይ ስለሚቆይበትመንገድ ብቻ መጨነቅን ግዴታው በማድረጉ ነው፤ ይህንን ለመረዳትም እያገባደድን ባለው ክረምት የመንግስት ትኩረት በምን ላይ አንደሆነ የሚያሳይ ማስረጃን ጨርፌ ላሳይህ፡፡
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የእስልምና እምነት ተከታዮች መንግስት በሃይማኖታቸው ጣልቃ መግባቱን በመቃወም እና የታሰሩ ኮሚቴዎቻቸው እንዲፈቱ በመጠየቅ እያደረጉ ያለውን ትግል በሰላማዊ መንገድ አጠንክረው ሲቀጥሉ፤በተቃራኒው ‹‹ፀጥታ አስከባሪዎች›› አንዳንዴ በጥይት፣ አንዳንዴ በአስለቃሽ ጢስ፣ አንዳንዴ በማጋዝ…ምላሽ ሲሰጡ…
በርግጥ መንግስት ከኃይል እርምጃው በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎችን (በምን አግባብቶ ወይም በምን አስፈራርቶ እንደሆነ ባይታወቅም) ወደ አደባባይ በማስወጣት መብት ጠያቂዎቹን ከ‹‹አክራሪ››ነት እና ‹‹ወሃቢዝም››ነት ጋር አያይዘው የውግዘት በረዶ እንዲያዘንቡባቸው እያደረገ ነው፡፡ ኢቲቪም ይህንን ኩነት እየተከታተለ ማራገቡን ቀጥሎበታል፤ ‹‹የቲፒ ከተማ ነዋሪዎች ‹አክራሪዎችን አወገዙ››፤ ‹‹በደቡብ ወሎ ኩታ በር ዞን አንድነት ፓርቲ ህገ-ወጥ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰልፍ ተካሄደ››፤ ‹‹የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ‹የሼሁ ግድያ ድራማ አይደለም› አሉ፣ ‹የሼህ ኑሩ ኢልም ነው፣ የአሸባሪዎች ብር ነውም›ብለዋል››፤‹‹የመርሀቤቴ ነዋሪዎች ፅንፈኞችን በመቃወም የአቋም መግለጫ አወጡ››፤…
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- አንድነት ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የ‹‹ፀረ-ሽብር ሕጉ›› እንዲሰረዝና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ እና የአዳራሽ ስብሰባዎችን እያካሄደ ነው፤ መንግስትም አንዳንዴ የአፀፋ የድጋፍ ሰልፍ ሲያካሄድ፤አንዳንዴ የአዳራሽ ስብሰባዎች ከመካሄዳቸው አስቀድሞ ‹መጋኛ› ሲሆንባቸው፤ አንዳንዴም የአስተባባሪዎቹን መኪና ጎማ ሲያፈነዳ፤ አንዳንዴም አዳራሽ ከልክሎ ሲያደናቅፋቸው… መዋሉ ፋታ የነሳው ይመስላል፤ በወላይታ የተጠራውን የአዳራሽ ስብሰባም ‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውልድ ቦታ እንዴት ተደርጎ!›› ያሉ ካድሬዎች የአንድነት ሰዎችን አዋክበው ስብሰባውን አክሽፈዋል፤
ክረምቱእንዲህእየተገባደደነው፡-ገዥው ፓርቲ ‹የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ አንደኛ ሙት ዓመት አከብራለሁ› በሚል መላ ኢትዮጵያን ችግኝ መትከያ፣ መላ ዜጎቿን ደግሞ ወደ አርሶ አደርነት በአስማት የቀየራቸው አስመስሏቸዋል፤ቴሊቪዥንና ራዲዮንም አስፈላጊነታቸው በየመንደሩ ችግኝ መተከሉን እየተከታተሉ መዘገብ ብቻ እስኪመስል ድረስ እንዲህ ሲሉ ጀምበር ወጥታ ትጠልቃለች፡- ‹‹የላይ አርማጮህ ነዋሪዎች ችግኝ ተከሉ››፣ ‹‹በመቀሌ ከተማ ‹ዘመቻ መለስ› በሚል የችግኝ ተከላ ተካሄደ››፣ ‹‹አቃቂ ኮረብታ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ችግኝ በኦሮሚያ ፌደራል ፖሊስ አባላት ተተከለ፤ ቦታውም ‹መለስዜናዊ ኮረብታ› ተብሎ ተሰይሟል››፣ ‹‹በምዕራብ ሀረርጌ አስራ ሰባት ሚሊዮን፣ በወልበራ አስራ አራት ሚሊዮን ችግኝተ ተክሏል››፣ ‹‹በመንዝ ላሎ ወረዳ ተቆጥሮ የማያልቅ ችግኝ ተከላ ተደርጓል››፣ ‹‹የብአዴን አመራርና ካድሬ በባህር ዳር ከተማ በቢሊዮን የሚቆጠር ችግኝ ተከሉ፤ በፕሮግራሙ ላይ ጓድ አዲሱ ለገሰ ‹ችግኝ የምንተክለው አገሪቱ በአረንጓዴው ልማት በአለማችን ማግኘት የሚገባትን ቦታ እንድታገኝ ለማድረግ ነው› ሲል፣ ጓድ በረከት ስምዖን ደግሞ ‹ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአለማችን በአንድ ጊዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ችግኝ እየተከሉ ያሉባት ብቸኛ ሀገር ናት› ብሏል››፤‹‹ዝክረ መለስ 1ኛ ዓመት መታሰቢያን ምክንያት በማድረግ ከሐምሌ አስራ አምስት ቀን ጀምሮ ሁሉም ቀበሌዎች በስሙ ‹ፓርክ› ሰይመው ችግኝ ተከላ እያካሄዱ›› መሆኑን ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ መግለፁን የአማራ ክልል ብዙሃን መገናኛ ዘግቧል፤ ‹‹በወልቂጤ ከተማ በተደረገው ችግኝ ተከላ ላይም አንዲት ወጣት ‹መለስ ለሴቶች የተለየ አመለካከት ነበረው›› ማለቷም በዘገባው ተጠቅሷል፤ …ማን ነበር የመለስ ራዕይ ‹ችግኝ መትከል ነው› ያለው? …ኢህአዴግ ይሆን?
ከዚሁ ጎን ለጎን (አሁንም ሙት ዓመቱን ለማሰብ) በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የእግር ጉዞ ተደርጓል፣ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓትም ተካሄዷል፤መነሻውን መቀሌ፣ መድረሻውን አዲስ አበባ ያደረገ ‹‹የመለስ ቱር አረንጓዴ ልማት›› የብስክሌት ውድድርም ሊጠናቀቅ ገና አንድ ሳምንት ይቀረዋል፤ በብሄራዊና ሀይማኖታዊ በዓላት ቀንለሃያ አንድ ጊዜ ይሰማ የነበረው የመድፍ ድምፅም፣ የመለስን አንደኛ ሙት ዓመት ለማብሰር ተተኩሷል፤ …በግድ አልቅሱ፣ በግድ ተዝካር አውጡ፣ በግድ ችግኝ ትከሉ፣ በግድ ተወያዩ፣ በግድ አደባባይ ውጡ፣ በግድ የፎቶ ግራፍ ኤግዚቢሽን ጎብኙ፣ በግድ.. ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ሽፈራው ሽጉጤ ከአንድ ሺህ ሰባት መቶ በላይ ለሚሆኑ የዩኒቨርስቲ ከፍተኛ መምህራን ‹የአቅም ግንባታ ስልጠና› እየሰጡ ነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምሁራኖቹን ማሰልጠን ያስፈለገበት ምክንያት ‹‹ብቃት ያለው ምርጥ የተማረ ኃይል ለማፍራት››መሆኑን ቢነግርህ አይግረምህ፤ ይህ ኢትዮጵያ ነውና የዐዋቂነት ማረጋገጫው መማር፣ ማንበብ፣ መመራመር… አይደለም፣ የፖለቲካውን ኃይል መያዝ እንጂ፤ ‹ስልጣን ላለው ሁሉምሚስጥረ-ጥበብይገለፅለታል› እንዲል አብዮታዊ ዲሞክራሲ መለስ ዜናዊም በሁሉም መስክ ‹አስተማሪ› ነበር፤ የህግ ባለሙያዎችን ሰብስቦ የሀገሪቱን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ትርጓሜ ሲተነትን ደጋግመህ ሰምተኸዋል፤ በቀጣዩ ቀን ደግሞ ለግብርና ባለሙያዎች ከውሃ ማቆር እስከ በላብራቶሪ የሚዳቀል ምርጥ ዘር ድረስ ባሉጉዳዮችዙሪያ የሁለት ቀን ማብራሪያ መስጠቱን ታስታውሳለህ፤ እመነኝ ተተኪው ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ነው እያደረገ ያለው፤ የሆነ ሆኖ ኃ/ማርያም ለምሁራኖች ከሙያቸው ጋር ስለተያያዙ ጉዳዮች ጭምር በሰጣቸው ስልጠና ላይ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ነበር ‹‹የኢንዱስትሪዎች በበቂ ሁኔታ አለመኖሩ፣ በክፍል ውስጥ የምናስተምረውን ንድፈ ሃሳብ በተግባር ለማሳየት እንቅፋት ሆኖብናል››፤ በርግጥጠቅላይ ሚንስትሩ‹‹መፍትሄ››ያለውን የተናገረው ብዙም ሳይጨነቅ ‹‹እኔ ኢንዱስትሪን ‹ዲፋይን› የማደርገው ግብርናም ኢንዱስትሪ ነው ብዬ ነው››በማለት ነበር፤…ግና!ይህ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በተጨባጭ አላብራራም፡፡ለምሳሌ ህክምና የሚያጠና ተማሪ በምን መልኩ በሞፈርና ቀንበር የተግባር ልምምድ ማድረግ እንደሚችል፤ወይም ፖለቲካ ሳይንስ የሚያጠና ተማሪ የተግባር ልምምዱን በግብርና ኢንዱስትሪ እንዴት ሊወጣው እንደሚችል? ማለቴ ነው፡፡
ለዓመታት በርካታ ምሁራን ብቃት አልባ ተማሪዎች እንደ ሰማይ ከዋክብት የመብዛታቸው መንስኤን ከትምህርት ፖለሲው ጋር የሚያነፃፅሩበትን ሀቲት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ ባገኘው የሀገር መሪነት ስልጣን ገልብጦ በዩንቨርስቲ ቆይታው መምህራኖቹ የነበሩትንም ጭምር ‹‹አቅም አንሷችኋልና-እገነባችኋለሁ›› ሲል ከመስማት የከፋ እንደ ሀገር ክሽፈት የለም (በነገራችን ላይ ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ ቴውድሮስ አዳህኖም፣ ሶፍያን አህመድ በአጠቃላይ ሁሉም የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አንድ ህንዳዊ ፕሮፌሰር በኢህአዴግ ጽ/ቤት ‹‹ልማታዊ መንግስት›› እንዴት ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ሲተነትንላቸው፣ እነርሱም ደብተርና እስክርቢቶ ይዘው በንቃት ሲከታተሉ የቴሌቪዥ ዋና ዜና ሆኖ የቀረበበትን ምክንያት ዛሬም ድረስ ሊገለፅልኝ አልቻለም፤ በተለይም ፕሮፈሰር እንድርያስ እሸቴ ‹‹በቃሉ የፀና…›› በሚል ርዕስ መለስን አስመልክቶ በተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ‹‹በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ ልማታዊ ስርዓተ መንግስት ‹ዴሞክራሲያዊ ሊሆን ይችላል፤ መሆንም አለበት› ብሎ በአደባባይ የተከራከረው እኔ እስከማውቀው ድረስ መለስ ነበር›› ማለቱን፣ ተተኪዎቹ ፍልስፍናውን ገና እየተማሩት ከመሆኑ አንፃር ስናየውሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ጉዞው ወዴት ነው? ያስብላል፡፡ …ከቶስ በተማሪ ፖለቲከኛ የሚተዳደር ሕዝብ ከኢትዮጵያ በቀር ወዴት ይኖራል?)
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ በቂ ገንዘብ ስላልተገኘ ተደጋጋሚ የቦንድ ሽያጭ እየተካሄደ ነው፤ አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞችም በካድሬ ባልደረቦቻቸው ጫና በድጋሚ ቦንድ ለመግዛት መወሰናቸው ተሰምቷል፤ በርግጥ ከፍተኛ የኢህአዴግ የአመራር አባላት በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቦንድ እንዲገዙ ለመቀስቀስ የአዘጋጇቸው ስብሰባዎች ‹‹ቅድሚያ የዜጎች መብት ይከበር›› ባሉ የሀገራችን ልጆች መክሸፉም የክረምቱ የመንግስት ዋና ሥራ ነው፤ ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- በነቢብ የኢትዮጵያ፣ በገቢር የገዥው ፓርቲ የግል ንብረት የሆነው ቴሌቪዥን ጣቢያ ባለፉት ሶስት ወር ብቻ ከሃያ በላይ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም›› አሳይቷል (ገና ይቀጥላልም) በርዕሳቸው እንደሚከተለው እንዘርዝራቸው፡- ‹‹ኢፍቲን›› በሶማሊያ ላይ የሚያጠነጥን፣ ‹‹የጥቁር ህዝቦች ልሳን (መለስ በአፍሪካ)››፣ ‹‹ከፓን አፍሪካ እስከ አፍሪካ ህዳሴ›› የጠቅላይ ሚንስትር መለስን ህይወት የሚዳስስ፣ ‹‹ዘመነ አፍሪካ››፣ ‹‹የአፍሪካ ልሳን-መለስ››፣ ‹‹መለስ ማን ነው?››፣ ‹‹ሀገሬ-ቤቴ››፣ ‹‹ባለራዕዮቹ›› ስራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ደውል›› እና ‹‹ደውል 2›› ህገወጥ-የሰዎች ዝውውርን በተመለከተ (በተለያያ ጊዜ የተላለፉ)፣ ‹‹የዲያስፖራ የልማት እንቅስቃሴ››፣ የካርታ ስራ ድርጅትን በተመለከተ፣ ‹‹የጥልቅ አስተሳሰብ ባለቤት›› በፕ/ር እንድርያስ እሸቴ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥን፣ ምድር ባቡር ኮርፕሬሽንን በተመለከተ፣ ‹‹ያልተለመደ ጉብኝት›› የአዲስ አበባ አስተዳደር የአምስት ዓመት የመንግስት ግንባታዎችን በተመለከተ፣ ‹‹ሼህ ኑር ለምን ሞቱ?›› የደሴውን ሼህ ኑር ይማምን ግድያ በተመለከተ፣ ‹‹የተስፋ ስንቅ››፣‹‹በቃሉ የፀና›› በድህረ መለስ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ያልተጠኑ ገፆች›› በመለስ ዜናዊ ህይወት ዙሪያ (በርግጥ በዚህ ፊልም እህቱ ጠላ፣ ወንድሙ አንባሻ በመሸጥ መተዳደራቸውን በምስልም በድምፅም ማቅረቡ ምን የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ እንደሆነ ለማወቅ ግራ ያጋባል፤ …ምናልባት እንዲያ እየዘረፈ ለቤተሰቦቹ ‹ሶልዲን› የማይሰጥ ‹ቆነቋና› ነበር ለማለት ይሆን? ወይስ ለአዜብ መስፍን ‹የወር ቀለባችንን እንቸገራለን› የአንድ ሰሞን ማስተዛዘኛ ምስክር ፍለጋ ነው?
በጥቅሉ ለኢህአዴግ ሕዝብን የማስተዳደር፣ ሀገርን የመምራት መገለጫ ይህ ነው፤ ሌላ አይደለም፤ ግና! ለዘመናት ያልተመለሱ ጥያቄዎቻችን ዛሬም መጮኻቸውን አላቋረጡምና እነሆ እንዲህ ቀጥለዋል፡- ሀገር ማስተዳደር ‹መለስ ጀግና ነበር› እያሉ ማሰልቸት ነውን? የመንግስትስ ስራ (ግዴታ) ምንድር ነው? ሀገሪቱን ‹‹መለስ-ፓርክ›› ወደሚል ስያሜ ከመቀየራችሁ በፊት፣ ለጤፍ ዋጋ አለቅጥ መናር ምክንያቱን ስለምን መመርመር ተሳናቸው? ሀገሪቱን በ‹አራጣ› እንደያዘ ስግብግብ ነጋዴ በሚሊዮኖች ህይወት ላይ የማይሞላ ‹ሳፋ› ደቅኖ አዋጣ፣ ግዛ፣ ክፈል፣ ገብር… እያለ የሚያስጨንቀው ማን ነው? ስለመለስ ‹የሃሳብ ምጡቅነት› መስካሪ ምሁራኖቻችን ለጎዳና ኑሮ የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስንት ሚሊዮን እንደደረሱ እና እልፍ አላፍት ታዳጊዎቻችን በሴተኛ አዳሪነት እንደተሰማሩ የምትነግሩን መቼ ነው?እንዲህ የመሆኑ ምክንያትስ በማን ይሆን? ‹የሁለት ዲጂቱ›ዕድገት ሸክምን የማለዘብ አቅም ከሌለውፋይዳው ምንድር ነው? ‹ሳቅ ትዝታ› ስለሆነባቸው ጎጆዎች ለምን አትነግሩንም? መለስ ‹ያለመለማት› ኢትዮጵያ ወዴት ትሆን? ‹ፖለቲካ› ማለትስ ይህ ነውን? …ነጋ ድራስ ገ/ህይወት እንዳሉት ‹‹…መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡›› የመተራረሚያው ጊዜም በጣም ያለፈ ይመስለኛል፡፡ አገዛዙን ‹እንደ መንግስት› መቀበሉም እንዲሁ፡፡

Wednesday, August 28, 2013

መንግሥት ለተፈጠረው ችግር በአስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ እንጠይቃለን! ሰማያዊ ፓርቲ


ነሃሴ 21/2ዐዐ5 ዓ/ም.
ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
semayawi party's protest call in Addis Ababaፓርቲያችን ሰማያዊ በህገ መንግሥቱ በተደነገገው ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቱን ተጠቅሞ ለመንግሥት ጥያቄዎችን በማቅረብ ግንቦት 25/2ዐዐ5 ዓ/ም. ታላቅ ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ አድርጓል፡፡
መንግሥት ላቀረብናቸው ጥያቄዎች በሦስት ወር ውስጥ መልስ የማይሠጥ ከሆነ በተጠናከረና በተደራጀ መልኩ ጥያቄያችንን በድጋሚ በህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ እንደምናቀርብ በግንቦት 25/2ዐዐ5 ዓ/ም. በተደረገው ሠልፍ ላይ ለህዝብ ቃል በገባነው መሠረት ነሃሴ 26/2ዐዐ5 ዓ/ም. በድጋሚ ሰልፍ ጠርተን አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረግን መሆኑን ለህዝብ በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች ገልፀናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለሰልፉ በሰላም መጠናቀቅ አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግልን አዋጁ በሚጠይቀው መሠረት ለአዲስ አበባ መስተዳድር ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሰወቂያ ክፍል ጉዳዩን እንዲያውቀው አድርገናል፡፡
ይሁን እንጂ ፓርቲያችን ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ በጠራበት ግዜና ቦታ ላይ በሌላ አካል ሰልፉ መጠራቱን በትናንትናው ዕለት ነሀሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም በመንግሥት ቴሌቪዥን ዜና ሰምተናል፡፡ በተጨማሪም ለመንግሥት መዋቅር ዜጐች በዚህ ሰልፍ እንዲወጡ በግድ እንዲፈርሙ እየተደረገ መሆኑን ከአዲስ አበባ ኑዋሪዎች አረጋግጠናል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ አስፈላጊውን የህግ ቅድመ ሁኔታ አሟልቶ ነሐሴ 26/2ዐዐ5 ዓ/ም. በመስቀል አደባባይ የጠራውን ተቃውሞ ሰልፍ ለህዝብ ያሳወቀና አስፈላጊውን ዝግጅት ያጠናቀቀ በመሆኑ ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ በጠራበት ቀንና ሠዓት በሌሎች አካላት የተጠራው ሰልፍ ከመረጃ እጥረት ከሆነ እንዲሠረዝ እየጠየቅን ይህ ካልሆነ ግን ሰማያዊ ፓርቲ በህጋዊ መብቱ የሚያደርገውን የተቃውሞ ሰልፍ ሆን ብሎ ለመረበሽና አቅጣጫውን ለማስቀየስና በዜጐች መካከል ግጭት ለመፍጠር የታቀደ ስለሆነ ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂ መንግሥት መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብና የሚመለከታቸው አካላት እንዲያውቁት በአፅንዖት እንገልፃለን፡፡
በመጨረሻም መንግስት ዜጐችን ያለፈቃዳቸው በማስፈረም ተገደው ሰልፍ እንዲወጡ ማድረግ ህገ ወጥ ስለሆነ፣ በአስቸኳይ እንዲያቆም እንጠይቃለን፡፡

http://ecadforum.com/Amharic/archives/9578/

Tuesday, August 27, 2013

የአንድነቶች ሰላማዊነት ጽናት በባሌ ሮቤ እና በፍቼ ኦሮሚያ!


ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ሰኞ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም.
“አንድነት ፓርቲ ሳይገድል እየሞተ ህገ-መንግስቱን የማስከበር ሰላማዊ ትግሉን አጠንክሮ ዛሬም ወደፊትም ይቀጥላል፡፡” የሚለውን መርሃቸውን አንድነቶች ካስተዋወቁን ከርመዋል። ባለፈው ሳምንት በባሌ ሮቤ እና በፍቼ ኦሮምያ የተተከሉት መረን የለቀቁ አምባገነን አስተዳደሮች እና ደህንነቶች የፈጸሙባቸውን ወደር የለሽ የአንደበት፣ የሳይኮሎጂ እና የአካል ጥቃት በፈገግታ በመቀበል እየሞቱ ሳይገድሉ በሰላማዊ ትግል ህገ-መንግስቱን ለማስከበር ያላቸውን ጽናት ደግመው አሳይተውናል አንድነቶች። አንድነቶች የሚሰብኩትን የሚፈጽሙ መሆናቸውን ኢትዮጵያ እንደገና ባለፈው ሳምንት ተመልክታለች። የባሌ ሮቤ እና የፍቼ አምባገነን አስተዳዳሪዎች እና ደህንነቶች አረመኔነት አሳፋሪ ነበር። በፍጹም የስልጣኔ አየር የነፈሰባቸው አይመስሉም። ዘመናዊ አስተሳሰብ ለአንድ ቀንም የጎበኛቸው አይመስሉም። ይባስ ብሎ የባሌ ሮቢ እና የፍቼ አስተዳዳሪዎች እና ደህንነቶች ከህጋዊ የመንግስት መዋቅር ውጪ ጸረ-ነፃነት ወረበሎች (ቦዘኔዎች) ያደራጁ ይመስላሉ። ይኽ ጉዳይ ጥናት ሊደረገበት ይገባል።udj bale robe
በባሌ ሮቢ ኦሮሚያ ያየነው አፈና እስከአሁን በሰሜን ኢትዮጵያ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ካስተዋልናቸው አፈናዎች ሁሉ ዘግናኝ ነበር። የመቀሌው አፈና የተፈጸመው የድምጽ ማጉያ በመከልከል፣ የመቀስቀሻ በራሪ ወረቀቶችን በመንጠቅ፣ እና አንድነቶችን በማሰር እንደነበር እናስታውሳለን። የባሌ ሮቤ አምባገነኖች ግን ህውሃት በመቀሌ የፈጸመውን በሙሉ ቢፈጽሙም የአንድነቶችን በታጋሽነት እና በጽናት የታነጸ ሰላማዊ ትግል ሊያቆሙት አለመቻላቸውን ሲገነዘቡ ተራ ማስፈራራት ጀመሩ። ሐሙስ ነሃሴ 16 ቀን 2005 ዓ.ም. የአንድነት ፓርቲ ተወካዮች ከባሌ ሮቤ ከተማ ከንቲባ፣ ምክትል ከንቲባ፣ የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊ እና ከከተማው ካቢኔዎች ጋር 3 ሰዓት የፈጀ ውይይት አደረጉ። በዚኽ ውይይት ላይ ነበር የባሌ ሮቢ ባለስልጣኖች “አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን ማድረግ አይችልም፤ እኛ ከፍተኛ የሆነ የፀጥታ ስጋት አለብን፡፡ የቀድሞው ጠ/ሚር አቶ መለስ በፓርላማ እንደተናገሩት በአካባቢያችን የአልቃይዳ ክንፍ አለ” የሚል ማስፈራሪያ አዘል በማሰማት ለሰላማዊ ሰልፉ ትብብር መንፈጋቸውን የገለጹት። እሁድ በተቃረበ ቁጥር የባሌ ሮቤ አምባገነኖች ማስፈራሪያ እና ዛቻ ግለቱ እየጨመረ ቢሄድም አንድነቶችን ሊያስቆም አልቻለም። በዚኽን ጊዜ “እሁድ የገበያ ቀን ስለሆነ ሰልፍ ማድረግ አይቻልም። ሰላማዊ ሰልፍ ከተደረገ ደም ይፈሳል።” ማለት ጀመሩ የባሌ ሮቢ ባለስልጣኖች።
የአንድነቶችን ጽናት፣ ትዕግስት፣ ሰላማዊነት እና ቁርጠኛነት መስበር እና ሰልፉን ማሰናከል አለመቻላቸውን ሲገነዘቡ የባሌ ሮቤ ባለስልጣናት ቅዳሜ ምሽት ለእሁድ አጥቢያ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች እና አባላትን ካረፉበት ሆቴል በግዳጅ አስወጥተው አገቱ። በዚኽን ጊዜ ነበር የቀሩት አንድነቶች ሰላማዊ ሰልፉ እንዳይደረግ የወሰኑት። የመጣው ይምጣ ብሎ ሰልፍ በመውጣት በመሃይም አምባገነኖች የሰለጠነ የሰላም ትግል ሰራዊት ማስመታት ስህተት ነው። ሰላማዊ ሰልፉ እንዲቀር መደረጉ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። በድስፕሊን የታነጹ ሰላማዊ ትግል መሪዎች ገና ዘመቻውን ሲጀምሩ መቼ ማቆም እንዳለባቸውም ጭምረው ያውቃሉ። ይኽ ብስለት ያላቸው ጀግኖች የሚያደርጉት ማፈግፈግ ነው። በዚኽ አይነት ነበር እሁድ ቀን ነሐሴ 19 ቀን 2005 ዓ.ም. በባሌ ሮቤ የታቀደውን የሚሊዮኖችን ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ የታፈነው። በዚኽ አይነት ነበር በባሌ ሮቤ አካባቢ አለ ሲሉን የነበረው ሽብርተኛ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ እራሳቸው የባሌ ሮቤ ባለስልጣኖች መሆናቸውን ያረጋገጡልን። ይኽ ሁሉ ሲፈጸም የባሌ ሮቤ ወጣቶች ከአንድነት ፓርቲ ጎን መቆማቸውን ኢትዮጵያችን ልታውቅ ይገባል።
ፍቼ ሌላዋ ከተማ ናት። የመጀመሪያው ሁለት አባላትን ይዞ ፍቼ የገባው የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ቡድን በፍቼ አስተዳደር እና ደህንነት ካድሬዎች ከፍተኛ ድብደባ ተፈጸመበት። የእጅም የእግርም ጉዳቶች ደርሰባቸው ሁለቱ የዴሞክራሲ ሰራዊቶች። አንድነቶች በደረሰው ጥቃት አልተፈቱም። እንዲያውም ጊዜ ሳያባክኑ አዲስ ቡድን ወደ ፍቼ በመላክ ለነሐሴ 19 ቀን ያቀዱትን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ዘመቻ ለማሳካት ጎንበስ ቀና ማለት ጀመሩ። በዚኽ እርምጃቸው አንድነቶች በማይነቃነቅ ድስፕሊን የታነጹት የሰላማዊ ትግል ሐዋርያት መሆናቸውን ለፍቼ ህዝብ አሳዩ። እየሞቱ ሳይገሉ ህገ መንግስታዊ መብት ለማስከበር ያላቸውን ቁርጠኛነት አንድነቶች አስመሰከሩ። አንድነቶች የሚሉትን የሚፈጽሙ የሰብዓዊ መብቶች አስከባሪ ወታደሮች መሆናቸውን ፍቼዎች በአድናቆት አስተዋሉ። ይኽን ያስተዋሉት የፍቼ ወጣቶች ለአንድነቶች ትብብር መለገስ ጀመሩ። የፍቼ አስተዳደር እና ደህንነቶች ያሰማሩዋቸው ቦዘኔዎች በፍቼ ከተማ የሚገኘውን የአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት ለመስበር ሲሞክሩ የፍቼ ወጣቶች ድርጊቱን በመቃወም ከአንድነቶች ጎን ተሰለፉ። በፍቼ የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍም ቢሆን በአንድነቶች እና በፍቼ ወጣቶች ሰላማዊነት እና ጽናት የተገኘ እንደነበር ኢትዮጵያ በአድናቆት አስተውላለች።
ሶስተኛው የእሁድ ነሃሴ 19 ቀን 2005 የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ዘመቻ እቅድ በአዳማ/ናዝሬት ከተማ ማድረግ እንደነበር ይታወቃል። ይሁን እንጂ የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከአንድነት ፓርቲ ለተጻፈለት ደብዳቤ ነሃሴ 19 በከተማው ስብሰባ መኖሩ እና የኃይል እጥረትም እንዳለበት ጠቅሶ ሰላማዊ ሰልፉን አንድነት ፓርቲ ወደ ጷጉሜ 3 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲያዛውር ጠይቋል። አንድነት ፓርቲም የቀረበለትን ጥያቄ መቀበሉን ገልጿል። የአዳማ/ናዝሬት ከተማ አስተዳደር ህገ መንግስታዊ እውቅና ካለው አንድነት ፓርቲ ጋር በዚኽ አይነት ስልጡን እና ተራማጅ መንገድ ከስስምምነት መድረሱ ከባሌ ሮቤ እና ከፍቼ ከተማዎች አምባገነን አስተዳዳሪዎች ፍጹም የተለየ አድርጎታል። ከሁለቱ ከተሞች አስተዳደሮች የአዳማ ከተማ አስተዳደር የተሻለ መሆኑን ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሁን አልመ አስተውሏል። በዚኽ እርምጃው የአዳማ/ናዝሬት አስተዳደር ሊመሰገን ይገባዋል። ሊኮራም ይገባዋል። ኋላቀሮቹ የባሌ ሮቤ እና የፍቼ አምባገነን አስተዳደሮች ሊያፍሩ ይገባል። የሚያስተዳድሩትን ህዝባቸውን በንቀት አፍነውታል። እነዚህን ሁለት ከተሞች ለጉብኝትም ሆነ ለንግድ የሚጓጉ ከተሞች እንዳይሆኑ አድርገዋል እነዚህ አስተዳዳሪዎች። የሚያስተዳድሩትን ህዝብ እና የቀረውን አለም ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። በእነዚህ እና በመሳሰሉት ከተሞች ላይ ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ የሚፈሰው ገንዘብ ከምንጩ ቁጥጥር ሊደረግበት ይገባል። ከምንጩ ስል ለጋሽ አገሮችን ይጨምራል። ተዳባዳቢነት ዴሞክራሲያዊነት አይደለም! መሃይምነት ነው።
ለአንባቢያን፥
“እየሞትን ሳንገድል ህገ-መንግስት የማስከበር ሰላማዊ ትግላችንን እንቀጥላለን” የሚለው የአንድነቶች መርህ ከምራቸው እንደሆነ ባልፈው ሳምንትም አስተውለናል። ፍጹም ሰላማዊነታቸው እና የመርህ ጽናታቸው በሚፈጸምባቸው የአካል ድብደባ እንደማይነቃነቅ ፍቼ ላይ አይተናል። በዚኽ ባለፈው የፈተና ሳምንት አንድነቶች መኪና በመከራየት፣ ወረቀቶች በማሳተም፣ ለህክምና ወጪ ባማድረግ እና ለተለያዩ ጉዳዮች ብዙ ወጪዎች እንዳደረጉ መገንዘብ አያዳግትም። ትግሉ የጋራ በመሆኑ ቋሚ ተመልካች መሆን ያዳግታል። የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል ለምንል በሙሉ የዳር ተመልካች መሆን ያዳግተናል። በባሌ ሮቤ እና በፍቼ በአንድነቶች ላይ የደረሰውን አይተን እና ሰምተን እጃችንን አጥፈን መቀመጥ ህሊናችንን ያዳግተዋል። የዜግነት ሚና መጫውት ያልጀመርን መጀመር፣ የጀመርን ደግሞ መቀጠል አለበን። ተሳትፎዋችንን ማሳደግ አለብን። አንድነቶች አንድም ክፉ ቃል ሳይሰነዝሩ እና ፈገግታ ከፊታቸው ሳይለያቸው ይኽን ሁሉ ስቃይ የሚቀበሉት ለግላቸው ብር ለማካበት እንዳልሆነ ግልጽ ነው። እየሞቱ ሳይገድሉ በአምባገነነኑ መለስ የረቀቀውን ፀረ-ሽብር ህግን ለማሰረዝ እና የኢትዮጵያችንን የፖለቲካ ትግል ባህል ለመቀየር እንደሆነ ልቦናችን ያውቀዋል። ስለዚህም አንድነቶች የጀመሩትን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ በመቀላቀል ታሪክ እንስራ።
የሚከተሉትን በማድረግም አንድነቶች መሰራት የጀመሩትን ታሪክ መቀላቀል እንችላለን።
እርዳታ፥ በገንዘብ!
እርዳታ፥ በአሳብ!
እርዳታ፥ መረጃዎች በፍጥነት በማሰራጨት!
እርዳታ፥ ፊርማዎች በማሰባሰብ!
እርዳታ፥ እንደገና በገንዘብ!
ፊርማ ለማስቀመጥም ሆነ ገንዘብ ለመላክ ይኽን የአንድነቶች ድረ ገጽ ይጎብኙ፥ www.andinet.org

Monday, August 26, 2013

ESAT Special program Ethiopia wedet Part I Aug 18 2013


ትዞራለች … ትዞራለች … ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች!

በአዕምሮ ሁከት የተለከፈችው እህት በጅዳ!

11-e


አንድ ወዳጄ መሃመድያ ተብሎ በሚጠራው የጅዳ ከፍል ከኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህርት ቤት አካባቢ ይህችን በፎቶው ላይ የምታዩዋትን እህት አግኝቶ ሊያነጋግራት ቢሞክርም ፈቃደኛ አልነበረችም። ከየት ነው የመጣሽው? ስትባል”ከመቀለ” ከማለት ባለፈ 
ስሟንና የሆነችውን አትናገርም። ብዙ ሊያግባባት ሞክሮ ያልተሳካለት ይህ ወዳጀ ይህች እህት ያደፈና የተቀደደ ጥቁር “አባያ” ለብሳና መናኛ ነጠላ ጫማ የተጫማችው እህት የአዕምሮ ሁከት እንዳለባት የተረዳው ብዙ ለማነጋገር ሞክሮ በሰጠችው አንዳንድ ምላሽ እንደሆነ ገልጾልኛል!
ልጁን ትምህርት ቤት ሊያስመዘግብ በሔደበት አጋጣሚ በጠራራው ሜዳ ስትንከራተት በማየቱና ምንም መርዳት ባለመቻሉ ያዘነው ወዳጄን መረጃ ይዤ የጅዳን ቆንስል ሃላፊዎች ስልክ በመደወል ይህችን እህት በመጠለያው አምጥተው ሌላው ቢቀር ካሉት የአዕምሮ በሽተኞች ጋር ቀላቅለው ከመኪና እና ከመሳሰሉት አደጋዎች አንዳትጋለጥ ይሰበስቧት ዘንድ ለማሳወቅ ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም!
11አንድ ሌላ ወዳጄ ከትላንት በስቲያ የዚህችን እህት አሁን ድረስ በአካባቢው መኖርና ዝም ብላ እንደምትዞር ነገረኝና ወዳለችበት አካባቢ ሔጄ በአካል ለማነጋገር ሞክሬ ነበር። በጠራራው ጸሃይ የውሃ ፕላስቲክ ባንድ እጇ፤ በሌላ እጇ ፊስታል አንጠልጥላ እየሳቀች እና እየተኮሳተረች ክው ክው እያለች የምትራመደው እህት አገኘኋት። ብዙ ከተከትልኳት በኋላ አረፍ ስትል ጠብቄ አማርኛ ትችያለሸ? አልኳት “ግደፈኒ” አለችኝ ፊቷን ዘወር እያደረገች! ለማግባባትና ለማቅረብ ሞከርኩ ፣ ልታስቀርበኝ አልቻለችም! ብዙ ተከተልኳት! … ትዞራለች … ትዞራለች … ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች! በቃ! እንዲህ ሆናለች …
13ዛሬም እዚያው አካባቢ እየዞረች እንደምትገኝ ወደ ትምህርት ቤት ለጉዳዩ የሔደ ወንድም አግኝቷት በስልክ ገልጾልኛል። ስትንከራተት አይቶ ሊረዳት የፈለገው ይህ ወንድም እሱም ሆነ ያየውን የዚህች እህት አበሳ ያሳያቸው የትምህርት ቤቱ ሴት ኢትዮጵያውያን መምህራን ተከትለው ሊያነጋግሯትና ሊረዷት ቢፈልጉም ፈቃደኛ ባለመሆኗ ምንም ማድረግ እንዳልቻለ እያዘን ካነሳው ፎቶ ጭምር ልኮልኛል! ዛሬም ይህን መረጃ ለማቀበል ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊ ወደ ቆንስል ጀኔራል ዘነበ ከበደ እና ቆንስል ሙንትሃ ስልክ ደውዬ የነበረ ቢሆንም ሊመልሱልኝ ግን አልቻሉም! ይህ በእንዲህ እንዳለ በተፈናቃይ ሰራተኞች ዙሪያ ጥናት ለማድረግ በአምባሳደር ውብሸት የተመራ ቡድን ዛሬም በጅዳ ከቆንስል ሃላፊዎች ጋር በመምከር ላይ መሆኑን ታውቋል።
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ

ዘረኝነት ምንድን ነው?

ማስተዋል ለማያቅተው

race


አንዳንዴ፣ ጊዜና ሁኔታውን ከጠበቁ አንድ ሁለት ቃላት፣ ከሺ ዓ/ነገሮች የበለጠ በአእምሮ ውስጥ ይገቡና እውነቱን ቁጭ ያደርጉታል።
አውሮፓውያን መቼም በዘረኝነት የተጠመቁበት ጊዜ አለፎና ተመክሮዋቸውን ሰብስበው ለራሳቸው፣ በተለይ ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት ወዲህ፣ በሰላም ለመኖር ይሞክራሉ፤ የኋላኋላ ተባብረው፣ ቀደም ሲል ደግሞ ቢያንስ በየራሳቸው መንግሥታት ሥር። በተለይም ጀርመን ስለዘረኝነት ተመክሮ ያውራ ቢባል፣ ይህ እንደማይሳነውና እንደሚችል ማንንም አያጣላም። ይህም ሆኖ ግን አሁንም ህዝቡ ከዳር እስከ ዳር፣ ከዚህ በሽታ ነጻ ነው ማለት አይደለም። ስለሆነም በስፖርት ሜዳ ላይ ሁሉ በተለይም እግርኳስ ጨዋታ ላይ ይህ የዘረኝነት በሽታ ደጋግሞ ይንጸባረቃል። አልፎ አልፎም ከአፍሪቃ በመጡ ወይንም እዚህ በተወለዱ ጥቁር ተጫዋቾች ላይ የዘረኝነት ስድቡ ሲበዛ፣ አእምሮ ያለው ዳኛ ጨዋታውን አልመራም ብሎ እስቲያቋርጥ ድረስ ሁሉ ያጋጥማል። በቅርቡ እንደሆነው። በዚህ ዓይነት ሁኔታ፣ በአንድ የጠዋት የቴሌቪዥን የስፖርት ሪፖርት ላይ እንደተዘገበው፣ አንድ የክለቡ ባልደረባ የሆነው ተጫዋች፣ አንድ ጀርመን ሀገር የተወለደ ጥቁር ጓደኛው ላይ የሚሰነዘረውን ዘረኝነት አስመልክቶ፣ በፌስቡክ(Facebook) ላይ፣ ለአስነዋሪዎቹ የዘርኝነት ስድቦቹ እንደሚከተለው ይመልሳል (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Thursday, August 15, 2013

የሥላሴዎች እርግማን (ሁለት)፤ አደህይቶ ማድከም (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም )


ከታትፎና ለያይቶ በማዳከም ቤቱን አፍርሶና መሬቱን ነጥቆ፣ ከሥራው አፈናቅሎና ሥራ አሳጥቶ ያለርኅራኄ ማደህየት በፕሮግራም የተያዘና በውጭ ኃይሎች የሚደገፍ ሥራ ነው፡፡
Prof. Mesfin Woldemariam
Prof. Mesfin Woldemariam
ለጥቂት ዓመታት በአሜሪካ ቆይቶ የመጣ አንድ ጓደኛዬ ራሱን በሁለት እጆቹ ይዞ ‹‹አዲስ አበባ በመሬት መናወጥ ፈራርሳ በመጠገን ላይ ያለች ከተማ ትመስል የለም እንዴ!›› አለኝ፤የመሬት አይደለም አንጂ የመናወጥ ነገር በእርግጥ አለ፤ የመሬት መናወጥ ባይደርስባትም የአእምሮ መናወጥ የመታት ከተማ ነች አልሁት፤ ቅንጅት ነፍሱን ይማረውና በፖሊቲካው መድረክ ብልጭ ብሎ ድርግም ካለበት ዓመት ጀምሮ በአዲስ አበባ ታይቶ የማይታወቅ የማፍረስና የመገንባት ሥራ በአንድ ላይ ጎን ለጎን ሲካሄድ እያየን ነው፤ ከጥንስሱ ጀምሮ የማሰብ ችግር ውላጅ መሆኑ በግልጽ ይታያል፤ ብዙ አገሮች አዳዲስ ከተማዎችን ሠርተዋል፤ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ሕንድ፣ ናይጂርያ፣ ብራዚል አሉበት፤ የወያኔ/ኢሕአዴግ ግን የተለየ ነው፤ አዲስ ከተማ እየሠራ ሳይሆን የጥንቱን እያፈረሰ ነው፤ ደርግ ሲጀምር ከጥንቱ ሥርዓት ጋር በመጣላት ነበር፤ ወያኔ ሲጀምር ግን ከማን ወይም ከምን ጋር ተጣልቶ አንደሆነ በግልጽ ባይታይም በጥላቻ መወራጨቱ ይታይ ነበር፤ ጎልቶ የወጣውም የችግረኛ ጉጉትና ምኞት፣ ሽሚያና ዝርፊያ የወያኔ ዓላማ ከራሱ የማያልፍ መሆኑን ያመለክት ነበር፤ በውጤቱም የሆነለት ያባትህ ቤት ሲዘረፍ እንደሚባለው ሆኖ ከውጭ ባንክ ተርፎ፣ ከአገር ውስጥ ባንክ ተርፎ፣ በጆንያና በጉድጓድ በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ያስቀመጠ ተደላድሎ እየሳቀ ይዝናናል፤ ያልሆነለትም በየሜዳው ያለቅሳል፤ ከተማው በሙሉ በማፍረስና በመገንባት ይታመሳል፤ ይተራመሳል፤ ዋናው ዓላማ ሕዝቡን ማዳከም ነው፤አዳክሞም ማደህየት ነው፡፡–
. ይህ ሁሉ መንገድ የደሀውን ቤት ሁሉ እየመነጠረ ሲረዝምና ሲሰፋ፣
. የደሀ ቤቶች ተመንጥረው መንገዱ ከረዘመና ከሰፋ በኋላ ባለሥልጣኖች በድንገት ስለባቡር የሚያስታውሳቸው አማካሪ     ሲያገኙ፤
. የድሆች ቤቶች እየተመነጠሩ የሰፋውን መንገድ እያፈረሱ ሲያጠቡት!
.ቤቶች ሲፈርሱና መንገዶች ሲረዝሙ፣ መንገዶች ሲሰፉና ሲጠቡ፣
. መንገዱ ለባቡሮች ሲቆፈርና ሲተራመስ፣
. መንገዱ በደሀዎቹ ቤቶች ፍርስራሽ ተጨናንቆ በደሀ እንባ ሲጨቀይ፣
. ለደሀዎች መኖሪያ ኮንዶሚንየም እየተባለ በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ሲገባና ሲወጣ፣
. የመንገዱና የባቡሩ ወጪ ከኮንዶሚኒየሙ ሥራ ጋር ተዳብሎ በቢልዮን የሚቆጠር ብር እየተተራመሰ ከመንግሥት ኪስ   ሲፈስ፣
.‹‹የመንግሥት ሌቦች›› የሚፈስሰውን እየለቀሙና እየተወዳደሩ ‹‹በምድር ላይ ሳንበተን ስማችንን እናስጠራ›>ብለው ግንበ-   ሰናኦርን ሲክቡ፣
.የሙስና ተከላካዮች ፈራ-ተባ እያሉ በእርሳስ ሲመዘግቡና ግንዱንና ስሩን ሳይነኩ በኢዮባዊ ትእግስትና በሰሎሞናዊ ፍርድ  ቅጠሎቹን እየከረከሙ ሲያረግፉ፣
.ሙስና ስሩ እየጠነከረ ግንዱም እንደግንበ-ሰናኦር ወደሰማይ እያደገ ሲሄድና ቅጠሉም ወዲያው ሲለመልም፤
.ደሀነትም በጌትነት እየተጋጠ በሞትና በሕይወት መሀከል ሆኖ እያቃሰተ ሲያድግ፣
.ለደሀነት መቀነሻ የሚባለው ሁሉ ደሀነትን ለማባባስ ሲውል፣
የደላው ይደሰታል፤ የተጎዳው እንባውን በየመንገዱና በየቤተክርስቲያኑ፣ በየቤተ መስጊዱ ይረጫል፤ የሚታዘብ ያንጎራጉራል፤
በቁንጣን፣ በስካር ጥቂቶች ሲንሩ፣
ብዙዎቹ ደግሞ በረሀብ መንምነው በቁንጫ ሲያርሩ፣
የደሀ እንባ ሲጎርፍ መሬቱ ሲሸበር፣
ዝብርቅርቁ ወጣ፤ ሕይወት ትርጉም አጣ፤
መንገዱ ጠበበ፤ ትርምስምሱ በዛ፤
እሪታው፣ ኡኡታው ቀለጠ እንደዋዛ፤
መሬቱም፣ ዓየሩም በክፋት ጠነዛ፤
ጥላቻና ቂሙ በሰፊው ተነዛ፤
እምቢልታው ሲጣራ ነጋሪት ሲያገሳ፣
የአለው ሁሉ ሞቶ የሞተው ሲነሣ፣
ምጽዓት መድረሱ ነው፤ ሊስተካከል ነው ፍርድ፤
በግና ፍየሉ ሊለዩ በገሀድ!
አፍርሶ መገንባት ዘለቄታ ያለው እድገትና መሻሻል ያስከትላል ብለው የሚያምኑ ከኋላቸውም ከፊታቸውም የሚያዩት ሁሉ ያከሸፋቸውና የከሸፉ ናቸው፤ ወደኋላ እንዳያዩ ታሪክ የላቸውም፤ ወደፊት እንዳያዩ ራእይ የላቸውም፤ የሥላሴዎች እርግማን!

ኢህአዴግ ከከፍተኛ አበል ጋር ፀረ አንድነት ፓርቲ ስልጠና አዘጋጀ


ፍኖተ ነፃነት
አንድነት ፓርቲ የጀመረውን ህዝባዊ ንቅናቄ ለማስተጓጎል ከፍተኛ አበል በመክፈል ለአባላቱ ስልጠና ማዘጋጀቱን ለኢህአዴግ ቅርበት ያላቸው የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጠቆሙ፡፡
አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የጀመረው ህዝባዊ ንቅናቄ ህዝባዊ ተቀባይነት ማግኘቱንና በስኬት መቀጠሉን ተከትሎ ኢህአዴግ “አንድነት ፓርቲንና ንቅናቄውን እንዴት ማስቆም ይቻላል” በሚል በከፍተኛ አመራሮቹ ውይይት ካደረገ በኋላ በመላ ሀገሪቱ ፀረ አንድነት ፓርቲ ስልጠና “ጠንካራ” ላላቸው አባላቱ ለመስጠት መዘጋጀቱን የሚገልፁት ምንጮቹ “ለስልጠናው ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ተመድቧል፤ ኢቲቪና የክልል ሬዲዮ ጣቢያዎችና የመንግስት ጋዜጦች አንድነት ፓርቲ የሸሪአ ህግን በኢትዮጵያ ተግባራዊ ለማድረግ ከሚንቀሳቀሱ ሽብርተኞች ጋር እየሰራ ነው የሚል የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እንዲከፍቱ ጥብቅ መመሪያ ደርሷቸዋል፡፡” በማለት ጨምረው ገልፀዋል፡፡ ምንጮቹ አክለውም “ኢህአዴግ ከየቀበሌው  እየመረጠ ስልጠና የሚሰጣቸው አባላቱ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችንና አባላትን በማሸማቀቅ፣በማስፈራራት፣ በቤተሰቦቻቸውና በሃይማኖት አባቶቻቸው በኩልም ከፖለቲካ እንዲወጡ ተፅዕኖ እንዲደርስባቸው የተቻላቸውን እንዲያደርጉ የሚያበቃ ነው” ብለዋል፡፡ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች እንዳረጋገጡት የዚሁ ስልጠና አካል የሆነ  ስልጠና ከነገ ጀምሮ በደቡብ ወሎ ዞን ኩታበር ወረዳ ከየቀበሌው ለተውጣጡ ከ200 በላይ ለሚሆኑ የኢህአዴግ አባላት ለሁለት ቀን ይሰጣል፡፡
Millions of voices for freedom - UDJ

‘‘የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ገዥ እንጂ መሪ አግኝቶ አያውቅም’’ ፕሮፌሰር በፍቃዱ ደግፌ


ፕሮፌሰር በፍቃዱ ደግፌ
Semayawi Party- Ethiopia (Facebook)
ፕሮፌሰር በፍቃዱ ደግፌ በተደጋጋሚ ጊዜአት በአደባባይ ከማይታዩ የሀገራችን አንጋፋ ሊህቃን አንዱ ናቸው። ምሁሩ በበርካታ መድረኮች ባለመቅረብ በቁጥብነታቸው ቢታወቁም ባገኙት መድረክ ግን አነጋጋሪ ርዕሰ ጉዳዮችን ያነሳሉ።
ባለፈው እሁድ ሰማያዊ ፓርቲ ባዘጋጀው የመወያያ መድረክ ላይ ቀርበው ታዳሚዎችን የመሰጠና ያወያየ ኃሳብ አንሸራሽረዋል። በፓርቲው ጽ/ቤት የተገኙ ወጣት ምሁራንም የፕሮፌሰሩን ኀሳብ በሌላ ኀሳብ በመሞገት ምሁራዊ አስተሳሰቦችና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅና ማራኪ ውይይት ተደርጓል።
ፕሮፌሰር በፍቃዱ በመወያያ መድረኩ ላይ ቀርበው የመነጋገሪያ ኀሳቦችን ያቀረቡት ፓርቲው በወጣቶች የሚመራ በመሆኑ አቅጣጫ የሚጠቁሙ ኀሳቦችን ለማሳየት ነበር። ጎን ለጐንም ሀገራዊ ርዕሰ ጉዳዮች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ፕሮፌሰሩ በዋናነት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ማነቆዎች ላይ የመንግስትና የሕዝቡ ሚና ምን መሆን እንዳለበት የራሳቸውን የመፍትሄ ኀሳቦች ሰጥተዋል። ከሁሉም በፊት ግን ፕሮፌሰሩ የሰሞኑ ወቅታዊና አነጋጋሪ ጉዳይ ስለሆነው የኃይማኖት ጉዳይ የተናገሩትን እናስቀድም። ፕሮፌሰሩ በኢትዮጵያ ክርስትናና እስልምና ምን ያህል መስተጋብር ፈጥረው እየኖሩ መሆኑን ከራሳቸው የቤተሰብ አወቃቀር በመነሳት የተናገሩት የታዳሚውን ቀልብ ያሳበ ነበር።
Befekadu Degefe, former Economics Research Fellow at The New School for Social Research
ፕሮፌሰር በፍቃዱ ደግፌ
‘‘የእኔ ቅድመ አያት ሙስሊም ናቸው። እናቴ ጌጤ ትባላለች። አያቴ ደግሞ ብሩ ይባላሉ። ቅድመ አያቴ መንሱር የሚባሉ ሲሆን፤ የመንሱር አባት ደግሞ በፈቃዱ ይባላሉ። እኔ በቅድመ አያቴ ስም ነው የምጠራው። ስሜን ያወጡልኝ አያቴ ናቸው። ቀኝ አዝማች ብሩ ይባላሉ። በፍቃዱ ሙስሊም ነው ያገቡት፤ ሰባት ልጆች ወልደው ነበር። ሦስቱ ሙስሊም ሲሆኑ አራቱ ክርስቲያን ሆነዋል። ከነዚህ ውስጥ ሴቷ ሙስሊም አግብታ አብራ ኖራለች። አብረን ነው የምንበላው አብረን ነው የምንኖረው’’ በማለት ለሀይማኖቶች መቀራረብ ከዚህ የተሻለ ማነፃፀሪያ የለም ብለዋል።
ፕሮፌሰሩ ወደ ዋናው ነጥባቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ሲመለሱ መነሻ ያደረጉት የሀገሪቱን የድህነት ደረጃ በመጥቀስ ነበር። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በአለም ላይ ማሊ ከምትባል ምዕራብ አፍሪካዊት ሀገር ብቻ ነው የምትሻለው ብለዋል።
‘‘ሀገሪቷ የገበሬና የገጠሬ ሀገር ናት። ስለዚህ ግብርና ትልቁ ስራ ነው። የሀገሪቱ ኢኮኖሚ እድገት ምንጭ ግብርና ነው። ግብርናው ወደ ኢንዱስትሪ አድጎ ብዙ ሰራተኛ መቀጠር አለበት። ሰራተኛው ከግብርናው ወደ ኢንዱስትሪ መምጣት አለበት’’ ያሉት ፕሮፌሰሩ አሁን ግን ገበሬው ከራሱ አልፎ ከተማን መመገብ ብቻ ሳይሆን የእራሱም ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን ነው የጠቀሱት።
‘‘ኢትዮጵያ ባት የሌለው ገበሬ ነው ያላት። ባት የሌለውም ማለት እግሩ አጥንት ነው። የዚህ ሀገር የግብርና ስራ ጉልበት በጣም የሚፈልግ ቢሆንም ገበሬው አቅሙን ያጣ ነው። ይሄ ሀገር እራሱን መመገብ ስላልቻለ በፈረንጅ ቸርነት ያለ ሀገር ነው’’ ሲሉ የጠቀሱት ፕሮፌሰር በፍቃዱ ‘‘ከተሞችም የድህነት መሸሸጊያና መጠለያ ሆነዋል’’ ብለዋል።
ገበሬው የተጎዳ በመሆኑና በቂ ምርት የማያመርት ስለሆነ የኑሮ ውድነት መከሰቱን የጠቀሱት ምሁሩ የኑሮ ውድነቱ ምስጢር አይደለም ብለዋል። የሰራ አጥነት በከተሞች የተስፋፋው ከገጠር ወደ ከተማ የሚፈልሰውና ድህነትን የሚሸሸው ሰው ስለበዛ ነው። ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገው ፍልሰት የተመረቁ ተማሪዎችንም እንደሚያካትት በመግለፅ ከተሞች የሰራ አጥነት ማዕከል ለመሆን በመገደዳቸው የችግር ቋት ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት ያለውን የሀገሪቱን ችግር ለመፍታት አንድ ትውልድ መስዋዕት መሆን እንዳለበትም ጠቅሰዋል። በተለይ አሁን ያለው ትውልድ የድሎት ኑሮ ለመኖር ያለው ዕድል የጠበበ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
የሀገሪቱ ሁኔታ ለመቀየር ግብርና ብቸኛው አማራጭ መሆኑንም የጠቀሱት ፕሮፌሰር በፍቃዱ፤ አሁን ሀገሪቱ የምትመካበት ምንም ሀብት ወይም ጥሪት የላትም ብለዋል። ‘‘ሀገሪቱ ቤንዚን የላትም። በእርግጥ ቤኒዚን ሌሎች ሀገሮችን ሲያባልግ አይተናል። ኢትዮጵያ ቤንዚን ከማግኘቷ በፊት ሕዝቡ በጥረቱ መልማት እንደሚችል ማመን አለበት። ከቤኒዚን በፊት የስራ ዲሲፕሊን መቅደም አለበት። ጥረቱ ካለ ቤንዚን ብቻ ሳይሆን ዩራኒየምንም ሆነ ወርቁንና ፕላቲኒየምን አውጥቶ መጠቀም ይቻላል። ጥረቱ መጀመር ያለበት ደግሞ ከግብርናው ነው’’ ብለዋል።
የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ከግብርናው መጀመር አለበት ከተባለ የሀገሪቱ የመሬት ስሪትና ይዞታ መታየት እንዳለበት ነው የገለፁት። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት ገጠሩ በአንድ አካባቢ ታፍኖ እንዲቀመጥ በመደረጉ ገበሬዎች የሚያርሱት የመሬት ስፋት በከፍተኛ ደረጃ እያነሰ ነው። በመንግስት ስታስቲክስ መሰረት በኢትዮጵያ ከአንድ ሄክታር በታች የሚያርሱ ገበሬዎች ወደ 11 ሚሊዮን ገበሬዎች ናቸው። ከሁለት ሄክታር በታች የሚያርሱ ወደ 14 ሚሊዮን ናቸው። ይሄ ደግሞ ገበሬው ምን ያህል ውልቅልቁ እንደወጣ ያሳያል’’ ብለዋል። በመፍትሄነትም የመሬት ጥበትን የሚቀንሱ አማራጭ የገቢ ምንጮች በመፍጠር መሬቱ ላይ በውርስም ሆነ በሌላ መንገድ የሚደረገው እየቆራረጡ መከፋፈል መቆም አለበት ብለዋል። በመሆኑም አንድ ገበሬ ቢያንስ ሦስት፣ አራት ወይም አምስት ሄክታር በመያዝ ትርፍ ሊያመርት ይገባል። ለዚህ ደግሞ በሀገሪቱ እንደገና የመሬት ክፍፍል ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። ገበሬውም ለሚወልዳቸው ልጆቹ መሬት እየቆረጠ የሚሰጥበት አካሄድ አንድ ቦታ መቆም አለበት። ልጆቹ ወደ ሌሎች አማራጭ የስራ ዕድሎች መሰማራት አለባቸው ብለዋል። ገበሬው ትርፍ ባመረተ ቁጥር አነስተኛ ኢንዱስትሪ በማስፋፋት ግብርናን ከኢንዱስትሪው ጋር ማመጋገብ ተገቢ እንደሆነም አስረድተዋል።
ግብርናውና ኢንዱስትሪው ከተመጋገበ በኋላ ገበያ መፍጠር ወሳኝ መሆኑንም ፕሮፌሰሩ በገለፃቸው ላይ አፅንኦት ሰጥተውታል። ‘‘የሀገር እድገት መሰረቱ ብዙ ማምረት ነው። በብዛት ያላመረተ ሀገር የኢኮኖሚ እድገት አለ ለማለት አይቻልም። እድገት ያለ ገበያ ደግሞ አይሳካም። በአሁኑ ወቅት የገበያ አማራጭ ሁለት አይነት ሲሆን የውጪና የሀገር ውስጥ ገበያ ነው። የውጪውን ገበያ ለመወዳደር የምርት ጥራት በቂ ነው’’ ያሉት ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያ ካለችበት ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ አንፃር ለመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ገበያ ጥሩ ዕድል ያላት መሆኑን ጠቅሰው፤ ‘‘የሰው ኃይላችንን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ከምንልክ የግብርና ውጤቶችን ብንልክ የተሻለ አማራጭ ነበር’’ ብለዋል።
መንግስት በኢኮኖሚው ውስጥ ስለሚኖረው ሚና
‘‘በፕሮፌሰር በፍቃዱ እምነት በአሁኑ ወቅት ትልቁ ቀጣሪ መንግስት ነው። መንግስት የሀገሪቱ ግዙፍ ተቋም ነው። በዚህ ሁኔታ መንግስትን ከኢኮኖሚው ማስወጣቱ ተገቢ አይደለም። ተወደደም ተጠላ መንግስት መንገድ፣ ግድብ፣ ትልልቅ ፋብሪካዎችን ካልገነባ ማን ሊገነባው ነው?’’ ሲሉ የሚጠይቁት ፕሮፌሰሩ ከመንግስት ውጪ ያለው ኢኮኖሚ የጉሊት ኢኮኖሚ ነው። የኢትዮጵያን እድገት በኃላፊነት ለመያዝ የሚችል የግል ክፍለ ኢኮኖሚ የለም። ስለዚህ መንግስት የግሉን ሴክተር መፍጠር አለበት። በ1959 ዓ.ም ኮሪያ ከእኛ እርዳታ የምትቀበል ሀገር ነበረች። ሲንጋፖር ብትሄዱ ‘‘የኢትዮጵያ አደባባይ’’ የሚባል ቦታ አለ። በችግራቸው ጊዜ እርዳታ ስለላክንላቸው ነው። ኮሪያም ዘምተናል እና ይሄ ሀገር ትልቅ ሀገር ነበር። ‘‘ትልቅም ነበር ትልቅ እንሆናለን’’ የሚለው አባባል እውነት ነው። ነገር ግን ትልቅ ነበርና ትልቅም እንሆናለን ማለት አሁን ግን ትልቅ አይደለንም ማለት ነው። የምስራቅ ኢሲያ ሀገሮች የኢኮኖሚ ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ መሆኑንም በ1959 ዓ.ም ጀኔራል ቹንኪ ፓርክ የኮሪያን መንግስት ገልብጦ ስልጣን ከያዘ በኋላ የሀገሪቱን የፊውዳል ሐብታሞች ሰብስቦ የግሉን ሴክተር መፍጠር ችሏል። እነ ሳምሰንግ ዘዩናድይ ወዘተን ሊፈጠሩ ችለዋል። በእኛም ሀገር መንግስት ጠንካራ የግል ሴክተር መፍጠር አለበት። መንግስት የግል ሴክተር ይፍጠር ሲባል አሁን እንዳለው መንግስት የግሉን ሴክተር ተክቶ ይስራ ማለት አይደለም ብለዋል።
ጃፓኖች ከድህነት አዘቅት የተነሱት አፄ ቴዎድሮስ በሞቱበት እ.ኤ.አ 1868 ዓ.ም ወደስልጣኔ ማምራት የጀመሩበት ዘመን እንደነበር ያወሱት ፕሮፌሰሩ በዚያን ጊዜ አፄ ቴዎድሮስም ሀገሪቱን ወደ ኢንዱስትሪ የመቀየር ራዕይ የነበረው ንጉስ ነበር ብለዋል። በመሆኑም መንግስት የሀገሪቱን ኢንዱስትሪ ለመቀየር የቅድሚያ ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ኢንዱስትሪ ሲባል ግዙፍ ፋብሪካ ማቋቋም ብቻ ሳይሆን የመንደር ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የምርት ሰንሰለትን መመጋገብ መፈጠር አለበት ብለዋል። ለምሳሌ ጥሬውን ጤፍ ከገበሬው ይዞ ወደ ከተማ ከማምጣት እዛው ወፍጮ ቤት በመትከል ኢንዱስትሪ መጀመር ይቻላል። ከወፍጮ ቤቱ ጎን ለጎን ለጤፍ መያዣ ጆንያ ፋብሪካ ማቋቋም ይቻላል፤ ጆንያውን ለማምረት ደግሞ የቃጫ ፋብሪካ እያሉ ምርት የማመጋገብ የምርታማነት ሰንሰለት በመፍጠር ኢንዱስትሪን በመንደር ደረጃ መጀመር እንጂ ግዙፍ ፋብሪካን በማሰብ ሊሳካ አይችልም ብሎ ተስፋ መቁረጥ አይገባም ብለዋል።
ሀገሪቱን ለመለወጥ የትምህርት ስርዓቱም መለወጥ አለበት ያሉት ፕሮፌሰር በፍቃዱ በአፄ ኃይለስላሴ ጊዜ ትምህርት የምንማረው፤ ለልማት ሳይሆን ቋንቋ ለመተርጎም ነበር። በዚያን ጊዜ ወደ ሀገሪቱ የገባው ትምህርት የአርስቶክራት ትምህርት ነበር። የመደብ (class) ትምህርት ነው። ለስነ-ፅሁፍና ከፈረንጆች ጋር ለመግባባት ነበር። አሁን ግን የትምህርት ስርዓቱ ወደ ዳቦ የሚቀየር መሆን አለበት። ነገር ግን እየተሰጠ ያለው ትምህርት እውቀት እንጂ ስኪል የለውም። በአሁኑ ወቅት 27 ከመቶ የዲግሪ ተመራቂዎች ስራ የላቸውም። ዩኒቨርሲቲዎች የስራ አጥ ማምረቻ ሆነዋል። ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡት የተለዩ የነጠሩና የሳይኒስትነት ደረጃ ያላቸውን እንጂ ሁሉንም በጅምላ እንዲገቡ ማድረጉ ኪሳራ ነው። ጥራት ያላቸውን ወደ ዩኒቨርሲቲ እያስገቡ የቀረውን ደግሞ ስኪል እናስተምረው ብለዋል። የትምህርት ስርዓቱ ሰው ሰርቶ ለመብላት የሚያስችል እውቀት እንዲኖረው በሚያስችል መልኩ መከለስ አለበት ሲሉም ገልፀዋል።
በዕለቱ ከነበሩ ወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የፓርቲው አባላት ለፕሮፌሰር በፍቃዱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች አቅርበውላቸው ነበር። ከነዚህም ጥያቄዎች መካከል ሀገሪቱ የፖሊሲ ሳይሆን የብሔራዊ ስሜት ማጣት ዋነኛ ችግሯ መሆኑ ተጠቅሶ ነበር። ፕሮፌሰሩ ግን የሀገሪቱ ብሔራዊ ስሜት ሙሉ በሙሉ አለመሞቱንም ይልቁኑ በዚህኛው ትውልድ እየተነሳ መሆኑን ከገለፁ በኋላ ‘‘ሐገሪቷ ያጣችው ብሔራዊ ስሜት ሳይሆን ብሔራዊ መሪ ነወ። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ገዥ እንጂ መሪ አግኝቶ አያውቅም። ልማት በሕዝብ ብቻ ሳይሆን ብሔራዊ ስሜት ባለው መሪ ሊረጋገጥ ይችላል’’ ሲሉ መልሰዋል።
‘‘በተጨማሪም የሀገሪቱ ብሔራዊ ስሜት በአሁኑ ጊዜ በወጣቱ እያንሰራራ ነው።’’ ያሉት ፕሮፌሰሩ ለብሔራዊ ስሜት መጎዳትም ኦነግን ተጠያቂ አድርገዋል። ‘‘በዚህ ሀገር ከመንግስቱ ኃይለማርያም ቀጥሎ ወንጀል የፈፀመው ኦነግ ነው። ኦነግ በሁለቱ ትላልቅ ሕዝቦች መካከል በአማራና በኦሮሞ መካከል ክፍተት እንዲፈጠር ጥረት አድርጓል። በክፍተቱም ወያኔ እንዲገባ አድርጎ ተገዥ አድርጎናል። ወያኔ ደግሞ ያጠፋው ነገር የለም። እኛ ዝም ብለን እየተገዛንለት ነው’’ ብለዋል።
ሰፈራ በተመለከተ የሕዝብ እንቅስቃሴ አስፈላጊ መሆኑን በመግለፅ የሰፈራ ፕሮግራም ደጋፊ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ነገር ግን ሰፈራው በዋናነት የሚሰፍረውን ሕዝብ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማረጋገጥ አስፈላጊ እንደሆነ ጠቅሰዋል። ‘‘ኮንዶሚኒየም የከተማ ሰፈራ ነው’’ ያሉት ምሁሩ፤ ሰፈራ የሕዝብን ቅድሚያ ጥቅም በሚያረጋግጥና ልማትን በተለይም ግብርናን በሚያፋጥን መልኩ ቢፈፀም ችግር እንደሌለው ነው የገለፁት። ለሁሉም ግን ይቻላል፤ እንችላለን ብለን ልንንቀሳቀስ ይገባል ብለዋል።
በዘሪሁን ሙሉጌታ (ሰንደቅ ጋዜጣ)

Thursday, August 8, 2013

ESAT Daliy News Amsterdam August 08 2013 Ethiopia


ለተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ደቡብ ኮርያ ከመጡት 59 ኢትዮጵያዊያን መካከል 38 ጥገኝነት ጠየቁ


Ethiopian Asylum Seekers in Korea
ሰበር ዜና፣ ከስምንት ወር በፊት ለተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ደቡብ ኮርያ ከመጡት 59 ኢትዮጵያዊያን መካከል 38 ኢትዮጵያዊያን የኮርያን መንግስት ጥገኝነት ጠየቁ። ከነዚህ ኢትዮጵያዊያን መካከል ኣንዳንዶቹ በሲቪል ሰርቪስ፣ በባንክ ፣ በግብረ ሰናይ ድርጅቶች፣ በተለያዩ ፋብሪካዎችና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ የሚሰሩ ነበሩ። ጥገኝነት ከጠየቁት መካከል ኣንዱ የኣዲስ ኣበባ ፖሊስ ባልደረባ መሆኑም ታውቋል።
እነዚህ ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ላለፉት ስምንት ወራት በኮርያ መንግስት የተዘጋጀላቸውን ስልጠናዎች ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን የሙያ ስልጠናውን ከጨረሱ በሁዋላ ጥገኝነት ለመጠየቅ መወሰናቸውን ኣሳውቀዋል። ጥገኝነት ለመጠየቅ ያበቃቸውን ነገር ሲገልጹ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰባዊ መብት ጥሰት በመቃወም፣ በግላቸው በሚሰሩባቸው መስሪያ ቤቶች የመንግስት ኣካላት ባደረሱባቸው በደል ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
እነዚህ ወገኖች በኣሁኑ ሰኣት ፒናን በተሰኘ የመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ሲሆን በኮርያ ቆይታቸው ሃገራቸውን ከኣምባገነን ኣገዛዝ ለማላቀቅ ከሚታገሉ ሃቀኛ ድርጅቶች ጋር ኣብረው በቆራጥነት ለመታገል መወሰናቸውን በኣንድ ድምጽ ገልጸዋል። ስለተሰጣቸው ስልጠና የኮርያን መንግስት ኣመስግነው ወደፊት ለሚያደርጉት የነጻነት ትግል የኮርያ መንግስት ድጋፍ እንደማይለያቸው ተስፋቸውን ገልጸዋል።
ተጨማሪ መረጃ ለሚሹ ወገኖች ከጥገኝነት ጠያቂዎቹ መካከል የቡድኑን ተወካዩች በስልክ መግኘት ይቻላል።
ሲሳይ ወልደግብሬል 821059503443
ቶማስ ኣሻሜ 821059506511
ኣልዓዛር ስዩም 821059503443
ከኣክብሮት ጋር
ገለታው ዘለቀ
Ethiopian Asylum Seekers in Korea 1

በመንግሰት የችግር አፈታት ዘዴዎች ዛሬም አዝነናል፧ አፍረናልም!!!!


ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ከሁሉም በማሰቀደም ሰማያዊ ፓርቲ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳቹ፣ በዓሉ የሰላምና የደሰታ እንዲሆንላቹ ኢድ ሙባረክ በማለት ምኞቱን ይገልፃል ::Blue Party Ethiopia
ኢሕአደግ መራሹ መንግሰት ተቋማትን የመቆጣጠር አባዜው ከግዜ ወደ ግዜ እየባሰባት በመምጣቱ ዛሬም እጁን ያላሰገባበት ምንም አይነት ተቋምና አሰተሳሰብ ባይኖርም በተለይ ባለፈው አንድ አመት ተኩል ጀምሮ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር በፈጠረው እሰጥ አገባ መፍትሔ አጥቶ እሰከ አሁኗ ሰአት ቀጥሏል:: ሰማያዊ ርቲ የመንግሰትን በሐይማኖት ጣልቃ መግባት አጥብቆ በመቃወም የራሳቸውን የእሰልምና እምነት መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን እንዲፈታና ችግሩም በውይይት እንዲፈታ በተደጋጋሚ ግዜ ጥሪውን አቅርቧል::
ነገር ግን መንግሰት ችግሮችን በሐይል ጨፍልቄ እፈታለሁ የሚል የተለመደ አካሔድ ለፓርቲያችን ጥሪ የሰጠው ምላሽ ካለመኖሩም በላይ የፓርቲያችንን ሰም በማጉደፍ የሀገር ጠላትና አሸባሪ ፓርቲ አድርጎ ለማሳየት ጎምበስ ቀና በማለት ላይ ይገኛል::
መንግሰት ከእሰልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን ጋር በፈጠረው ችግር ባለፈው አንድ አመት ተኩል ብዙ ችግሮች ተፈጥረዋል፣ ሀብትና እውቀት የሚያድግበት ግዜ ባክኗል፣ በሰው አካልና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፣ ሕይወት ጠፍቷል:: ችግሩ ግን አሁንም አልተፈታም፧ እንደውም እያደገና እየከረረ ሔዷል:: በዛሬው ነሐሴ 2 ቀን 2005 ዓ.ም የኢድ አልፈጥር በአል አከባበር ላይ በመላው ኢትዮጵያ በሕብረት የመሰገጃ ቦታዎች በተሳተፉ የእምነቱ ተከታዮች ላይ በመንግሰት ታጣቂዎች በተወሰደው እርምጃ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች አሰቃቂ ድብደባና የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል:: በአሰር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ደርሞ የማረሚያ ቦታዎች እና ፕሊሰ ጣቢያ አልበቃ ብሎ በጋራዦች ጭምር ታሰረዋል:: ባልተረጋገጡ መረጃዎችም የሰው ሕይወት ጠፍቷል:: በዚህም ነገር ፓርቲያችን ከልብ አዝኗል::
ሰላማዊ ፓርቲ አሁንም መንግሰት ችግሮቹን በሐይል ለመፍታት የሚወሰደውን እርምጃ አጥብቆ እያወገዘ በቀላሉ መፍትሔ ሊሰጣቸው የሚችሉ የመብት ጥያቄዎችን በማፈን ዜጎች ተገደው ወደማይፈልጉት መንገድ እንዳይሄዱ በጥብቅ ሊታሰብበት እንደሚገባ ማሳሰብ ይፈልጋል:: ሐገራችን ያለችበትን ቀጠናና ታሪካዊ መሰተጋብርም በውል የሚረዳ መፍትሄ ባሰቸኳይ እንዲሰጥ አሁንም አሁንም አጥብቀን እንጠይቃለን::
ነሐሴ 2 ቅን 200 ዓ.ም
አዲሰ አበባ
Blue Party Ethiopia