FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Thursday, January 30, 2014

የ2014 የዓለም የመፈንቅለ መንግሥት ትንበያ

ኢትዮጵያ 25ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች

coup map


በያዝነው የአውሮጳውያን ዓመት ሊከሰቱ የሚችሉ የመፈንቅለ መንግሥት አደጋዎች ይፋ ሆኑ፡፡ በርካታዎቹ በአፍሪካ አገራት ሲሆኑ አደጋው ካንዣበበባቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ 25ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
በአሜሪካ የፖለቲካ ሳይንቲስት የሆኑት ጄይ ዑልፌልደር የተለያዩ የሒሳብ ስሌቶችን በመጠቀም የ2014ዓም የመፈንቅለ መንግሥት ትንበያቸውን ሰጥተዋል፡፡ እንደ እርሳቸው ትንበያ ከሆነ 40 አገራት ቀይ የአደጋ ምልክት በርቶባቸዋል፡፡ ስለ ጉዳዩ ሲናገሩ መፈንቅለ መንግሥት እንዲሆን የሚመኙት ነገር ባይሆንም የመከሰቱ ጉዳይ ግን መነገር ያለበት ነው ይላሉ ምሁሩ፡፡
በተለያዩ የአሜሪካ አንጋፋ ጋዜጦች ላይ የተዘገበው ይኸው ጥናት እንደሚያመለክተው በዓለማችን ላይ 40 አገራት ከፍተኛ የመፈንቅለ መንግሥት አደጋ ያነጣጠረባቸው መሆናቸውን በጥናቱ ተገልጾዋል፡፡ አብዛኛዎቹም ከአፍሪካ መሆናቸው አሁንም አህጉሪቱ ለበለጠ ቀውስ የተጋለጠች መሆኗን የሚያሳይ ነው፡፡
forecast-dot-2014በቀዳሚነት የመፈንቅለ መንግሥት የሚያሰጋቸው አገራት ጊኒ፣ ማዳጋስካር፣ ማሊ፣ ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ኒጀር፣ ጊኒ ቢሳው እና ሱዳን፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፑብሊክና ደቡብ ሱዳን ናቸው፡፡ ከአውሮጳ ምንም አገር በዝርዝሩ ውስጥ ያልገባ ሲሆን ዩክሬይን አደጋው ጥላ ካጠላባቸው በቀዳሚነት የምትጠቀስ ሆናለች፡፡ ከወደ አሜሪካ ዩኳዶርና ሃይቲ ቀዩ የአደጋ ምልክት የታየባቸው ሲሆን ከእስያ ታላንድ፣ አፍጋኒስታን እና ፓኪስታንን ጨምሮ ስድስት አገራት የመፈንቅለ መንግሥት የቀይ ምልክት አደጋ ካለባቸው 40 አገራት ውስጥ ይገኛሉ፡፡
ከ40ዎቹ ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ 25ኛ ላይ ትገኛለች፡፡ በየጊዜው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ህወሃት/ኢህአዴግ ሥልጣኑን ለራሱ ታማኞች ብቻ በመከፋፈል እንዲያም ሲል በቤተሰብ ደረጃ በማውረድ እየሸነሸነው በመሆኑ ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የበይ ተመልካች ሆኗል፡፡ ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ሰሞኑን ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ አዲስ አድማስ ሲዘግብ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበቡን እና የነጻው ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን ገልጾ ነበር፡፡
አፋኝ ሕጎችን በማውጣትና ማንኛውንም ዓይነት የግለሰብ መብት በመንፈግ በአንጻሩ ሊኖር የማይችል የቡድን መብት አስከብራለሁ የሚለው ህወሃት/ኢህአዴግ በተመሳሳይ የሚወጡ መረጃዎችን በማጣጣል ዋጋ ቢስ ሲያደርግ መቆየቱን የተለያዩ የሲቪክ ማኅበራትና የፖለቲካ ፓርቲዎች በየጊዜው የሚያነሱት ነጥብ ነው፡፡ በተቀረው ደግሞ “ልማት፣ ህዳሴ፣ ውዳሴ፣ … ” በማለት የለውጥ ሃሳብ ከመጣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ይስተጓጎላሉ በሚል በሕዝቡ ዘንድ ማደናገሪያ በመፍጠር በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱትን የፖለቲካ ፓርቲዎች “ጸረ ልማት” በማለት እንደሚወነጅላቸው ያማርራሉ፡፡ በምርጫ ማጭበርበርና ማንኛውንም ፖለቲካዊ ሆነ ማኅበራዊ እንዲሁም ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ በሙሉ ቁጥጥር ሥር ማዋል ኢህአዴግ በሥልጣን ለመቆየት የሚጠቀምባቸው ዓይነተኛ መንገዶቹ እንደሆኑ በስፋት ይጠቀሳል፡፡
ይህንን የመፈንቅለ መንግሥት ትንበያ የቀመሩት ምሁር ስሌታቸውን ለማቀናበር የተለያዩ መረጃዎችን መጠቀማቸውን ገልጸዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል የአገራቱ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ፣ በቅኝ ግዛት የመያዝ ሁኔታ፣ የአገራቱ ዕድሜ፣ ከነጻነት በኋላ የኖሩበት ዓመታት፣ የፖለቲካ መረጋጋት፣ የእርስበርስ ግጭት፣ የነጻ ምርጫ ሁኔታ፣ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ በየቀጣናው ያለ የመፈንቅለ መንግሥት እንቅስቃሴ፣ ወዘተ የተወሰኑት ናቸው፡፡ ይህንን አያይዘውም የመፈንቅለ መንግሥት ትንበያ ማድረግ የግድ መፈንቅለ መንግሥት ይሆናል ማለት እንዳይደለ ነገር ግን አደጋውን ተመልክቶ አስፈላጊ እርምጃዎች በመውሰድ እንዳይሆን መከላከል ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ (ካርታዎቹ የተወሰዱት ከጄይ ዑልፌልደር ብሎግ ነው)
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የዛሬ ዓመት የአሜሪካንን የደኅንነት ምክርቤት ጠቅሶ ባወጣው ዜና በ2030 እኤአ ከሚከሽፉ መንግሥታት (failed states) መካከል ኢትዮጵያ አንዷ መሆኗን ዘግቦ ነበር፡፡ ዜናውን ከዚህ በታች በድጋሚ አትመነዋል፡፡

“በ2030 ከሚከሽፉ መንግሥታት አንዷ ኢትዮጵያ ነች”

ዘገባው የ15 አገራትን ዝርዝር አውጥቷል
የአሜሪካ የብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር በ2030 የሚከሽፉ 15 መንግሥታትን (failed states) ዝርዝር አውጥቷል፡፡ “በግጭት መብዛትና በአካባቢ ጥበቃ ቀውስ ምክንያት” ይከሽፋሉ ተብለው ከተተነበዩት የአፍሪካ፣ የእስያና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡
እጅግ የነጠረ፣ ያልተዛባና የተጠና ዘገባ ለአሜሪካ የስለላ ተቋማት፣ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አውጪዎችና ለዓለምዓቀፍ ግንኙነት ተመራማሪዎች በማውጣት የታወቀው የአሜሪካ ብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት ከተቋቋመ በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ምክርቤቱ በሚያወጣቸው ዘገባዎች የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የተለያዩ መ/ቤቶች ተጽዕኖ እንደማያደርጉበት የሚናገር ሲሆን፤ ዘገባዎቹንም ከአድልዎ እና ከአሜሪካ መንግሥት አቋም ነጻ በመሆን እንደሚያዘጋጃቸው ይናገራል፡፡
NICየም/ቤቱ ዘገባ በተለይ ምርጫ ከተካሄደ በኋላ ለመጪው ፕሬዚዳንት የወደፊቱን የዓለማችን መልክ ምን እንደሚመስል የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ አስተሳሰቦች እና ዓለምአቀፋዊ ዝንባሌዎች ላይ አቅጣጫ የሚጠቁም ትንበያ ያደርጋል፡፡ ለፕሬዚዳንቱ ዓለምአቀፋዊ የደኅንነት ዘገባ ያቀርባል፤ ለብሔራዊ የጸጥታ ምክርቤት እና ለአገር ውስጥ ደኅንነት መ/ቤት ምክር ያቀብላል፤ በአጠቃላይ የአሜሪካን የስለላና የደኅንነት ማኅበረሰብ ሊከተል በሚገባው ጉዳይ ላይ አቅጣጫ የሚያስይዝ ሃሳብ ያቀርባል፡፡
በዚሁም መሠረት ባለፈው የታህሳስ ወር “በ2030 የዓለም አቅጣጫ፡ አማራጭ አገራት” በሚል ርዕስ አንድ ዳጎስ ያለ ጥናት አቅርቧል፡፡ ይኸው 160ገጽ ያለው ዘገባ የዛሬ 17ዓመት የዓለማችን ገጽታ ምን እንደሚመስል ከየአገራቱ በተወሰደ ጥናትና እዚያው በሚገኙ ተመራማሪዎች የሰበሰበውን ያካተተ ነው፡፡ ዓለማችን የምታዘነብልባቸው ቀዳሚ ሁኔታዎች አንዱ ሰዎች በራሳቸው አነሳሽነት ድህነትን ለመቀነስ፣ በትምህርት ለማደግ፣ በቴክኖሎጂና በህክምና ለመራቀቅ እንዲሁም በገቢም የመካከለኛው መደብ ላይ ለመድረስ የሚያደርጉት ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ ከተጠቀሱት አንዱ አቅጣጫ ጠቋሚ ነው፡፡
ሌሎቹ ዓለምን አንድ አድርጎ በመዳፉ ሥር የሚገዛ ኃይል የማይነሳ መሆኑ ከሚታዩት ከፍተኛ ዝንባሌዎች ተጠቃሽ ሲሆን አሜሪካ ምንም እንኳ “የዓለም ፖሊስ” የመሆኗ ሁኔታ የሚቀንስ ቢሆንም የዓለምን አቅጣጫ መቆጣጠሯ ይቀራል ማለት እንዳልሆነ ይጠቁማል፡፡ የዓለም የሕዝብ ቁጥር ከመጨመሩ አኳያ “እያረጁ” የሚሄዱ አገራት የኢኮኖሚ ዕድገታቸው እንደሚያሽቆለቁልና ከገጠር ወደከተማ ፍልሰት እንደሚጨምር፤ 60በመቶ የሚሆነው የዓለማችን ሕዝብ በከተሞች አካባቢ ኑሮውን እንደሚያደርግ ይተነብያል፡፡ በዚህም ምክንያት የውሃ፣ የምግብና የኃይል (ኤነርጂ) ፍላጎት ከሕዝብ ቁጥር መጨመር ጋር ተያይዞ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያድግ ይናገራል፡፡ የቴክኖሎጂ ምጥቀትና የማኅበራዊ ሚዲያ አገልግሎትም የዓለማችንን አቅጣጫ እንደሚቀይር ያስረዳል፡፡
የቻይና እና የአሜሪካ ግንኙነት በስፋት እንደሚቀጥልና በበርካታ ፈርጆች ትብብርና ስምምነት እየፈጸሙ ሰፋ ያለ ዓለምአቀፋዊ ኅብረት እንደሚያደርጉ የሚናገረው ይህ ሪፖርት በየአገራቱ እየሰፋ የመጣው በድሃና በሃብታም መካከል ያለው ክፍተት የማኅበራዊ ቀውስ እንደሚያስከትል ይጠቁማል፡፡ ይህም ቀውስ በአንዳንድ አገራት ውስጥ እየሰፋ በመምጣት ለተባባሰ ግጭትና ክስረት እንደሚያጋልጥ የኑሮ ልዩነቱም የማኅበራዊ ቀውሱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንደሚያደርሰው ይተነትናል፡፡ የሃይማኖት ሚና እንደሚጨምር የጠቆመው ዘገባ ይህንኑ ተከትሎ መካረርና ግጭት እንዲሁም አሸባሪነት ለመስፋፋት ሃይማኖት ምክንያት እየሆነ እንደሚሄድ ይናገራል፡፡
በዘገባው ከተነገረው በተጻጻሪ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ከተጠናቀቀ ወዲህ እስካሁን በ44 አገራት ጉዳይ በቀጥታና በተዘዋዋሪ መንገድ ጣልቃ በመግባት ጦርነት ያካሄደችው አሜሪካ የዓለም ኃያል ሆና እንደምትቀጥል በመናገር ሪፖርቱን የሚያጣጥሉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ እንደማስረጃም አድርገው አሜሪካ በተለያዩ አገራት ያላትን 737 የወታደራዊ ተቋማት ይጠቅሳሉ፡፡ ስለሆነም ዘገባው የአሜሪካ የበላይነት የመቀነሱን ጉዳይ አንስቶ የተናገረውን አይቀበሉም፡፡
እኤአ በ2030 የሚክሽፉት 15ቱ መንግሥታት (ፎቶ: ጂአይ)
ዘገባው የዓለማችንን የወደፊት ሁኔታ ሲተነብይ በዋንኛነት ከጠቀሳቸው ጉዳዮች አንዱ በ2030 የሚከሽፉ መንግሥታትን ዝርዝር ሰጥቷል፡፡ “በግጭት መብዛትና በአካባቢ ጥበቃ ቀውስ ምክንያት” የሚከሽፉ መንግሥታት ተብለው ከተጠቀሱት 15 አገራት መካከል ኢትዮጵያ እንዷ ስትሆን አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ባንግላዴሽ፣ ቻድ፣ ኒጀር፣ ማሊ፣ ኬኒያ፣ ቡሩንዲ፣ ሩዋንዳ፣ ሶማሊያ፣ ዴሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ፣ ማላዊ፣ ሃይቲና የመን የተቀሩት ናቸው፡፡
ይሁንና ይኸው ም/ቤት እኤአ በ2015 ፓኪስታን የምትከሽፍ አገር ትሆናለች በማለት ትንቢት ሰጥቶ ይኸው እስካሁን አለች በማለት ዘገባውን የሚያጣጥሉ ክፍሎች ኢትዮጵያም ሆነ ሌሎቹ አገራት ለመክሸፋቸው በቂ ማስረጃ የለም በማለት የዘገባውን ጥቆማ ይቃረናሉ፡፡ በሌላ በኩል እንዲህ ያለው የመክሸፍ ሁኔታ ሊዋጥለት የማይችለው ኢህአዴግ “ህዳሴ፣ ውዳሴ” ከማለት ይልቅ ይህንን ጉዳይ አጥብቆ ሊያስብበት እንደሚገባና የሥርዓት መበስበስ አመላካች የሆነውን “የመንግሥት ሌቦች” መበራከት መፍትሔ ሊያበጅለት እንደሚገባ ደጋፊዎቹና አመራሩ በየጊዜው የሚያነሱት ነጥብ ነው፡፡
በዚሁ የኢትዮጵያ እንደ አገር የመክሸፍ ጉዳይ ላይ ያነጋገርናቸው አሁን ካላቸው ተግባር አኳያ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ በአውሮጳ የሚገኙ የፖለቲካና ዓለምአቀፋዊ ግንኙነት ተመራማሪ “ችግሩ የኢህአዴግ ብቻ ሳይሆን የተቃዋሚውም ነው” ይላሉ፡፡ “በአገር ውስጥ ያለው ተቃዋሚ ከውስጥ የሥልጣን ሽኩቻና ከስብሰባ/ውይይት ጋጋታ ባለፈ መልኩ ሕዝብን የሥልጣን ባለቤት ሊያደርግ የሚችል የተቀናጀና ውጤታማ ተግባር ሊፈጽሙ ይገባቸዋል” የሚሉት ምሁር በውጭ ያለውም “ከጊዜያዊና ጥቃቅን የራስ ክብር የመፈለግ አካሄድ በመላቀቅ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጣ ጡንቻውን በወያኔ ላይ ማሳረፍ ይጠበቅበታል” ብለዋል፡፡ “የደኅንነት ተቋሙ ባወጣው ዘገባ ላይ በግልጽ እንደተነበየው የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ የመጨመሩ ያህል በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ይህንኑ ለውጥ ማምጣት የሚችል የዘመኑ ቴክኖሎጂ ለአሉባልታና ተራ የፖለቲካ ወሬ ከመጠቀም ይልቅ አገር ለማዳን ተግባር ሊጠቀምበት ይገባል” በማለት አስተያየታቸውን ደምድመዋል፡፡
የደኅንነት ምክርቤቱ ያወጣው ሙሉ ዘገባ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡
http://www.goolgule.com/coup-forecasts-for-2014/

“ኢትዮጵያውያን ለምንድን ነው የውጭ ገበሬዎች የሚያስፈልጓቸው? ምንድን ነው ይዘውልን የሚመጡት?” አቶ ግርማ

"አንድም ሰው ከቀዬው እንዲፈናቀል አልተደረገም" ሚኒስትር ዴኤታ

displaced anuaks


  • “ሰፋፊ የእርሻ ኢንቨስትመንቶች እንደታሰቡት ውጤታማ አልሆኑም” መንግሥት
  • መንግሥት የውጭ ባለሀብቶች የመሬት ቅርምት ኢትዮጵያን አይመለከትም አለ
የውጭ ባለሀብቶች በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ ለመሰማራት ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን ወስደው እያለሙ እንጂ፣ መሬት ለመቀራመት ብለው ወደ ኢትዮጵያ አልገቡም ሲል ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
“መሬት መቀራመት ኢትዮጵያን ጭራሽ አይመለከታትም፤” ሲሉ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታውቀዋል፡፡
ሚኒስትሩ የመሥሪያ ቤታቸውን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለፓርላማው ማክሰኞ ዕለት ሲያቀርቡ፣ ሰፋፊ መሬቶች ወስደው በግብርና ላይ ኢንቨስት እያደረጉ ስለሚገኙ የውጭ ባለሀብቶች ትክክለኛ ማብራሪያ እንዲሰጡ በተጠየቁበት ወቅት ነው ይህንን ያሉት፡፡
በፓርላማ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ ግርማ ሠይፉ ለሚኒስትሩ ባቀረቡት ጥያቄ፣ የውጭ ኩባንያዎች ሰፋፊ መሬቶች አንዳንዶቹ እንደሚሉት ቤልጂየምን የሚያህል መሬት ተሰጥቶ እየተካሄደ ስላለው ኢንቨስትመንት በቂ ማብራሪያ በሪፖርቱ ስላልተካተተ እውነቱ ሊብራራ ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በሰፋፊ መሬቶች ላይ የሚካሄድ የግብር ኢንቨስትመንት ችግር የለውም ያሉት አቶ ግርማ፣ በመንግሥት ላይ እየቀረበ ያለው ክስ አርሶ አደሮች እንዲፈናቀሉ ማድረጉ አንዱ ነው ብለዋል፡፡
forced displacementየውጭ ኩባንያዎቹ ብድር የሚያገኙት ከኢትዮጵያ መንግሥት መሆኑን የመገናኛ ብዙኃን እየዘገቡ መሆኑን በማስታወስ፣ “በኢትዮጵያ ገንዘብና በኢትዮጵያ መሬት ለምንድን ነው የውጭ ኩባንያዎች መጥተው የሚያለሙት?” በማለት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
“ኢትዮጵያውያን ለምንድን ነው የውጭ ገበሬዎች የሚያስፈልጓቸው? ምንድን ነው ይዘውልን የሚመጡት?” በማለት አቶ ግርማ የሚኒስትሩን ማብራሪያ ጠይቀዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ጥያቄ ያቀረቡት ብቸኛው የግል ተመራጭና የምክር ቤት አባል ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ ሲሆኑ፣ በሰፋፊ የግብርና መሬት ላይ በሚካሄደው ኢንቨስትመንት የምዕራባዊያን ኩባንያዎች እንዲሳተፉ ለምን የማስተዋወቅ ሥራ አይሠራም በማለት፣ የህንድና የቻይና (የምሥራቁ የዓለም አገሮች) ኩባንያዎች የጐላ ተሳትፎ ሚዛኑን መጠበቅ ይገባዋል የሚል መልዕክት ያለው ጥያቄያዊ አስተያየታቸውን አቅርበዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ኃላፊዎች በጋራ ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ወንድይራድ ማንደፍሮ በሰፋፊ መሬቶች ላይ ለሚካሄድ የግብርና ኢንቨስትመንት ሲባል አንድም ሰው ከቀዬው እንዲፈናቀል አልተደረገም ብለዋል፡፡
ሁለቱም ምስሎች በጋምቤላ አካባቢ ከሳተላይት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ቀያዮቹ ነጥቦች በሙሉ በመሬት ነጠቃ ከቀያቸው የተፈናቀሉና ቤታቸው የፈረሰ አባወራዎችን ሲሆን ቢጫዎቹ ደግሞ ተፈናቃዮቹ በግዳጅ የሰፈሩበትን ነው፡፡
ሁለቱም ምስሎች በጋምቤላ አካባቢ ከሳተላይት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ቀያዮቹ ነጥቦች በሙሉ በመሬት ነጠቃ ከቀያቸው የተፈናቀሉና ቤታቸው የፈረሰ አባወራዎችን ሲሆን ቢጫዎቹ ደግሞ ተፈናቃዮቹ በግዳጅ የሰፈሩበትን ነው፡፡
“የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት የሆኑ ነፃ መሬቶችን ብቻ ነው ለሰፋፊ የግብርና ኢንቨስትመንት የምንሰጠው፡፡ ማንም ከቀዬው አልተፈናቀለም፤” በማለት አስረድተዋል፡፡
በሰፋፊ መሬቶች ላይ የሚደረግ የግብር ኢንቨስትመንት ከፍተኛ የገንዘብ አቅም እንደሚጠይቅ የተናገሩት ማኒስትር ዴኤታው፣ ከዚህ ጋር የተያያዙ ችግሮች መኖራቸውን ግን አልሸሸጉም፡፡
በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም ሆነ በባለሀብቶቹ ቀደም ብሎ ተይዞ የነበረው እምነት ኢንቨስትመንቱ ቀላል እንደነበር፣ ነገር ግን በተግባር ሲታይ ጊዜ የሚወስድና አቅም የሚጠይቅ እንደነበር ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ለባለሀብቶቹ የሚሰጠውን የመሬት መጠን እየቀነሰ እንደሚገኝ፣ በአጠቃላይ ግን ትልቅ አቅም የሚፈጥር ዘርፍ እንደሚሆን አብራርተዋል፡፡
በዚህ ዘርፍ በፌዴራል መንግሥት ፈቃድ የተሰጣቸው ባለሀብቶች 43 መሆናቸውን አስረድተው፣ ከእነዚህ ውስጥ 15 የሚሆኑት ብቻ የውጭ ኩባንያዎች ናቸው ብለዋል፡፡ በመሆኑም በዘርፉ በአብዛኛው እየተሳተፉ የሚገኙት የአገር ውስጥ ባለሀብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው በበኩላቸው በኢትዮጵያ ውስጥ መሬት መቀራመት የለም ብለዋል፡፡
አሁን ባለው የዓለም የዕድገት ሁኔታ የገንዘብ አቅም ያለው በምሥራቃውያን አካባቢ መሆኑን፣ ምዕራባውያኑ በዘርፉ ያልተሳተፉት የአቅም ችግር ስላለባቸው እንደሆነ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
“የመሬት መቀራመት ጉዳይ እየተነሳ ያለው ከዚሁ የዓለም ጂኦ ፖለቲካ አካባቢ ነው፡፡ ከምሥራቅ የዓለም አገሮች ወደ አፍሪካ እየመጣ ያለ ኢንቨስትመንት ስለማይወደድ ነው፤” ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩም ሆነ የሥራ ባልደረቦቻቸው የውጭ ኩባንያዎቹ እያገኙ ስላለው ከፍተኛ ብድር ግን ማብራሪያ ሳይሰጡበት ታልፏል፡፡
የግብርና ሚኒስቴር የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም እንደሚያስረዳው፣ በ2006 ዓ.ም. የመኸር ወቅት 253 ሚሊዮን 805 ሺሕ 340 ኩንታል ምርት ሊገኝ እንደሚችል፣ ይህም ካለፈው ዓመት ዘጠኝ በመቶ መጨመሩን ነው፡፡ (ሪፖርተር)
http://www.goolgule.com/why-ethiopia-needs-foreign-farmers/

በጎንደር የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና የቅስቀሳ ቡድን አባላት በፖሊስ ታሰሩ

ጥር 22/2006 (BlueParty Ethiopia)

እስካሁን 14 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በጎንደር የታሰሩ ሲሆን ከታሰሩት ውስጥ አራት ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች ይገኙበታል፣
1. ጌታነሀ ባልቻ (የድርጅት ጉዳዮች ሃላፊ)
2. ብርሃኑ ተ/ያሬድ (የሀዝብ ግንኙነት)
3. ዮናታል ተስፋዬ (የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ)
4. ይድነቃቸው ከበደ (የህግ አማካሪ)
ሁለት ሹፌሮች እና አንድ ፊልም አንሺም (Cameraman) ከታሳሪዎቹ ውስጥ ናቸው፣ በአሁኑ ስዓት ታሳሪዎቹ በወረዳ ሁለት ፖሊስ ጣብያ ሲገኙ ጌታነሀ ባልቻ (የድርጅት ጉዳዮች ሃላፊ) እና አግባው ሰጠኝ ወደ ጎንደር ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ተወስደዋል።
ጥር 25 2006 ዓ.ም. የኢትዮ ሱዳን ድንበር ማካለልን ህገወጥነት በተመለከተ በጎንደር መስቀል አደባባይ የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ ከአዲስ አበባ የተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ ሉኡካን ቡድን በዛሬው እለት በጎንደር ከተማ በቅስቀሳ ላይ እንዳሉ ከፍተኛ እንግልት እየደረሰባቸው ሲሆን ጎንደር የገባው ቡድን በጠቅላላ በእስር ላይ ይገኛል፡፡ የቅስቀሳው አባላት በጎንደር ከተማ እና በተለያዩ ቦታዎች ቅስቀሳውን እንደጀመሩ የፓሊስ አባላት ፈቃድ ስለሌላችሁ መቀስቀስ አትችሉም ያሏቸው ሲሆን አባላቱም በህጉ መሰረት ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ የሚጠበቅብን ስላልሆነ ለሚመለከተው አካል ያሳወቅን በመሆናችን ህጋዊዎች ነን በማለታቸው ፓሊስ በማዋከብና በመደብደብ ጎንደር ከተማ በሚገኘው ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ በአሁኑ ሰአት ከፍተኛ መጉላላትና እንግልት እያደረሱባቸው ይገኛል፡፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችም ፖሊሶቹን ምን አደረጓችሁ በማለት እና ይህ ጉዳይ የኛም ጉዳይ ነው በማለት አባላቱን ከፖሊስ ለማስለቀቅ የተቻላቸውን ያደረጉ ሲሆን ፖሊስም ሐይል በመጨመር ህዝቡን በዱላ በማባረር የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና የቅስቀሳ ቡድኑን እንዲሁም የጎንደር የፓርቲው መዋቅር አባላትን ጨምሮ አስረዋቸዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የጎንደር ነዋሪ ህዝብ የፖሊስ ጣቢያውን በመክበብ የታሰሩት እንዲፈቱ እየጠየቀ ሲሆን ሰልፉ በተያዘለት ቀን እንዲደረግ ለማድረግ ሌላኛው የሉኡካን ቡድን ከአዲስ አበባ በዛሬው እለት መንቀሳቀሱ ታውቆአል፡፡
A protest call in Gonder, Ethiopia
http://ecadforum.com/Amharic/archives/10862/

Wednesday, January 29, 2014

እስክንድር ነጋ የ2014 የነጻነት ወርቅ ብዕር ተሸላሚ ሆነ


Golden Pen of Freedom


የዓለም የጋዜጦችና ዜና አታሚዎች ማኅበር (WAN-IFRA) የ2014 የነጻነት ወርቅ ብዕር ሽልማቱን ለኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛና አሳታሚ እስክንድር ነጋ እንዲሰጥ መወሰኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቆዋል:: ህወሃት/ኢህአዴግ “የጸረ ሽብር ሕግ” በማለት ባወጣው አዋጅ ሰበብ እስክንድር ነጋ 18 ዓመት እንዲታሰር የተበየነበት መሆኑን መግለጫው ጨምሮ ገልጾዋል::
መግለጫው እስክንድርን ጨምሮ ሰሎሞን ከበደ፣ ውብሸት ታዬ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ዩሱፍ ጌታቸው ከእስር እንዲፈቱ አሳስቦዋል:: ኢትዮጵያን በቅርቡ የጎበኙት የማኅበሩ ፕሬዚዳንት በአገሪቱ የሚገኙ ጋዜጠኞችና አታሚዎች በፍርሃት የጋዜጠኝነታቸውን ሞያ እንደሚያከናውኑ መታዘባቸውን አስታውቆዋል::
ሽልማቱ በሰኔ ወር በቶሪኖ ጣሊያን በሚደረገው የዓለም የጋዜጦች ኮንግረስ፣ የዓለም አርታኢዎች መድረክ እና የዓለም ማስታወቂያ ሥራ መድረክ ጣምራ ስብሰባ ላይ ይሰጣል::
***********************************

2014 Golden Pen of Freedom awarded to jailed Ethiopian journalist

2014-01-27
Eskinder Nega, an Ethiopian publisher, journalist and blogger who is serving an 18-year jail sentence under anti-terror legislation, has been awarded the 2014 Golden Pen of Freedom, the annual press freedom prize of the World Association of Newspapers and News Publishers (WAN-IFRA).
Mr Nega was arrested on September 14, 2011 after publishing an article criticising his government’s use of the 2009 Anti-Terror Proclamation to jail and silence critics, including Ethiopian actor and activist Debebe Eshetu.  He was sentenced on 23 January 2012 and denounced as belonging to a terrorist organisation.
In making the award, the WAN-IFRA Board sent a message to the Ethiopian government that misusing anti-terror legislation to jail journalists and those critical of his government is unwarranted and against international protocols, including the Vienna Declaration on Terrorism, Media and the Law.
“This award recognises the courage of Eskinder Nega to speak out despite the risks that saw him jailed under his country’s draconian and overly broad anti-terror laws,” said WAN-IFRA President Tomas Brunegård, speaking on behalf of the Board.
“We call on the Ethiopian government to release Eskinder Nega and all journalists convicted under the sedition provisions, including Solomon KebedeWubset TayeReyot Alemu,and Yusuf Getachew”, said Mr Brunegård, who recently visited Ethiopia as part of an international mission that found that the country’s publishers and journalists practice journalism in a climate of fear.
The Golden Pen of Freedom is an annual award made by WAN-IFRA since 1961 to recognise the outstanding action, in writing or deed, of an individual, a group or an institution in the cause of press freedom. More on the Golden Pen can be found at http://www.wan-ifra.org/node/31099
The award will be presented on 9 June during the opening ceremonies of the World Newspaper Congress, World Editors Forum and World Advertising Forum, the global summit meetings of the world’s press, to be held in Torino, Italy.
In an opinion piece published in the New York Times, Mr Nega said of his imprisonment: “I’ve never conspired to overthrow the government; all I did was report on the Arab Spring and suggest that something similar might happen in Ethiopia if the authoritarian regime didn’t reform… I also dared to question the government’s ludicrous claim that jailed journalists were terrorists.”
WAN-IFRA has been vocal in their opposition to Ethiopia’s misuse of anti-terror legislation, writing to late Prime Minister H.E. Meles Zenawi in 2012 requesting the immediate release of Mr Nega and most recently demanding his release, along with four other imprisoned journalists, in a joint international press freedom mission to Ethiopia, conducted with the International Press Institute. The full report from the international press freedom mission can be found at http://www.wan-ifra.org/node/97172
Mr Nega opened his first newspaper, Ethiopis, in 1993, which was soon shut down by authorities due to its critical reporting. He then, along with his wife Serkalem Fasil, managed Serkalem Publishing House, responsible for newspapers such as Asqual, Satenaw and Menelik, all of which are currently banned in Ethiopia.  He has also had his journalist’s licence revoked since 2005, but continued to publish articles despite the ban.
Mr Nega is no stranger to being imprisoned due to his writings. He was detained at least seven times under Prime Minister Meles Zenawi.  This included a 17-month jail sentence, along with his wife, on treason charges for their critical reporting on the Meles government’s violent response to peaceful protests that followed the disputed 2005 elections.
WAN-IFRA, based in Paris, France, and Darmstadt, Germany, with subsidiaries in Singapore and India, is the global organisation of the world’s newspapers and news publishers. It represents more than 18,000 publications, 15,000 online sites and over 3,000 companies in more than 120 countries. Its core mission is to defend and promote press freedom, quality journalism and editorial integrity and the development of prosperous businesses.
Inquiries to: Larry Kilman, Deputy CEO and Executive Director of Communications and Public Affairs, WAN-IFRA, 96 bis, rue Beaubourg, 75003 Paris France. Tel: +33 1 47 42 85 07. Fax: +33 1 42 78 92 33. Mobile: +33 6 10 28 97 36. E-mail: larry.kilman@wan-ifra.org
http://www.goolgule.com/2014-golden-pen-of-freedom-awarded-to-jailed-ethiopian-journalist/

የኢትዮጵያውያን ምሬት፡ የሕይወት ማሽቆልቆልና በፍርሃት መሽማቀቅ አፋጣኝ መፍትሄ ይሻል

Posted by The Ethiopia Observatory

ኢትዮጵያ በሕወሃት ዘመነ አመራር የታወቀችባቸው ብዙ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ። ብዙ “እንዴ!”የሚያሰኙ ጥሩ ሀሳቦችም ፈልቀዋል – አፈጻጸማቸው እትየለሌ ቢሆንም። ከነዚህም መካከል መሠረተ ልማት፡ በጤናና በትምህርት መስኮች መሻሻሎች መታየታቸው ወዘተ መልካም ይነገርላቸዋል – የቢል ጌትስን የራስ ተጠቃሚነትና ኢምፓየር ግንባታ ወደጎን ትተን! በዕጦት ደረጃም በሀገራችን የሰብዓዊ መብቶች አለመከበር፣ የፍትህ አለመኖርና ለአብዛኛው ሕዝባችን የምግብ ዕጦት ዋና ዋና ተጠቃሽ ችግሮች ናቸው።
Prime Ministers Katainen and Hailemariam (Credit: ERTA)
Prime Ministers Katainen and Hailemariam (Credit: ERTA)
ለምሳሌም ያህል፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 30 ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግንና መንግስትን መቃወምን ግልጽ ቢያደርግም፡ እሁድ ዕለት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመሰጠት ለመቃወም: ለሚመለተው አሳውቀው ሰላማዊ ሰልፍ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ሲሉ የአዘጋጁ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት ጎንደር ውስጥ ተይዘው ታስረዋል። በተመሳሳይ መንገድ ትግራይ ውስጥም የአረና አመራሮች ሕዝቡን ቀሰቀሳችሁ በሚል ውንጀላ አዲግራት ውስጥ አመራሩና አባሎቹ ክፉኛ ተደብድበዋል – ጉዳት የደረሰባቸውም ሕክምና ለመሻት ተገደዋል። ይህንኑ አስመልክቶ፡ አንዱ ተደብዳቢ መምህር አብርሃ ደስታ የሚከተለውን ጽፏል፡
    “ህወሓቶች በተግባራቸው ሊያዝኑ ይገባል። ህዝብን ፖለቲካ እንዲያውቅና ራሱ ከጭቆና እንዲከላከል ለማገዝ በምንሞክርበት ግዜ መንግስት ወደ ተራ የሽፍትነት ተግባር መሰማራቱ የሚያስደምም ነው … እኛ ለህዝብ ነፃነት ነው የምንታገለው። ትግላችን ሰለማዊ ነው። ወታደርና ፖሊስም የለንም። እኛ ያለን ህይወት ነው። ያለችንን ህይወት ለህዝብ ደህንነት ስንል መስዋእት አድርገናል። በህዝብ ፊት ተደብድበናል። በፖሊስና አስተዳዳሪዎች ፊት ተደብድበናል። እኛ መክፈል ያለብን ህይወትን ነው።”
ይህ በግልጽ የሚታየው የዛሬይቱ ኢትዮጵያ የስብዓዊ መብቶች አንጸባራቂ ሥዕል ነው። ይህ ሁኔታ በየቀኑ በተለያየ መልኩ ሀግሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ያለ የመንግሥት ሕገ ወጥነት ነው!
በኤኮኖሚው መስክ ያለው ችግር ግዙፍ ነው። ድህነት ከመቀረፍ ይልቅ፡ ሥር እየስደደ መሆኑን ብዙዎች ያማርራሉ። ለጥቂቶች ግን ሀገሪቱ ምድራዊ ገነት ሆናለች። ሕዝቡ እየተደበደበም፡ በየቀኑ አልዋጥ ባይ ፕሮፓጋንዳ በግድ እየተጋተ ነው!
በዚህ ሁኔታ ውስጥ ነው ለብዙዎቹ የአዲስ አበባ መሽቀርቀር እንደአጠቃላይ የሃገሪቱ የልማትና ዕድገት መለኪያ ተደርጎ እንዲወሰድ የተቀነባበረ ጥረት የሚድረገው። የምርጫ ዘመን በመቃረቡ፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በቅርቡ ስንዴ ለውጭ ገብያ ሻጭ ልትሆን ነው በማለት ጥር 18፣ 2014 አርሲ ሆነው ማስማታቸው ልብ ሊባል ይገባል። ነገር ግን ኢትዮጵያ በልማት ገና ሀ ሁ … ላይ ናት – በምግብ 40 በመቶ የሚሆነውን ሕዝቧን በቀን ሶስቴ ሳይሆን፡ አንዴም መመገብ ያልቻለች አገር ናት! ይህ በመሆኑ አይደል እንዴ የምዕራቡ ዓለም፡ በቋሚነት ከ10 በመቶ በላይ የሆነውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ክዓመት ዓመት በዓለም አቀፍ እህል ዕርዳታ ሕይወት በመስጠት ላይ ያለው?
ከሁሉም ጎልቶ የሚነገርለትና የሕወሃት ሰዎችም ቶሎ የሚስፈነጠሩበት የአገሪቱ ከትላልቅ ጦርነቶች መላቀቋ ነው። ስለዚህም የሕወሃት ሰዎችና ደጋፊዎቻቸው በመመጻደቅ ሲናገሩ መስማቱ የተለመደ ሆኖአል። በዚህም መነሻነት፡ እንዲህ ይላሉ: ባለፉት 20 ዓመታት፡ ሕወሃት ለረዥም ዘመናት አገሪቱን ያደሙትን ጦርነቶች አቁሞ ልማት ላይ እንድታተኩር አደረገ የሚባለው በብዛት ይሰማል። የሕወሃት ስዎችም ይህ በተደጋጋሚ እንዲነገርላቸው ብዙ ጥረቶች አድርገዋል፡ እያደረጉም ነው። እራሳቸውም በተደጋጋሚ እራሳቸውን በዚህ ሲያሞካሹ ይሰማል፤ ለውጭ የፕሮፓጋንዳ ድርጅቶችም ይህንን እንዲያስተጋቡላቸው፡ ከፍተኛ ክፍያዎችን በየጊዜው ፈጽመዋል።
እስከዛሬ አጥጋቢ ግንዛቤ ያላገኘው ግን፡ ድሮም ሆነ ዛሬ የጦርነቶች አጋጋይ ሕወሃት መሆኑ ነው። የኤርትራንና የትግራይን መገንጠል ጉዞ በተግባር ሲተረጉም ኖረ። ቀኑ ደርሶ ጅብሃ ሲገነጠል፡ ሕወሃት ባዶ የሥልጣን ወንበር ስለታየው፡ ኢትዮጵያዊነትን መረጠ። በትግል አጋሩ ጅብሃ ዘንድ ይህ እንደክህደት እንዳይታበት – በሰላም ሂዱ፡ ኢትዮጵያ ከእናነተ ሰላም እንጂ ሌላው ቀርቶ የባህር በር እንኳ አያስፈልጋትም አለ። ይህንን አስመልክቶ፡ በየካቲት ወር 1994 ስብሃት ነጋ ለዓለምሰገድ አባይ በሰጡት ቃለ መጠይቅ የሕወሃት ቀደምት ፓሊሲ መገንጠል ሆኖ እስከ 1985 መቆየቱን ያረጋግጣሉ። ከቃለ መጠይቁ ውስጥ በጣም አስገራሚው ነገር ግን፡ ብዙ የሕወሃት ተዋጊዎች ኢትዮጵያዊነትን ገና ድሮ አሽቀንጥረው የጣሉ በመሆናቸው፡ ዛሬም ቢሆን በተለይ ከአማራ ጋር ኢትዮጵያዊ ሆኖ መገኝትን በሙል ልብ አለመቀበላቸውን ነው ያመላከቱት [See Identity Jilted: Re-imagined Identity (1998)]።
ያለፈው አልበቃ ብሎ፡ ዛሬም ሕወሃት ሀገሪቱ ውስጥ ሽብርና ፍርሃት በማንገስ የውስጥ ግጭቶችን በመተንኮስ: የተለያዩ ብሄረስቦችን አባሎች በማፈናቀልና ችግሮችን በማባባስ ተጠቃሚ ለመሆን ሲምክር ይታያል – ድ/ር ቴድሮስ ፍጹም “እኔ ያለሁበት ፓርቲ ውስጥ ይህ አይደረግም!” ብለው ዝናቸውን አጋልጠው ቢገዘቱም። ነገሩ ግን፡ ዛሬም በምሥራቅ በተለያያዩ የኦሮም ክፍሎችና ኢትዮጵያውያን ሶማሌዎች መካከል፡ በደቡብም እንዲሁ በተለያዩ ጎሣዎች መካከል፡ አማራንና ኦርሞችን በማጋጭት፡ ጥላቻና መቃቃርን በዜጎች መካከል ለመፍጠር ብዙ ሲሞክር ቆይቷል። አንዳንድ ቦታዎችም፡ ለምሳሌ ቦረና፡ ተሳክቶለት ስሞኑን የብዙ ዜጎች ደም ፈሷል፤ ሕይወትም ተቀጥፏል። ቤት ንብረቶችም ተደምስሰዋል። ሌላው ቀርቶ፡ የሕክምና ባለሙያ የነበሩት የአገር አስተዳደር ሚኒስትሩ – የዛሬው የሃይማኖትች ጉዳይና የጸረሽብር ኤክስፐርቱ ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም – ኬንያ በሥጋቷ ምክንያት (2012ን በማስታወስ) ልተቀስቅሳቸው ብትሞክርም፡ ነገሩ አውቆ የተኛ ቢነቀንቁት አይሰማ ሆኖ እሳችውም እንደክረምት ድብ ክፉኛ አሸልበዋል።
ለማንኛውም፡ በዓለም ላይ እንደሕወሃት የተሳካለት የለም – ዕድሉን ሃገራችንን ለማሻሻል በሚገባ አልተጠቀመበትም እንጂ! ስለሆነም ክሥራ ይልቅ ፕሮፓጋንዳ፡ ዕውነትን ተናግሮ ችግሮችን በጋራ ከመፍታት ይልቅ፡ ሁሉንም ስው ማሞኘት እንችላለን በሚል ትዕቢት ብዙ የሚያሳፍሩ ተግባሮች ሲያከናወን ይታያል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፡ በበጎነታችው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ደጉን የሚመኙ የውጭዎቹ የፖለቲካ፡ የዲፕሎማሲና ኅብረተስባዊ መሻሻሎችን አራማጆች ይህንን የሕውሃትን የሰላም ማስፈን የዋህ መስል ቅጽል በአመኔታ የሚጋሩት በሁለት ተክፈለው ይታያሉ፡ –
(ሀ) በእውነትም ጦርነትና የንጹሃን ዕልቂት መቆሙን፡ ኢትዮጵያ ክድህነት ተላቅቃ ማየት የሚሹ ወገኖች፤
(ለ) ጊዘው የበለጸጉት ሃገሮች ወደታዳጊ ሀገሮች ውስጥ ዘልቀው በመስፋፋትና በኢኮኖሚ ትብብር ስም የራሳቸውን ኤኮኖሚያዊ፡ የበላይነት ማቆየት የሚሹበት፡ ፖለቲካዊና ስትራተጂካዊ ጥቅሞቻቸውን የሚያበራክቱበት በመሆኑ፡ ከላይ ከተጠቀሱት ጋር ተዳብረው፡ የሕወሃትን ገድል መተረኩ፡ ለሚሹት ዓላማ አንድ ጥቅም ትስስሮሽ መፍጠር የሚያስችል መሣሪያ አድርገው የሚጠቀሙበት ወገኖችም እዚሀ ውስጥ ተስልፈዋል።
ከላይ የተመለከቱት ከተለያየ አግጣጫ ተነስተው ሁለቱም አንድ የሚገናኙበት መጋጠሚያ፡ ስለኢትዮጵያ በጎ ነገር እንዲስተጋባ ማድረጋቸው ነው። በተለይም በሁለተኝው ክፍል የሚገኙት፡ በተቻለ መጠን ስለኢትዮጵያ በጎውን በማጋነን፡ የሕወሃትን የስብዓዊ መብቶች ጽልመት፡ ጎስኝነት፡ ሙሰኝነት የሚሸፋፍን አመለካከት በምዕራባውያንም ሆነ ምሥራቃዊ ሚዲያዎች ላይ በጊዜው ያስደስኮሩላቸዋል።
በተጨማሪም፡ እነዚህ ሀገሮች ለኢትዮጵያ ግዙፍ ዕርዳታ መፍሰሱን ይደግፋሉ። ነገር ግን ይህ ዕርዳታ በብዙ መስኮች – በተለይም በግብርናው – መስክ የሀገሪቱን ችግሮች፡ በምግብ ምርት እራስን ከማስቻል ይዘት ስሌለው፡ ትኩረታችውም ሆነ ጥረታቸው – በዘለቄታ ሀገሪቱን ከምግብ ዕርዳታ ተመጽዋች ነጻ ለማድረግ አላስቻለም። በመሆኑም፡ እየተደረገ ያለው፡ ትላንት እንደነበረ ሁሉ ዛሬም ኢትዮጵያ አንድ ሶስተኛ መንግሥታዊ በጀቷን በዓለም አቀፍ ዕርዳታ ተመጽዋችነት ላይ የተመሰረተ ሆኖ የውስጥና የውጭ ፖሊሲዋን በማክራየት እንድትቀጥል አስገዳጅ ሁኔታ ተፈጥሮባታል።
በአሁኑ ወቅት፡ በተለያዩ ምክንያቶች (የስብዓዊ መብቶች አለመከበር ችግር፡ የየራሳቸው የሀገሮቹ የኢኮኖሚ ችግሮች) መንስኤነት፡ ከለጋሽ ሀገሮች በቀጥታ የሚገኝው ዕርዳታ በክፍተኛ ድረጃ ቀንሷል (ክአሜሪካና እንግሊዝ በስተቀር)። በዚህም ምክንያት የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚስጠውን ብዙውን የዕርዳታና ብድር ጫና ድርሻ ተሸካሚ ሆኖአል።
ለምሳሌ፡ ሌላው ቀርቶ ስብዓዊ ዕርዳታን እንኳ በተመለከተ፡ 12 የአውሮፓ ኅብረት ሀገሮች (እንግሊዝን አይጭምርም) በ2012 ለኢትዮጵያ በባይላተራል መንገድ ለዕርዳታ ያዋጡት €24 ሚልዮን ሲሆን፡ በ2013 ይህ መዋጮ ወደ €12.4 ሚልዮን ወርዷል። ከነዚህም መካከል ትልቁን ቅናሽ ያደረገችው ጀርመን ናት – ከ€8.2 ሚልዮን ወ €4.2 ሚልዮን ዝቅ በማድረግ። በመሆኑም፡ከዚህም ከዚያም አስባስቦ የበጀት ምንጮች በማስባስብና ተጨማሪ ምክንያቶች በመፍጠር (ነፍስ ወክፈ መልሶ ማቋቋም) በ2013 እንዳደረገው፡ የአወሮፓ ኮሚሽን በ 2011-2013 12 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ለመርዳት እንዲቻል €130 ሚልዮን ለግሷል።
አሁን ለሁሉም ለጋሾች ከባድ የሆነው “የልማት” ዕርዳታውም እንዲሁ በበዙ ጥያቄዎች ላይ መውደቁ መሆኑ ይሰማል።
በዓለም ዙሪይ ያለፉው ሩብ ምዕተ ዓመት የልማት ጊዜ በመሆኑ፡ ብዙ ታዳጊ አገሮች ከፍተኛ ተጠቃሚ ሆነዋል። ኢትዮጵያ ይህ ዕድል ቢገጥማትም፡ መሣሪያ ያነገቡት የሕወሃት ሰዎችና አጫፍሪዎቻቸው ግንባር ቀድም ተጠቃሚዎች የሆኑበት ሥርዓት በመዘርጋቱ፡ የትላንቱ ጦረኞችና የዛሬዎቹ የስላም ደጋፊ-መስል የአንድ ብኄረስብ ሰዎች፡ ሆን ብለው ዕኩልነትን የሚጻረር የፖለቲካ፡ የኤኮኖሚ፡ የደህንነትና ማኅበራዊ ፓሊስዎችን በኢትዮጵያ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።
ይህ ግን ዘላቂ መሠረት ስሌለው፡ ዛሬ የኤኮኖሚው የጥንድ ዕድገት ውደሳው ጋብ ብሎ፡ ሀገራችን የመንግሥት ብልግናና የሃስት ፕሮፓጋንዳ ከሚመገቡት መካክል ወድቃለች። በዚሁም ምክንያት (ሽፋኑ የውሃ ዕጥርረት፡ ድርቀት፡ የሃይማኖትና የብኄረቦች አለመቻቻልና ግጭቶች ላይ ቢመካኝም)፡ ተደጋጋሚ ዓለም አቅፍ ጥናቶችኢትዮጵያ ከሚወድቁት የአፍሪቃአገሮች (Failed States) መካከል ተደምራ፡ የወደፊት ጽዋዋ አስፈሪ እንደሚሆን ቀንደኛ ደጋፊዎቿ ድምዳሜ ላይ መሆናቸውን በግልጽ የምንሰማበት ዘመን ላይ ደርስናል።
ድሮስ ቢሆን፡ የሕዝብ ዓመኔታ ያጣ መንግሥት፡ መሣሪያውን ደግኖ በኅይል ለመግዛት ከመሞከር ውጭ ምን አማራጭ አለው? ጊዜው የጥላቻ፡ የክፋትና የቂም በቀል በመሆኑ፡ በአንድ በኩል፡ የሕወሃት ስዎች ዘረፋ ላይ የተሰማሩ ሲሆን፡ በሌላ በኩል ደግሞ፡ የኢትዮጵያውያንን ስብዓዊ መብቶች በመግፈፍና መርገጣቸውን በማባባስ፡ ሃገሪቱን ወደ ቀውስ ጎዳን እየገፉ ናቸው። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዴት ዕድገት ይኖራል?
እንዲያውም፡ የራሱን የአገዛዝ ዘመን ለማራዘም ሲል፡ የኢትዪጵያ ሕዝብ ፍላጎትና አመለካከት ሳይጠየቅ ኤርትራን በፊርማው እንድትገነጥል ያደረገ፡ አገሪቱን የባሀር በር ለማሳጣት የደፈረ የመንግሥታዊ ባህልና ኃላፊነትና ግንዛቤ የሌለው ሕወሃት፡ ለሱዳን የኢትዮጵያን መሬት ቆርጦ ለመስጠት ዝግጅት ላይ መሆኑ ሕዝቡን በቃ! የሚል ድምዳሜ ላይ ማድረሱ አያጠራጥርም!
በዓለም ታሪክ ውስጥም ሕወሃት “ታዋቂ” የሚሆነው፡ ራሱን ሥልጣን ላይ ለማቆየት፡ የሀገርን ልኡላዊነትና መሬት ቆርሶ ለጎረቤት ሀገርና ለከፍተኛ ብድር ስጭና ገንዘብ ለዋጭ አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ ነው።
ዛሬም ሆነ ነገ፡ ለሀገራችን ዘላቂው መፍትሄ ግን መንግሥት የሕዝብን ፍላጎት ለማክበር መቻሉና ለዚህም ተጠያቂነት ያለበት ሥርዓት መዘርጋቱ ነው። ይህንን ለማድረግ፡ አሁንም ትንሽ የተስፋ መስኮት አለ – የሕውውሃት ስዎች ኃላፊነት የሚስማቸው ቢሁን። ይህ ለሕወሃትና ግብረአበሮቹ ተቀባይ ሳይሆን ቢቀር፡ ቀሪው ምርጫ ሕዝቡ እየተረገጠ መቀጠል፡ ወይንም እነርሱ ከመድረኩ መወገድ ነው።
እስካሁን በዚህ ድህረ ገጽ ይህንን አሳብ አላራመድንም ነበር። የሁኔታው አስከፊነት ግን አሁን የወቅቱ አስፈላጊ እርምጃ አድርጎታል!
http://ecadforum.com/Amharic/archives/10852/

ኳሱ በማን እጅ ነው? (ይድነቃቸው ከበደ)


Ethiopian political commentator from Addis Ababa, Ethiopia. Ydnekachew Kebede
ይድነቃቸው ከበደ
ከአምስት ወር በፊት የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የአዲስ ዓመት የሥራ ዘመን መጀመር አስመልክቶ በጋራ ባአካሂዱት ጉባዔ አዲሱ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመም ፕሬዚዳንታዊ የመክፈቻ ንግግር ማድረገቸው የሚታወቅ ነው፡፡ የፕሬዚዳንቱ የንግግር  ይዘት መንግሥት በ2006 ዓ.ም. ትኩረት ሊያደርግባቸው የሚገቡ ዋና ዋና ተግባሮች ላይ ብቻ ያተኮረ ነበር፡፡ይሁን እንጂ የፕሬዚዳንቱ ንግግር በሕግ መንግስቱ በተሰጣቸው ሥልጣንና ተግባር መሠረት የተደረገ ንግግር ስለመሆኑ የሚያመላክት አንዳችም ነገር አላየሁበትም፤በመሆኑም የፕሬዚዳንቱ ንግግር በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢነገር የተሻለ ይሆን ነበር ግን በሁለቱም ቢነገር ውጤቱ ዉሃ ቢወቅጡት እንቦጭ ነው፡፡
በዚህም መሠረት ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ባቀረቡት የመክፈቻ ንግግር ላይ ሊካተቱ የሚገባቸው ነገር ግን ያልተካተቱ፣ እንዲሁም መካተት አልነበረባቸውም ያሏቸውን በመለየት አቶ ግርማ ሰይፉ ጥያቄና አስታየት አቀርበዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም  ደሳለኝ በምክር ቤቱ በመገኘት በአቶ ግርማ ነጥቦች ዙሪያ ምልሽ መስጠታቸው የሚታወቅ ነው፡፡ይሁን እንጂ ምላሻቸው ሙሉ በሙሉ በሚያስብል ደረጃ ስኬታማ አልነበረም ለዚህም ዋንኛው ምክንያት የመንግስት የአስተዳደር ብሉሹነት ነው ፡፡
የፕሬዚዳንቱ የመክፈቻ ንግግር ከተደረገ እና የመንግስት አቋም በጠቅላይ ሚኒስተር አቶ ኃይለማርያም ከተገለፀ ስድት ወር ሊሞላው የተወሰኑ ቀናት ይቀረዋል፡፡በሚቀሩት የተወሰነ ቀናት ውስጥ የግማሽ ዓመት ወይም የስድስት ወር የመንግስት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ምን ያኸል ውጤታማ ነበር የሚለውን በመንግስት እይታ ወደፊት የሚገለፅ ቢሆንም ወደ ጉሮሮ ጠብ ያላለ እድገት እና የዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች የታፈነበት ወራት መሆኑ ግልፅ ነው፡፡
ይህ በእንዲ እንዳለ ለዘህ ፁሁፍ መነሻ የሆነው ዋና አሳብ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከአምስት ወር በፊት በፓርላማ ያደረጉት ንግግር ነው፡፡ ንግግራቸውም ስለተቃውሞ ሠልፍ እና ስለህዝባዊ አብዮት የሰጡት ማብራሪያ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ጠ/ሚ ኃይለማርያም ስለ አብዮት ያላቸው ፍራቻ ከምን እንደመነጨ መገመት ቀላል ቢሆንም ስለ ህዝባዊ ስብሰባና የተቃውሞ ሠልፍ የያዙት ሃሳብ ግን የመንግስታቸው እየታ ጤናማ አለመሆኑ በሚገባ የሚሳይ ነው፡፡
በወቅቱ አቶ ኃይለማርያም እንዲህ ነው ያሉት ‹‹ ሌት ተቀን የጐዳና ላይ ነውጥ አምጥቼ ገዥውን ፓርቲ እቀይራለሁ ብሎ አቅዶ መንቀሳቀስ ወንጀል ነው፤ የጐዳና ላይ ነውጥ በዚች አገር ላይ እንሞክራለን የምትሉትን አቋሙ፡፡ ይህንን ለሕዝቡም ጭምር ነው የምናገርው በቂ መረጃ ስላለን ነው በተግባር ላይ ስላልዋለ ምንም ማድረግ ስለማንችል እንጠብቃለን፡፡ በተግባር ላይ የማዋል ሙከራ ካለ ትክክል ስላልሆነ እርምጃ እንወስዳለን ‹ኳሱ› በእናተ እጅ ነው ››፡፡ በማላት በሰማያዊና በአንድነት ፓርቲ እየተደረጉ ያሉ ሕዝባዊ ስብሰባና የተቃውሞ ሠልፎች መንግስታቸው በምን መልኩ እንቅስቃሴውን እየተከታተለ እንደሆነ እና ሊወሰድ የታሰበውን እርምጃ የሚያመላክት ነው፡፡
የአቶ ኃይለማርያም ማስጠንቀቂያ በቀጥታ የተላለፈው አንደኛ ለህዝብ ሲሆን ሌላው ደግሞ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ነው፡፡ በእርግጥ ይህ ንግግር ከተደረገ ወራቶች የተቆጠሩ ቢሆንም መንግስት ከማስጠንቀቅ ባለፈ የተፈራውን ህዝባዊ አብዮት እና የተቃውሞ እንቅስቃሴ ሊገታ የሚያስችል አንድም የመንግስት መልካም አስተዳደር በአገራችን ላይ አልታየም፡፡ ለዚህም እንደማሳያ  ብዙ ምክንያቶች መጥቀስ ቢቻልም በእያንዳንዱ ሰው ንሮ ላይ የሚታይ ችግር መልሶ መድግም ለቀባሪው እንደማርዳት ነው፡፡ በተጨማሪ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሰላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ሊያቀዘቅዝ ሳይሆን የበለጠ ሊያነሳሳ የሚያስችል የመንግስት የአስተዳደር ሽባነት ጎልቶ የታየበት ወራት ነው፡፡ በመሆኑም ለእዝብ እና ለተቃዋሚ ፓርቲዎች የተላለፈው የመንግስት ማስጠንቀቂያ ተግባራዊነቱ እስከምን ድረስ ነው ? ::
በመንግስት የተፈራው እና ማስጠንቀቂያ የተሰጠበት አንደኛው ነገር ሕዝባዊ አብዮት ነው፡፡ ሕዝባዊ አብዮት በየትኛውም የዓለማችን ክፍል በህግ ተፈቅዶ ወይም ቅድመ እውቅና ተሰጥቶት የሚከናወን ተግባር አይደለም፡፡ ዜጎች በመንግስታቸው የሚታየው የአስተዳደር ብልሹነት መሸከም ሲከብዳቸው እና ሸክማቸውን ያበዛባቸውን ደካማ መንግስት ለመለወጥ ወይም ለማውረድ ሲፈለጉ ምርጫና መሰል ነገሮችን ሣይጠብቁ በአደባባይ በመውጣታ ስልጣን የህዝብ መሆኑን በማሳየት ብልሹ የመንግስት ባለስልጣናትን እና ስልጣንን አሽቀንጥሮ የሚጣልበት አይነተኛ መንገድ ነው፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያን ጨምሮ እንደዚህ አይነቱ አብዮት በተለያዩ አገራት ተግባራዊ ተደርጓል ፤ይሁን እንጂ እስከዛሬ ድረስ የተደረጉ አብዮቶች ሙሉ በሙል ውጤታማ ናቸው ብሎ መደምደም ባይቻልም አብዛኞቹ አብዮቶች ስኬታማ ነበሩ፡፡ስኬታማ ያልሆኑ አብዮቶች ደግሞ ውጤታቸው የተበላሸ ያደረገው ዜጎች ያነሷቸው መሠረታዊ ጥያቄዎች ሣይሆን አብዮቱን ከፊት ሆኖው ሲመሩት የነበሩ መሪዎች አብዮቱን የመምራት እና የማስተባበር እንዲሁም የተገኘውን ውጤት የማስጠበቅ ድከመት ነው፡፡
በመሆኑም በጨቋኝ ሥርዓት መንግስት አስተዳደር ውስጥ ስለአብዮት ተግባራዊነት ይቅርና ስለ አብዮት ማሰብ እዳው ብዙ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ እነኚ አምባገነን መሪዎች ስልጣናቸው ሕዝብን ለማገልገል ሣይሆን እራሳቸው የሚገለገሉበት ዓይነተኛ መንግድ ነው፤ በመሆኑም ይህን ስልጣናቸው ማጣት ለእነሱ ከባድ ኪሳራ ነው፡፡ ስለዚህ የፈጀውን ይፍጅ በማለት ለተነሱ እና ለሚነሱ አብዮቶች ለማኮላሸት ዘብ ነው የሚቆሙት፡፡ ይሁን እንጂ ህዝባዊ አብዮት በይትኛውም መለኪያ ስዕተትም አጥያትም አይደለም ይህዝብ ጥያቄ እንዴት ስዕተት ሊሆን ይችላል ? በመሆኑም ሕዝባዊ አብዮት በአገራችን ላለመከሰቱ ኳሱ በማን እጅ ነው ? ፡፡ እንዲሁም መንግስት እየታየበት ያለው የአስተዳደር ብሉሽነት ለማረም እና ህዝብን ለማገልገል ካልተቻለው አለመቻሉንም ተገንዝቦ ለሚችሉት እድሉን ካልሰጠ እና ይባስ ብሎ ወደለየለት የአምባገነን ስርአት የሚያመራ ከሆነ ሕዝባዊ አብዮት ምን ይጠብቃል !፡፡
ሌላው እና ዋንኛው ጉዳይ በአገራችን ኢትዮጵያ እታየ ያለው የመንግስት የአስተዳደር ብሉሽነት ለማጋለጥ እና አማራጭ መፍትሔ ለመስጠትና ለማስተዳደር በሰላማዊ መንገድ በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች መኖራቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እነኚኽ ፓርቲዎች በተለይ ሰማያዊና አንድነት የሚያደርጓቸው ማናቸውም ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በመንግስት በኩል የሚሰጠው ምላሽ ድብደባና እስራት ነው፡፡
እርግጥ ነው በሠላማዊ ትግል ሂደት ውስጥ ውጣ ውረዶ የበዛ ነው፡፡ በዓለማችን ላይ የተካሄዱት ሠላማዊ ትግሎች ውጤት ያስመዘገብት መተኪያ የሌለውን የሰው ልጅ ሕይወትን እስከመንጠቅ በመድረሰ ነው፡፡ሠላማዊ ትግል ማለት ታጋዩ የሚታገልለትን ውጤት ሳይመለከት በትግሉ ሂደት የሚሰዋበት ፅኑ እምነት ነው እስከመባል ይደርሳል፡፡
ይህን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመረዳት ሰማያዊ እና አንድነት ፓርቲ የሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች በህዝቡ ውስጥ ጥሩ መነቃቃትን የፈጠረ ነው፡፡በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ በወጣት አመራሮቹ እና አባላቶቹ በመታገዝ የሚያደርጋቸው ሰላማዊ ተቃውሞ ድርጊቶች እጅግ በጣም የሚበረታታ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች ባለተከበረበት፣መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ እየገባ አንድን ሃይማኖት ከሌላው ሃይማኖት እያጋጨ፣ዜጎች የሚናገሩትን ቋንቋ መሠረት በማድረግ ብቻ ከመሬታቸው የሚፈናቀሉበት፣የኑሩ ውድነት እና እጅግ በጣም ቅጥ ያጣው ሙሰኝነት በተስፋፋበት፣የአገር ሀብት ፍታሃዊ ክፍፍል ባልታየበት እነዚህ እና መሰል ችግሮች ሙሉ በሙሉ ባይሆን እንኳን በከፊል መፍትሔ ባልተገኘባቸው ጉዳዮች ተከታታይ እና ጠንካራ የተቃውሞ እንቅስቃሴ አለመደረጉ የፓርቲዎቹ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጥያቄን የሚያጭር ነው፡፡
እርግጥ ነው ተቃዋሚ ፓርቲዎች በመንግስት እየደረሰባቸው ያለው ተፅኑ ቀላል የሚባል አይደለም በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ እየደረሰበት ያለው ጫና ስራዎችን የሚሰራበት ቢሮ እስከማስከልከል የደረሰ ነው፡፡ ነገር ግን ከላይ የተገለፁት እና መስል የመንግስት አስተዳደር ችግሮች እልባት እንዲያገኙ ይህ ባይቻል እንኳን መጠነኛ ማሻሻያ እንዲታይ ምርጫን 2007 እየተጠበቀ ከሆነ ሠላማዊ ወይም አመፅ አልባ ትግል ህዝብን ከምን ሊታደግ ነው ? :: በመሆኑም የመንግስት የአስተዳደር ሃላፊነት ለማግኘት ምርጫን መጠበቅ ግድ ቢልም በመንግስት ላይ እየታየ ያለው የአስተዳደር ችግሮች እንዲታረም እና ማሻሻይ እንዲደረግባቸው ምርጫን መጠበቅ ተገቢ ሆኖ አይታይም፡፡ ስለዚህም በሠላማዊ መንግድ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የተለያዩ አመፅ አልባ ትግሎችን በመንደፍ እና በማስተባበር ውጤት ሊያመጣ የሚያስችል እንቅስቃሴዎቻቸውን በይበልጥ አጠናክረው መቀጠል አለባቸው፡፡ እንዲህ አይነቱ እንቅስቃሴ ለገዢው ስርዓት የአስተዳደር ብሉሹነት ዕድል እና ትምህርት ካልሰጠው አሁንስ ኳሱ በማን እጅ ነው ? ::
http://ecadforum.com/Amharic/archives/10849/

Tuesday, January 28, 2014

ህወሓቶች አደብ ግዙ! (አብርሃ ደስታ)

በሌሎች ላይ የምትፈፅሙት ተግባር ሁሉ በራሳቹ ላይ እንደምትፈፅሙ (እንደሚፈፀም) አስቡ። በስልጣን ላይ ያለ ሁሉ በስልጣን አይኖርም። የስልጣን ዕድምያቹ በጣም አጪር መሆኑ እናንተም ታውቁታላቹ። በሰዎች ላይ ግፍ ስትፈፅሙ ሰዎች ይጠሏችኋል። በሰዎች ስትጠሉ የስልጣን ዕድምያቹ ያጥራል። እናንተ ያላቹ የህዝብ ድጋፍ ሳይሆን ጠመንጃ ነው። ጠመንጃ ስልጣን ለመያዝ ይረዳ እንደሆነ እንጂ በስልጣን ለመቆየት አያስችልም። ስለዚህ በጠመንጃ አፈሙዝ የስልጣን ዕድምያቹ ለማራዘም የምታደርጉት ጥረት ከንቱ ልፋት ነው።

Abraha Desta the facebook
አብረሃ ደስታ
እናንተ ከስልጣን ወርዳቹ ስልጣን የህዝብ ሲሆን፣ ፍትሕ ሲነግስ፣ እኩልነት ሲሰፍን ለፈፀማችሁት ወንጀልና ላደረሳችሁት በደል በሕግ እንደምትጠየቁ አያጠራጥርም። በስልጣን የኖረ የለም። እንኳን አምባገነኖች ዴሞክራሲያዊ ስርዓቶችም በስልጣን ኮረቻ ተቀምጠው ለዘላለም አይኖሩም።
ምናልባት እናንተ ምግባራችሁ አውቃቹ በህዝብ ስትተፉ ሀገር ለቃችሁ በመውጣት ለማምለጥ ትሞክሩ ይሆናል። ገንዘቡም አላቹ። ሁሉም ካድሬዎች (በሰዎች ላይ ግፍ እንዲፈፅሙ እየታዘዙ ያሉ የህወሓት አባላት) ግን እንደናንተ (እንደ ህወሓት መሪዎች) ከሀገር ወጥተው ለማምለጥ ዓቅሙ የላቸውም። ደግሞ ዓቅሙ ቢኖራቸውስ ለምን በሰሩት ጥፋት ከሀገራቸው ለመሰደድ ይወሰንባቸባል? የህወሓት ባለስልጣንናት ከስልጣን ወርደው በሀገራቸው በሰላም የሚኖሩበት ሁኔታ ለምን አያመቻቹም? ለምን መርሃቸውን ከ “ስልጣን ወይ ሞት” ወደ “ስልጣን ለህዝብ አስረክቦ በሀገር በሰላም መኖር” አይቀይሩም? ለካድሬዎቹስ አያስቡም እንዴ? የህወሓት ዕድሜኮ ትንሽ ነው። ህወሓት ሲሞት የህወሓት አባላትም ከህወሓት ድርጅት ጋር አብረው መሞት የለባቸውም። ህወሓትም ስልጣን ለህዝብ አስረክቦ ተቃዋሚ ፓርቲ ሁኖ መቀጠል ይችል የለ?! ዕድምያችሁ ከህወሓት ድርጅት ዕድሜ በላይ እንዲሆን አድርጉ።
እኛ ሰለማዊ ታጋዮች ነን። ያላቹ ሃብትና ጠመንጃ በመጠቀም እኛን መደብደብ፣ ማሳሰር፣ ማሰቃየት፣ መግደል ትችላላቹ። አምባገነን ስርዓት የሚችለው ነገር ቢኖር ሰው ማሳሰርና መግደል ነው። የዓላም አምባገነን መሪዎች በማሳሰርና በመግደል የስልጣን ዕድምያቸው ዘለአለማዊ ማድረግ ከቶ አይቻላቸውም። ዛሬ እኛን ብትደበድቡና ብትገድሉ ዕድምያቹ እያሳጠራቹ እንጂ እያሸነፋቹ አይደላችሁም። እኛ ብንገደል ሌላ ሰው አለ። ሁሉም ሰው መግደል አይቻልም። ምክንያቱም ሁሉም ሰው ከተገደለ ማንን ትጨቁናላቹ? የሚጨቆን ሰው ያስፈልጋችኋል። ሰው ጭቆና ሲበዛት በመሪዎቹ ላይ ያምፃል። እናም ትሸነፋላቹ። አምባገነን ተሸናፊ ነው። የማይሸነፍ ህዝብ ብቻ ነው። ምክንያቱም ህዝብ ለጭቆና አይነሳም።
እኛን በማሰቃየት ሰለማዊ ትግሉ መግደል አይቻልም። ሰለማዊ ትግሉ በመግደል የሰዎች የነፃነት ጥያቄ መግደል አይቻልም። የሰዎች የነፃነት ጥያቄ በመግደል ሰዎችን ለዘላለም መጨቆን አይቻልም። ስለዚህ መሸነፋቹ አይቀርም።
የሰለማዊ ትግል በር ባትዘግቡን መልካም ነው። ምክንያቱም ደም መፋሰሱ፣ ጦርነቱ፣ መጠፋፋቱ አንፈልገውም። እኛ የምንፈልገው ሰላም ነው። መንገዳችንም ሰለማዊ ነው። የሰላም በር ሲዘጋብን እጆቻችንና እግሮቻችን አጣጥፈን እንቀመጣለን ማለት ግን አይደለም። አንድ በር ሲዘጋ ሌላ በር ማንኳኳታችን ግድ ነው። ነፃነት እንፈልጋለንና። “መታፈን ይብቃን!” ብለን ተነስተናል። ስለዚህ ትግላችን በምንም ዓይነት ስትራተጂ ማስቆም አይቻልም። የሚቻለው ስልጣን ለህዝብ ማስረከብ ነው። ዴሞክራሲ ማስፈን ነው።
ገዢዎች በሐሳብ መከራከር ሳይችሉ ሲቀሩ ወደ ሀይል እርምጃ እንደሚወርዱ እናውቃለን። ሐይል መጠቀም የሽንፈት ምልክት ነው። ህወሓት የፈሪዎችና የጨካኞች ስብሰብ መሆኑ አውቅ ነበረ፤ ወደ ድንጋይ ውርወራ ፖለቲካ ይወርዳል የሚል ግምት ግን ፈፅሞ አልነበረኝም። መንግስት ወንጀልን መከላከል ሲገባው ወንጀል ፈፃሚ ሆነ።
ህወሓት ዉስጧ መበስበሱ እየሸተተን ነው። ምናለ ድንጋይ ባለመወርወር ገመናችሁ ባታጋልጡ? ለማንኛውም አደብ ግዙ የምትሰሩትን እወቁ። በሃይል የሚሆን ነገር እንደሌለ ተረዱ። ካለፉ ስርዓታት ታሪክ ተማሩ። ህዝብ እያያቹ ነው።
It is so!!!
http://ecadforum.com/Amharic/archives/10835/

በልቡ የሸፈተ ህዝብ የካድሬዎች ጋጋታና ሽብር አይገታውም

በዲያስፖራ የአረና ትግራይ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

ሰሞኑን በትግራይ የህወሓት መሪዎችና ካድሬዎቻቸው ከየመንደሩ የተውጣጡ ነብሰ ገዳይ፣ ስብሰባ በታኝና አፋኝ የዱሪየ ቡድኖችን በተለያየ መልኩ በማደራጀት በአረና ትግራይ አባላትና አመራር ላይ የከፈቱትን አዲስ የመንጥርና የድብደባ ዘመቻን አስመልክቶ

ህወሓት/ኢሕአዴግ በትረ ስልጣኑን ከተጎናፀፈና ካደላደለ ወዲህ ከሱ የተለየ አመለካከትና ሃሳብ ያላቸው ወገኖች ሁሉ የተለያዩ ቀለማ ቀለሞችን በመቅባት፣ የፈጠራ ስም በመለጠፍና ሰበብ አስባብ በመፈለግ በቀጥታም ሆነ በረቀቀ መንገድ የመመንጠር፣ የማፅዳት፣ የመሰወር፣ የማሰር፣ የመግደልና እርስ በርስ የማናቆር ስራ ዋነኛ የስርዓቱን ባህርይ መገለጫ ሆኖ መቆየቱ እሙን ነው። የእርምጃው ዋናው ምክንያትም እውነት ተቃዋሚዎቹ የሀገርና የህዝብ ጠላቶች ስለሆኑ አይደለም። ነገር ግን ጥያቄያቸው “ስለ ሀገራችንና ህዝባችን ጉዳይ እኛም ያገባናል!! አባቶቻችን ደም ከፍለው ያቆዩልንን ሀገር የመጠበቅ የኛም ግዴታ ነው!! ዘላቂ ልማትና ዕድገት የሚመጣው እውነተኛ ዲሞክራሲ፣ የሕግ ልዕልና፣ ፍትሕ፣ ነፃነት፣ ሰላምና አንድነት ሲረጋገጥ እንጂ በጡንቻ አይደለም!! ሕገ መንግስቱ የሰጠንን የመናገር፣ የመፃፍ፣ የመደራጀት፣ የመንቀሳቀስ፣ የእምነት፣ የመምረጥና የመመረጥ ነፃነታችንን ይከበር!!” ብለው ሰላማዊና ሕጋዊ መንገድን ተከትለው በቆራጥነት ስለተንቀሳቀሱና ስለጠየቁ ብቻ መሆኑን ማንም ቅን ህሊና ያለው ኢትዮጵያዊ ሊገነዘበው የሚችል ጉዳይ ነው።
ሰሞኑን የመድረክ አባል ከሆኑት የፓለቲካ ድርጅቶች አንዱ “በአረና ትግራይ ለሉዓላዊነትና ለዲሞክራሲ” አባላትና ከፍተኛ አመራር ላይ እየደረሰ ያለው ግፍና አፈና ማየቱ በቂ ይመስለናል። የአረና ትግራይ ፈጣን ዕድገትና በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መሄድ ያስደነጋጣቸው የህወሓት ካድሬዎችና መሪዎቻቸው እንቅስቃሴውን ለመግታት የማይፈንቅሉት ድንጋይና የማይሸርቡት ተንኰል እንደሌለ በተደጋጋሚ አይተናል። ዛሬም እንደለመዱት አዲስ የማጥቃት ስልት በመቀየስ ነብሰ ገዳይ፣ በታኝና አፋኝ የዱሩየዎች ቡድን በተለያየ መልኩ በሕቡእና በግልፅ በማደረጃት በአረና አባላትና መሪዎች ላይ አዲስ የመንጥር ዘመቻና ጥቃት ጀምሯል።
የማጥቃት ዘመቻው ቀደም ብሎ በሽሬ እንዳስላሴ የተጀመረ ሲሆን ሰሞኑን ደግሞ በባሰ መልኩ በአዲ ግራት ከተማና በሌሎች አካባቢዎችም በስፋት ቀጥሏል። በዚሁ ተከታታይ ዘመቻቸው ያነጣጠሩት አረና ትግራይ የጠራውን ስብሰባ እየተከታተሉ መበተን፣ ህዝቡን ወደ ስብሰባው እንዳይሄድ በተለያዩ ዘዴዎች ማስፈራራትና ማሰናከል፣ በታኝ የዱሩየዎች በዱን በማደራጀት ለመበጥበጥና ለማወክ ያለ የሌለ ሀይላቸውን በማንቀሳቀስ ስብሰባዎችን እንዲቋረጡ አድርጓል።
ጉዳዩን በቅርብ ተከታትለን እንዳረጋገጥነው የሚያሳዝነውና የሚያስገርመው ስብሰባውን መበተኑና መቋረጡ ብቻ ሳይሆን ህዝቡን ለመቀስቀስ በአካባቢው የተሰማሩ በሶስት ከፍተኛ የአረና ትግራይ መሪዎች በአፋኝና በታኝ ቡድን እንዲደበደቡ ማደረጋቸውና ማሰራቸው ነው። የዚሁ ጥቃት ሰለባ ከሆኑት ሰዎች ውስጥ አቶ አስገደ ገብረስላሴ የቀድሞ የህወሓት መስራችና አስልጣኝ የነበሩ፣ አቶ አብርሃ ደስታ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ፣ አቶ ዓንዶም ገብረስላሴ የዓረና ማእከላይ ኮሚቴ አባልና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ይገኙባቸዋል።
በአንጋፋ ወንድሞቻችን ላይ የደረሰባቸው ኢ ሰብኣዊ ጥቃት እጅጉን ያስቆጣንና ያስገረመን ቢሆንም በኛ እምነት ይህ ሁሉ ግፍና መሰሪ ተግባር በድምር ሲታይ የሚከተሉትን ሓቆችንና ክስቶችን የሚያመላክቱ የስርዓቱን ባህርይ ገላጭ ናቸው ብለን እናምናለን።
1. ህወሓት ታሪክ፣ ባህልና ሕግ የማይገዛው፣ መሰረታዊ እውነታዎችንና ዲሞክራሲያዊ መርሆዎችን የሚፃረርና የህዝቡን ሉዓላዊ ህልውና የሚያፈርስ የጥፋት መንገድ እየተከተለ በመሄድ ላይ እንደሆነ የሚያሳይ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃ መሆኑን ራሱ በራሱ ጋሃድ እየሆነ መምጣቱ የሚያመላክት ነው።
2. ይህ ዓይነቱ ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት የሚያሳየን ህወሓት ራሱን ከመንግስትነት ወደ ተራ ዘራፊነትና ማፊያነት በመቀየር የዜጎችን ድህንነት ለመጠበቅ የማይችል ሕገ አልባና የሻገተ ስርዓት መሆኑን ራሱን በራሱ እያስመሰከረ ያለ ድርጅት መሆኑን እንገነዘባለን። አንድ መንግስት በራሱ ህዝብና በገዛ ወገኑ ላይ ነብሰ ገዳይና አፋኝ ቡድንን በማደራጀት ዜጎቹን በአደባባይ ማስደብደብ ማለት የባዕድ ወራሪ እንኳን ያላደረገው ከዚህ የባሰ ጭካኔ፣ ውድቀትና ዝቅጠት አለ ብለን አናምንም።
3. የህወሓት ፀረ ህዝብ ተግባር ለይስሙላ ስለዲሞክራሲና ስለየብዙሃን ፓርቲ ስርዓት ይናገር እንጂ በተግባር በህዝብ ፊት ቀርቦ ለመከራከርና ለመዳኘት አቅምና ሞራል የሌለው፣ በህዝቡ ዘንድ ምን ያህል የተተፋና ጊዜ የጣለው ድርጅት መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ህወሓት የትግራይ ህዝብን ነፃነትና ደህንነት ጠባቂ ለመሆን ቀርቶ የነገ የሀገር ተረካቢና ተስፋ የሆነውን ወጣት በነፃነት አየር ተኰትኵቶና የወገንና የሀገሩን ፍቅር ተላብሶ እንዳያድግ ወኔን የሚያኰላሽ ትውልድ ገዳይ ድርጅት መሆኑን ከተግባሩ በላይ ሌላ ምስክር የሚያሻ አይደለም።
4. ህወሓት የትግራይ መንግስት ነኝ ይበል እንጂ ራሱ የፃፈውን ሕገ መንግስት እንኳ ጠንቅቆ የማያውቅ፣ በተግባር የሕገ መንግስቱን መሰረታዊ መርሆዎችን የሚፃረር ስራ የሚሰራ አፍራሽ ድርጅት መሆኑን ራሱን በራሱ እያስመሰከረ ይገኛል። የትግራይ ህዝብ እየተዳደረ ያለው ራሱ ባፀደቀው ሕገ መንግስት መሰረት ሳይሆን ገና በበረሃ የነበረው የደደቢት የካድሬ ሕግ መሆኑን ካለው ተጨባጭ ሁኔታና ከተግባራቸው መረዳት ይቻላል።
5. ህወሓት የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ነኝ በማለት የትግራይ ህዝብ ነብዪ መስሎ ለመቅረብ ይሞክር እንጂ በተግባር ግን የታገለለትን አላማ የሚፃረር ስራ የሚሰራና የህዝቡን ተስፋ እያጨለመ የሚገኝ ድርጅት መሆኑን ራሱ በራሱ እያስመሰከረ ይገኛል።
6. የጥቃቱ መንሲኤ ካድሬዎቹ እንደሚሉት የአረና ትግራይ አባላትና ደጋፊዎቻቸው የህዝብ ጠላት ስለሆኑ፣ ሕግ ስለጣሱ፣ የትምክሕተኞች አመለካከት ስለሚያራምዱ ወይም የደርግ ስርዓትን ዳግም ለመመለስ የሚታገሉ ስለሆኑ አይደለም። አረና ትግራይ ሕገ መንግስቱ የሚጠይቃቸው መመዘኛዎችን አሟልቶ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ በሰላማዊ መንገድ የሚታገል ድርጅት መሆኑን ይታወቃል። ይሁን እንጂ “አያ ጅቦ ሳታማኸኝ ብላኝ” እንደሚባለው ሁሉ ከጥቃቱ በስተጀርባ ያለው ሚስጢር ግን ባንድ በኩል ገዢው ፓርቲ በሀገር ደረጃ በተለይም በትግራይ ምድር እነሱ የማይቆጣጠሩት ትርጉም ያለው ነፃ የፓለቲካ ድርጅት እንዲፈጠር ፍፁም አይፈልጉም። በሌላ በኩል ደግሞ በትግራይ ህዝብ ላይ ያላቸው ንቀትና ዝቅተኛ ግምት የሚያሳይ ነው። ሕብረተሰቡ በፓለቲካ ድርጅትና በህዝብ መካከል ያለው ግንኙነትና ነፃነት፣ የዲሞክረሲ “ሀ ሁ”፣ ሕገ መንግስታዊ መብቱንና ታሪኩን በትንሹ ያውቃል ብለው ቢገምቱት ኖሮ እንዲህ ዓይነቱ ዓይን
ያወጣ አረሜናዊ ተግባር አይፈፁምም ነበር።
የተከበራችሁ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያውያን!!
እኛ በዲያስፓራ የምንኖረው የአረና ትግራይ የድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴና መላ የትግራይ ተወላጆች በሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ በየማዕዝናቱ በተለይም በበንሻንጉል፣ በጋምቤላ፣ በደቡብና በሌሎች ቦታዎች በወገኖቻችን ላይ የሚፈፀሙ አፈናዎችና እንግልት በቅርብ ስንከታተልና በተለያየ መልኩ ድምፃችንን ስናሰማ ቆይተናል። በቅርቡ በሳውዲ ዓረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ የደረሰው ልብ ሰባሪ የሆነ አሳዛኝና አሳፋሪ ዜና ስንሰማም በቁጣ ስሜት በመነሳሳት በያለንበት ከሌሎች ወገኖቻችን ጎን በአደባባይ ቆመን ጭኾናል። አውግዘናልም። ዛሬም በተመሳሳይ መልኩ እንደተለመደው በትግራይ በወገኖቻችን ላይ እየተካሄደ ያለው ጥቃትም ከዚሁ ተለይቶ የማይታይ ስለሆነ አሁንም የተሰማንን ቁጣና ብሶት ይህንን የጋራ መግለጫ በይፋ እንድናወጣ ተገደናል። ያልታደለች ሀገር ሁሉጊዜ መርዶ ነውና!!
ትግራይ እንደነ አሉላ አባ ነጋና ዮሐንስ የመሳሰሉ የብዙ ጀግኖች ዓፅም የተቀበረባትና አኩሪ ታሪክ ያላት ምድር ብትሆንም ዛሬ ህዝብዋ በአንድ ቤተሰባዊ ቡድን ለሚመራ ፓለቲካዊ ድርጅት በሞኖፓልና በንብረትነት ለማገልገል የተፈጠረ ህዝብ አድርገው በመቁጠር እንደ ህፃን ልጅ አፍህን ያዝ እየተባለ በካድሬ ዱላ እየተኰረኰመ ሲኖር ማየች እጅግ የሚያሳዝን የታሪክ ጠባሳ ነው። ስለሆነም ህወሓት በህዝቡም ሆነ የተለየ አመለካከት ይዘው በሚንቀሳቀሱ ወገኖቻችን ላይ የሚያካሂደው የስነ ልቦናና የአክል ጥቃት የዲሞክራሲ መርህ የሚፃረር ኢ ሰብኣዊ ተግባር ብቻ ሳይሆን የዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብት የሚጥስ ሕገ ወጥ ተግባር ስለሆነ ድርጊቱን እናወግዛን። እንዲሁም በግፍ የታሰሩ ወገኖቻችን ከእስር እንዲፈቱና በነሱ ላይ ድብደባ ያደረሱ የማፊያና የነብሰ ገዳይ ቡድን አባላትም በአስቸኳ ለፍርድ እንዲቀርቡ አበክረን እንጠይቃለን። በስልጣን ላይ ያለው ገዢው ፓርቲ ዜጎቻችንን ለያይተህ ግዛ በሚል ፈሊጥ በየተራ እንደ ፈለገ እያጠቃን እንዲኖር ምቹ ሁኔታ የፈጠርንለት እኛው ራሳችን በተለያየ ጎራ የየራሳችን ጎጆ አበጅተን በረባም ባልረባም በመነጣጠላችን መሆኑን እሙን ነው። ህዝብ ከተባበረ ምን ዓይነት ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል በሌሎች አጋጣሚዎች አይተናል። ስለዚህ በሀገር ቤትም በውጭም የምንኖር ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለሀገርና ለወገን ሲባል መለስተኛ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው አስነዋሪ ጥቃት በጋራ ልንቆምላቸው ይገባል። በመሆኑም ዛሬ በትግራይ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል ነገ በሌሎች ክልሎችም የሚደርስ ጉዳይ ስለሚሆን ድርጊቱን በጋራ እንድናወግዘው ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ጀግናው ኩሩና ታጋሽ የትግራይ ህዝብም በአካል ይቆጣጠሩት ይሆናል እንጂ የህወሓት ካድሬዎችና መሪዎቻቸው የሚሰሩትን አስቂኝና አሳዛኝ ድራማ ይስቷል ብለን አናምንም። ማን በሙሱና ተነክሮ ጨለማ ለብሶ የሀገርና የህዝብ ሀብት እየዘረፈና ወደ ዉጭ እያሸለከ እንዳለ ማን ደግሞ ለሀገሩና ለወገኑ በፅናት እየታገለ እንዳለ በውል ይገነዘባል። ትላንት ማን ከጎኑ እንደቆመ ማን ደግሞ ለሻዕቢያ ወረራ ለጅብ አሳልፎ እንደሰጠው ስለሚያስታውስ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ልቡ ከማን ጋር እንዳለ ጠንቅቀን እናውቃለን። በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ ክብሩንና ማንነቱን በሻዕቢያ በመደፈሩ፣ ለም መሬቱንና አንጡራ ሀብቱን ለባዕድ አሳልፎ በመሰጠቱ፣ ራሱ የሰራውን ቤት፣ በደሙና በአጥንቱ ራሱ የገነባትን ሀገር ፈርሶ የባሕር በር የሌላት ጎራዳና ሽባ ሀገር ይዞ በመቅረቱ ደስተኛ ነው ብለን በፍፁም አናምንም።
ስለሆነም ዛሬም ለገዢው ፓርቲ ህወሓት/ኢሕአዴግ መሪዎችና ካድሬዎቻቸው ደግመን ደጋግመን ልናስገነዝባቸው የምንፈልገው ጉዳይ አንድና አንድ ብቻ ነው። በሀገራችን ፍትሕ የጠማው፣ በረሃብ አለንጋ የሚገረፍና በልቡ የሸፈተ ህዝብ እስካለ ድረስ እናንተ የምትፈፅሙትን ጊዜው ያለፈበትና አረሜናዊ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃ ትግሉን የበለጠ እንዲግልና እንዲጎለብት ያደርገዋል እንጂ በፍፁም አይገታውም። እኛም የበለጠ እንድንጠነክርና ቀና ብለን በፅናት ከህዝባችን ጎን እንድንቆም ያደርገናል እንጂ አንገታችንን እንደማንደፋ ደግመን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
ኢትዮጵያ ሀገራችን ለዘላለም ትኑር
http://ecadforum.com/Amharic/archives/10833/

ከቀይ ወደ ሰማያዊ ጉዞ

ቹቸቤ

ከቀለማት ሁሉ ‘ቀይ’ አገራችንን አቅልሞ መዶሻው ቁልቁል ሲወቅረን ማጭዱ ከታች ሲያጭደን ኖረን ያለቀው አልቆ የተረፍነው ፈዘንና ደክመን ባለንበት ሰዐት ማጭዱንና መዶሻውን በብጫ ቀለም  ሸፍነው በትግራይ ስም አጨዳውን የቀጠሉበትና ቀን የሰጣቸው ጎጠኞች አገርም ሕዝብም ሊያጠፉ እንደገና በወገን ደም እያጨቀዩን ይገኛሉ። ቢሆንም ተስፋችን አላሟጠጠም። ብርቱዎች ቆርጠውና ቀልጥፈው ለነጻነት የሚደረገውን ትግል በሁሉም መስክ አፋፍመዋል። አዲስ የሆነው ነገር ከቀይና ነጭ ሽብር በሁዋላ ሰማያዊ ሰላማዊ ትግል የሚል መፈጠሩ ነው። ታሪክ ያልዘገባቸው ግን ከቀይ ሽብር ወደ ብጫ ስካር በሚል ጠጅ ቤት የቀሩ የአብዮት ትራፊ ወጣቶችን ህይወት ነው።Ethiopia’s Blue party (Semayawi party) leaders in police control
ርዕሱን በቀለም ጀምረነዋልና ሰማያዊ ፓርቲ በአውሮፓና በአሜሪካ ሃዋርያውን ልኮ ዓላማውን ሲያሳውቅ የሰነበተው በልደትና  በጥምቀት ሰሞን ነበርና ፓርቲው በመወለዱ ደስ ያላቸውና በመጠመቁና በማጥመቁም የጨፈሩ በርካቶች ናቸው። ወጣቱ ትውልድ ያገባኛል ይገባኛልም  ሲል ደስ ይላል። ደስታ ብቻም ሳይሆን ተስፋም ይሰጣል። ይልቃል ሰማያዊን ፓርቲዬ ብሎ ያላወቀውን ሲያሳውቅ ያወቀውንም  ሲያጠምቅ ሰንብቶ ወደ አገር ቤት የመልስ ጉዞ ከማድረጉ በፊት ለምታደርጉልን ድጋፍ አድናቆት አለኝ በማለት የኢትዮጵያ የወቅታዊ ጉዳዮች መወያያ መድረክን እድምተኞች አመስግኖ እንደጋገፍ እንበርታ በማለት ተሰናብቷል። ሌላኛው አጋሩ ብርሃኑም ደከመኝ ሳይል የተጠየቀውን ሁሉ ሲመልስ አርፍዷል። የልብ የልቡን ጥያቄ ያቀረበው እንደልቡም ጥሩ ውይይት መርቷል። ይቺን ማስታወሻ ስጽፍ ውይይቱ በሰፊው ቢሰራጭስ የሚል ማመልከቻ ላስገባ ነበር ግን የልቤን ልባሙ ሰው አውቆ ኖሮ ያሰብኩትን ሆኖ አገኘሁት።
ሰማያዊ ፓርቲ በወጣቶች የተገነባ ድርጅት ነው። እድሜ ጠገብ አዛውንቶችና እውቀት ጠገብ ምሁራኖችም ከጀርባው ይኖራሉ ብለን እናምናለን። እንዳለፈው ትውልድ የሀገር ፍቅር ስሜታቸውን ለሀገር ጥፋት የቆሙ መሰሪዎች እንዳይጫወቱበት ካለፈው በሚገባ ይማራሉ የሚል ተስፋም ይኖራል። ከምንም ነገር በላይ ግን አበቃለት የተባለው ወጣት የበቃለት ቁርጠኛ የነጻነት ታጋይ ሆኖ ሲነሳ ማየትን ያህል የሚያስደስት ነገር የለም። ወጣቱ ታሪክንና ትናንትን መማርያው አድርጎ እውቀትን ግን መመርያው ካደረገ ነገን ያሰበበት መድረሱ እርግጥ ነው። የዛሬዎች ጎልማሶች ትናንት በስሜትና በሀገር ፍቅር ተነስተው ዛሬ አገራቸውን ለሚያምሱ ጎጠኞች መሳርያ መሆናቸውን ሲያስቡ ልባቸው መድማቱ አይቀርም። የዚያኑ ያህል ዛሬን ድረስ የተሰራባቸውን ግፍ መለየት የማይቸሉ ወይም ያንን ቢለዩና ቢናገሩ ታሪካቸውና ህይወታቸው ወና ስለሚሆንባቸው በ’ተከድኖ ይብሰል’ የሚኖሩ ብዙ አሉ ይህንን ለቀጣዩ ትውልድ አልመኝም።
የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ካለፈው ሊማሩ የሚገባው ይህ ነው። ከምንም ነገር በላይ ዛሬ የማሰብና ያሰቡትን የመናገር መብት ያለበት ድርጅትን አጠናክሮ መንቀሳቅስና በተግባር ደግሞ መፈተንን ማስመስከር ይገባቸዋል። የስልጣንና የስራ ክፍፍልን ለሁሉም ማዳረስና ድርጅት አንጂ ግለሰብ ብቻ የሚገንበት እንዳይሆን ተግቶ መስራትም ይጠበቅባቸዋል። የዘመናችንን ጎጠኛና ሁዋላ ቀር ገዢ ማንነት በሚገባ እንዲታይ ዱላውንና ጥቃቱን ተቀብለው በቁርጠኛነት መነሳታቸው ደግሞ  ያኮራል። ከዘረኞቹ ገዢዎች ጋር ከሚደረገው ትግል ባሻገር ደግሞ የተኙትን የሚያነቃ የሰነፉትን የሚያበረታ ስራ መስራታቸውም ግሩም ነው። ተባብሮ ከመተኛት ከፊት ቀድሞ ሌሎቹንም ማነሳሳትም  ቸል የሚባል አይደለም። አንዳንዴ ከትብብርና ከውህደት በፊት መሆን ያለባቸው ነገሮችን በመዘንጋት የትብበር ጥሪ ማብዛቱም ደግ አይደለም። ስኳር ቡናው ውስጥ ስለገባ አያጣፍጠውም  ከስር ሄዶ ይተኛል እንጂ፣ እንዲጣፍጥ መማሰል አለበት። ቡናው እስኪፈላ መቆላት መፈጨት መንተክተክ አለበት ስኳሩም  እንዲሁ ብዙ ጉዞ አለው። እንዲያም ሆኖ መጥፎ ቡናን በስኳር ብዛት ማጣፈጥ አይቻልም። ድርጅቶችንም  ተባበሩ ስላልናቸው  ጠንካራ ና ውጤታማ ሊሆኑ አይችሉም።
በመጨረሻም ምሰጋናና ማበረታቻችን ሁሉ እያደረግን ከቀይ ወደ ሰማያዊ የምናደርገው ጉዞ የተሳካ እንዲሆን  ድጋፋችን አይለያቸው። “ግባችን እሩቅ መንገዱ ጠመዝማዛ ነው” ከሚለወ ተስፋ አስቆራጭ መፈክር “መንገዱ በስኬት የተሞላ ከግብ  መዳረሻችንም ቅርብ ነው” በሚል አዲሰ መፈክር  ልሰናበት።
http://ecadforum.com/Amharic/archives/10824/

Monday, January 27, 2014

በ‹‹ልማታዊ ጋዜጠኝነት›› እና በ“ኢትዮ ሱዳን ድንበር” ላይ ውይይቶች ተዘጋጁ

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ “በልማት ጋዜጠኝነት” ዙሪያ የፓርቲና የመንግስት ተወካዮች አቋማቸውን የሚገልፁበት ውይይት ለዛሬ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ሰማያዊ ፓርቲ የኢትዮ ሱዳን ድንበር በተመለከተ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ሃሳብ የሚያቀርቡበት ውይይት ያካሂዳል፡፡ 
‹‹ልማታዊ ጋዜጠኝነት›› በሚለው ርዕሰ ጉዳይ የተለያዩ ሃገሮችን ልምድ የሚያሳይና በኢትዮጵያ የሚኖረውን ቦታ የሚፈትሽ ውይይት በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል እንደሚካሄድ የገለፀው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒዩኬሽን ትምህርት ክፍል፤ የፓርቲ እና የመንግስት ተወካዮች አቋማቸውን እንደሚያቀርቡ ጠቁሟል፡፡ 
“ልማታዊ ጋዜጠኝነት” ለድሃ አገራት የሚጠቅምና የሚስማማ ነው በማለት የሚደግፉ እንዳሉ ሁሉ፤ በተቃራኒው ጋዜጠኝነት የመንግስት ጥገኛና አፈቀላጤ እንዲሆን ያደርጋል በማለት የሚተቹ መኖራቸው ይታወቃል፡፡ 
በሌላ በኩል የኢትዮ-ሱዳን ድንበርን በተመለከተ ዛሬ በዘጠኝ ሰዓት በጽ/ቤቱ ውይይት የሚያዘጋጀው ሰማያዊ ፓርቲ፤ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ልምድ እንዳላቸውና ሃሳባቸውን እንደሚያቀርቡ ገልጿል፡፡ መንግስት፣ ከሁመራ እስከ ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ድረስ ባለፉት ሁለት ወራት ድንበር እያካለለ መሆኑን በሱዳን የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች እንደተሰራጨ የገለፀው የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ ዮናታን ተስፋዬ፤ መንግስት ጉዳዩን ደብቆ ይዟል ብሏል፡፡ 
መንግስት በድንበር ጉዳይ የሚሰነዘሩ ትችቶች መሰረት የለሽ ናቸው ብሎ ማስተባበሉ ይታወሳል። 


http://addisadmassnews.com/

ደቡብ ሱዳን በጎሣ ፖለቲካ እሳት እየተበላች ነው!

የኃያላኑ የንዋይ ጥማትና የደቡብ ሱዳን የጎሣ ፍልሚያ

south sudan and the superpowers


ከተመሠረተች ምንም ያህል ያልሰነበተችው ደቡብ ሱዳን ሕዝቧ ሰላሙንና ነጻነቱን በደስታና በጸሎት አጣጥሞ ሳይጨርስ በእርስበርስ ጦርነት ውስጥ ከወደቀች አንድ ወር አልፏታል፡፡ ጎሣን መሠረት በማድረግ የተቀሰቀሰው ፍልሚያ ግን የተጀመረው ገና ደቡብ ሱዳን አገር ከመሆኗ በፊት እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡ በደቡብ ሱዳን ሣር ላይ የኃያላኑ ዝሆኖች የእጅ አዙር ጠብና ፍጥጫም አብሮ የሚጠቀስ ነው፡፡
አፍሪካ ከምዕራባውያን ቅኝ ግዛት ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ የመፈንቅለ መንግሥትና የእርስበርስ ጦርነት ትዕይንቶችን ስታስተናግድ ቆይታለች፡፡ ይህን “coup-civil war trap” አዙሪት በአብዛኛው የመከሰቱን ሁኔታ የፖለቲካ ተኝታኞች የሚስማሙበት ነው፤ ዋንኛውንም ምክንያት ጠንካራ ተቋማት ያለመመሥረታቸው ውጤት እንደሆነ ያሰምሩበታል፡፡
አዲስ አገርም ሆነ መንግሥት ምስረታ ወቅት የሚከሰቱ ሁለት አካሄዶች አሉ፡- በሕዝብ ይሁንታ ሳይሆን በጠብመንጃ ኃይል ወደ ሥልጣን የሚመጣው ቡድን በአንድ በኩል የፖለቲካ ተቋማት እንዲመሠረቱና ሥልጣንን ለተቀናቃኞቹ በማካፈል ተቀባይነት ያለው አመራር ለመመሥረት ይፈልጋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሥልጣን ማጋራቱ ተቀናቃኞቹን ኃይለኛ እንዲሆኑ ስለሚያደርግ ወደፊት እነዚሁ ተቀናቃኞች ኃይላቸውን አስተባብረው መፈንቅለ መንግሥት ያደርጉብኛል የሚል ሥጋት ውስጥ ይገባል፡፡ የመፈንቅለ መንግሥቱ ስጋት ሥልጣንን ከማጋራትም ሆነ ሕዝብን የሥልጣን ባለቤት ከማድረግ ስለሚበልጥበት አስቀድሞ ማካፈል የጀመረውን ሥልጣን በመፈንቅለ መንግሥት ፍራቻ መልሶ መሰብሰብ ይጀምራል፡፡
በቀጣዩም የራሱን ታማኞች በዙሪያው በማድረግ ራሱ ያጥራል፤ ሥልጣኑንም ያጠናክራል፡፡ የደኅንነቱንና የፖሊስ እንዲሁም የጦሩን ኃይላት በራሱ ጎሣ አባላት ወይም ቁልፍ ታማኞች ጠቅልሎ ይይዛል፡፡ ተቀናቃኞቹን በተወሰነ የሥልጣን ሣጥን ውስጥ በማስገባት በዓይነቁራኛ መከታተል ይጀምራል፡፡
የታማኝነት መለኪያው በጣም እየጨመረ ሲሄድ የሥልጣኑ አጥር ከጎሣ በማለፍ በቤተሰብ ደረጃ ይወርዳል፡፡ የፖለቲካ ተቋማትን በማጠናከር ሕዝብን ሙሉ የመብቱ ተጠቃሚ ከማድረግ ይልቅ መፈንቅለ መንግሥትን በመፍራትና በሥልጣን ወሰን ለሌለው ጊዜ ለመቆየት ሲባል በሚወሰደው እርምጃ የራስ ወገኖችን በግልጽ የመጥቀም አሠራር ይንሰራፋል፡፡ ሙስና፣ ንቅዘት፣ ወንጀል፣ “የመንግሥት ሌብነት”፣ ወዘተ ይጠናክራል፡፡ በአንጻሩ ቀድሞ የትግል ጓዶች የነበሩ የሥልጣን ክፍፍሉ እያነሳቸው ሲሄድ ቂም፣ ጥላቻ፣ “እንዴት ተቀደምኩ”፣ ወዘተ የሚል እልህ ውስጥ በመግባት በራሳቸው ጎሣና ቤተሰብ ዙሪያ ኃይል ማስተባበር ይጀምራሉ፡፡
SudaneseSoldierሁኔታው በዚህ መልኩ እየተፋጠጠ ገሃድ ከመውጣቱ በፊት አሰቀድሞ የመፈንቅለ መንግሥት ፍራቻ የነበረበት ኃይል ቀድሞ የመምታት እርምጃ በመውሰድ በታማኞቹ ድጋፍ ሥልጣኑን የማዳን ጊዜያዊ ዕድል ይገጥመዋል፡፡ የተገፉትና የተገለሉት ኃይሎች ወዲያው የመቋቋም ኃይል ካላቸው ፊትለፊት ይገጥሙታል፤ አስቀድመው ከተመቱ ግን ለጊዜው ተሸናፊ ቢሆኑም ቀኑን ጠብቆ ሊነሳ ወደሚችል የጎሣና የዘር እንዲያም ሲል የቤተሰብ ግጭት ውስጥ መግባታቸው የጊዜ ጉዳይ ይሆናል፡፡
መፈንቅለ መንግሥትን ለመከላከልና በሥልጣን አለገደብ ለመቆየት ሲባል የአፍሪካ መሪዎች ወደ እንደዚህ ዓይነት የማያባራ ሰቆቃ ሕዝብን እየመሩ “ሕዝባዊ ነን”፤ “በ99%” አብላጫ ምርጫ አሸንፈን ወንበር ይዘናል፤ “ልማታዊ መሪዎች ነን”፤ “ሁሉም ነገር ወደ ልማት”፤ “ጉዞ ሕዳሴ፣ ውዳሴ” በማለት ራሳቸው ሰክረው ሕዝብን አስክረው ለማደንዘዝ ይሞክራሉ፡፡ ለዓመታት ሲረጩት የቆዩትን የጎሰኝነት መርዝ በልማት ማር ለመቀባት ይሞክራሉ፡፡ ሥልጣኔን ከማጣ የእርስበርስ ዕልቂት ይከሰት፣ ደም ይፋሰስ፣ ህጻናት በማያባራ ሰቆቃ ውስጥ ይግቡ፣ እናቶች ዕድሜላካቸውን ያልቅሱ፣ ዜጎች መቅኖ ቢስ ይሁኑ፣ … በማለት የራስን ዘርና ጎሣ ብቻ ለዘላለም ሲጠቅሙ ይኖሩ ይመስል ራሳቸውን መልሶ በሚያወድም የማያባራ መከራ ይጥላሉ፡፡ በሥልጣን ለመቆየት የእርስበርስ ጦርነትን ይጋብዛሉ፤ ራሳቸው የቀበሩት ጊዜውን ጠብቆ የሚፈነዳው ቦምብ ግን ልማትን ከዘርና ጎሣ እንደማይለይ የዘነጉት ይመስላል፡፡
በደቡብ ሱዳን የኃያላኑ ፍጥጫ
21ኛው ክፍለ ዘመን በአውሮጳውያኑ አቆጣጠር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገች የመጣችውን ቻይና ልዕለ ኃያልነትን ለዓመታት በብቸኝነት የተቆጣጠረችውን አሜሪካ በሁሉም መስክ እየተገዳደረች ትገኛለች፡፡ ሁኔታው ያልጣማት አሜሪካ ይህንን የቻይና አካሄድ ለመገደብ ከተቻለም ለማስቆም ዕቅድ አውጥታ ስትንቀሳቀስ ቆይታለች፡፡ በተለይም ቻይና ከአፍሪካ አምባገነኖች ጋር በብድርም ሆነ በተዘዋዋሪ ስጦታ መልክ የምታከናውነው ስምምነት የምዕራባውያኑን በተለይም የአሜሪካንን ውቃቢ ያስቆጣ ተግባር ሆኖ ከርሟል፡፡
በዓለምአቀፍ ደረጃ ሸቀጧን እያራገፈች ያለችው ቻይና በፍጥነት እያደገ ያለውን ኢኮኖሚዋን ለማስቀጠል ከየትኛውም አገር ለምታገኘው ጥሬ ሃብት በተለይም ነዳጅ ከፍተኛ ዋጋ ትከፍላለች፡፡ ይህ የቻይና “ጭፍን” አካሄድ ደግሞ ምዕራባውያን ቻይናን ለማጥመድ የሚጠቀሙበት አይነተኛ መሣሪያ ሆኖላቸዋል፡፡
ከጅምሩ ከአልበሽር ሱዳን ጋር “በነዳጅ ፍቅር” የተለከፈችው ቻይና፤ ሱዳን ምዕራባውያን የሚያደርሱባትን ማዕቀብም ሆነ ማስፈራሪያ እንድትቋቋም በተለያዩ መንገዶች ረድታታለች፡፡ አልበሽር በዓለምአቀፉ ፍርድቤት ቢከሰሱም ሆነ ከምዕራብ መንግሥታት ውግዘት ቢደርስባቸውም ቻይና ከአፍሪካ አምባገነኖች ጋር በመሆን “አንለያይም” ስትቀኝባቸው ነበር፡፡ በመሆኑም ሱዳንን ለማንበርከክም ሆነ ለመቅጣት እንዲያም ሲል የቻይናን የኢኮኖሚ ጥቅም ለማጨናገፍና ኢንቨስትመንቷንም ለመከፋፈል ድርብ ተጽዕኖ የሚያመጣው ዕቅድ በምዕራባውያን ተነደፈ – ሱዳንን መከፋፈል፡፡
ለዓመታት ደቡብ ሱዳንን ነጻ ለማውጣት ሲታገል የነበረው ኤስ.ፒ.ኤል.ኤ. ይህንን አጀንዳ የሚያስፈጸም ሁነኛ መሣሪያ ሆነ፡፡ በጆን ጋራንግ ዘመን ወደ ስምምነት እየመጣ የነበረው የአማጺያኑና የሱዳን ውዝግብ ጋራንግ ከሞቱ በኋላ አቅጣጫውን በመቀየር ደቡብ ሱዳን በአገር ደረጃ እንድትመሠረት አሜሪካ ግልጽ አቋም በመያዝ ተጸዕኖ አደረገች፤ ከበቂ በላይ ፕሮፓጋንዳም ነፋች፡፡south sudan oil
በሌላ በኩል የአልበሽርን ሱዳን ይበልጥ መልከጥፉ ለማድረግና የነጻዪቱን ደቡብ ሱዳን መመሥረት ለማፋጠን የዳርፉር ቀውስ በአሜሪካና እስራኤል ምሥጢራዊ ድጋፍ ያገኝ ቀጠለ፡፡ በመጨረሻም ከ2 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ያለቀበት ጦርነት በደቡብ ሱዳን መገንጠል ተጠናቀቀ፡፡ የምዕራባውያን በተለይም የአሜሪካ ታላቅ ውለታ ያለባት ደቡብ ሱዳን ገና ነጻ አገር ሳትሆን የዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) አባል ለመሆን ማመልከቻ በማስገባት ለአሜሪካ ቀብድ መክፈል ጀመረች፡፡
ለደቡብ ሱዳን ነጻ መውጣት ቀጥተኛና ግልጽ ድጋፍ ትሰጥ የነበረችው አሜሪካ ደቡብ ሱዳን ነጻ አገር ከሆነች በኋላ እንደታሰበው በአገሪቷ ላይ ሙሉ ቁጥጥር ማድረግ አልቻለችም፡፡ እጅግ ኋላ ቀር የሆነው የደቡብ ሱዳን ኢኮኖሚ ከቻይና ቁጥጥር ሥር ሙሉ በሙሉ ሊወጣ አልቻለም፡፡ ሱዳን ከመከፋፈሏ በፊት የ20 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት የነበራት ቻይና ከክፍፍሉ በኋላ በደቡብ ሱዳን ብቻ የ8ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት አላት፡፡
ይህ ከፍተኛ የሆነ በነዳጅ ላይ ያተኮረ ኢንቨስትመንት የቻይናን የነዳጅ ጥማት የሚያረካ ባይሆንም የዛሬ ወር አካባቢ የእርስበርስ ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት በነበሩት 10ወራት ብቻ ቻይና ከደቡብ ሱዳን 1.9ሚሊዮን ቶን ነዳጅ ወይም 14ሚሊዮን በርሜል ቀድታለች፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው ከሆነ ይህ የነዳጅ መጠን ቻይና ከናይጄሪያ በዓመት ከምታስመጣው በእጥፍ የሚበልጥ ነው፡፡ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪርና የቀድሞ ምክትላቸው ሬክ ማቻር ዲንካ እና ኑዌር በማለት ዘር ለይተው ፍልሚያ ከጀመሩ ወዲህ ግን የነዳጅ ምርቱ 20በመቶ ወርዷል፡፡ ዋናው የእርስበርስ ጦርነት በነዳጅ በበለጸጉት የዩኒቲ እና ኧፐር ናይል ጠቅላይ ግዛቶች አካባቢ መሆኑ የጦርነቱ ዋንኛ አካሄድ ምን ላይ ያተኮረ እንደሆነ ገላጭ ነው፡፡
በትጥቅ ትግሉ ወቅት የአሜሪካንን እና የእስራኤልን ድጋፍ ሲያገኝ የነበረው የደቡብ ሱዳን ነጻ አውጪ ግምባር አሁንም በሳልቫ ኪር አገዛዝ ከሁለቱ አገራት የሚያገኘው ጥቅም አልቀረበትም፡፡ የቻይና ኢኮኖሚያዊ የበላይነትና በአፍሪካ መንሰራፋት የልዕለኃያልነት ጥያቄ ያስነሳባት አሜሪካና ተባባሪዎቿ ጉዳዩን ሲያጠኑና ተግባራዊ እርምጃ ሲወስዱ ቆይተዋል፡፡ በተለይ በአፍሪካ የአሜሪካ ወታደራዊ ዕዝ (አፍሪኮም – AFRICOM) መቋቋም አንዱና ዋንኛው የቻይናን የንግድ እንቅስቃሴ የመቆጣጠሪያ መንገድ መሆን እንዳለበት ወታደራዊ ጠበብቶች ስታቴጂካዊ ጥናቶች ያደረጉበት ነው፡፡
imiደቡብ ሱዳን ነጻ ከወጣች በኋላ አሜሪካና ደጋፊዎቿ ወዲያውኑ የኢኮኖሚ የበላይነት ለመቆጣጠር ባይችሉም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ግን ቆይተዋል፡፡ በተለይ ከነጻነት በኋላ እስራኤል ከደቡብ ሱዳን ጋር ውሃ ለማጣራት፣ የውሃ ጨውነትን ለማስወገድ፣ ውሃ ለማመላለስ፣ እንዲሁም ለመስኖ ስምምነት ፈርማ ነበር፡፡ በእርግጥ ስምምነቱ በዚህ መልኩ ቢፈረምም ሥራውን በዋንኛነት የሚያከናውነው በውሃ ቴክኖሎጂ ሳይሆን በመሣሪያ ማምረት የታወቀው የእስራኤል ወታደራዊ ኢንዱስትሪ (አይ.ኤም.አይ.) መሆኑ በደቡብ ሱዳን ውስጥ የአሜሪካ ወዳጆችን አቅጣጫ የሚያሳይ ነው፡፡ በእርግጥ አይኤምአይ ከውሃ ጋር በተያያዙ እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ላይ እንደ አማካይ ሆኖ የሚሠራ ቢሆንም ወታደራዊ ተቋም እንደመሆኑ ለግጭቶች፣ ለጦር መሣሪያዎች እና ገንዘብ ዝውውር እንደ አማካይ ሆኖ እንደሚሰራ ጉዳዩን የሚከታተሉ ይጠቁማሉ፡፡
የቻይናን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና የበላይነት ለመገደብ በተቀነባበረ ሁኔታ እየተካሄደ ያለው የደቡብ ሱዳን ግጭት ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ እንዳሄድ አሜሪካ ግጭቱ ከተነሳበት ጊዜ ጀምሮ “ዲፕሎማሲው” ላይ ተግታለች፡፡ የጋዳፊን አገዛዝ በመገርሰስ ቻይናን ከ20ቢሊዮን ዶላር በላይ ኪሣራ ላይ እንድወድቅ የተደረገበት የምዕራባውያን ዕቅድ፤ በደቡብ ሱዳን ላይ ተግባራዊ ሲሆን በአካባቢው ባሉ አገራት (በተለይ በኢትዮጵያ) ላይ የሚያደርሰው ተጽዕኖ ተሰግቷል፡፡ በመሆኑም “ሁኔታውን አስቀድሞ መቆጣጠር ኃላፊነቴ ነው” ያለች የምትመስለው አሜሪካ፤ የሳልቫ ኪር ወዳጅ የሆኑትን እና በአሜሪካ ጥቅም አስከባሪነታቸው የሚታወቁትን ዩዌሪ ሙሴቪኒን የመጀመሪያ ተሰላፊ አድርጋለች፡፡ ለአሜሪካ ሲሉ በጎረቤት አገር ጦርነት እስከመክፈት የሚታወቁት መለስ ሞት ቀደማቸው እንጂ ለዚህ ተላላኪነት ገጣሚ ሰው ነበሩ፡፡
ግጭቱ እንደጀመረ ሙሴቪኒ ጣልቃ ለመግባትና ሳልቫ ኪርን ለመደገፍ ጊዜም አልወሰደባቸውም፡፡ በቅልጥፍና የወሰዱት እርምጃም አስቀድሞ ትእዛዝ የተሰጣቸው ወይም ግጭቱን “በተስፋ” ሲጠብቁ የነበረ አስመስሎባቸዋል፡፡ 1,600 ወታደሮቻቸውን ወደዚያው በመላክ የተላላኪነት ሥራቸውን የጀመሩት የዑጋንዳው አምባገነን፤ ሬክ ማቻር በአዲስ አበባ ላይ በሚደረገው የሰላም ድርድር የማይስማሙ ከሆነ የምስራቅ አፍሪካ አገራትን አስተባብረው ወታደራዊ ክንዳቸውን በማሳረፍ እንደሚያንበረክኳቸው አስጠንቅቀው ነበር፡፡ የሙሴቪኒ ሁኔታ መለስ ባይኖሩም ለሁለት እንተካለን ብለው የገቡትን ቴድሮስ አድሃኖምና ስዩም መስፍንን እንዲሁም ሌሎች የህወሃት ኃላፊዎችን “ያስደነገጠ” መሆኑን መናገራቸውን በቀጣናው ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑ ጠቅሶ ፋይናንሺያል ታይምስ ዘግቧል፡፡
ዋንግ ዪ
ዋንግ ዪ
ቻይናም ግጭቱ እንደተጀመረ በደቡብ ሱዳን ካላት ጥቅም እና በምዕራባውያን ከተቀነባበረባት ጥቃት አኳያ ሁኔታውን ለመቆጣጠር ጥረት ስታደርግ ቆይታለች፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯን ወደ አዲስ አበባ በመላክ ሁለቱም ወገኖች በአስቸኳይ ወደ ስምምነት እንዲደርሱ ስትመክር ነበር፡፡ አንዳንድ የሚዲያ መረጃዎች እንዳመለከቱት ሚኒስትር ዋንግ ዪ በግላቸው ሁለቱን ወገኖች ለመሸምገል ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ጥረቱ ባይሳካላቸውም ሁኔታው ቻይና ምን ያህል እንዳሳሰባትና በጉዳዩ ላይ ትኩረት እንደሰጠች በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡
ሥልጣናቸውን ለማስጠበቅና ከምዕራባውያን ጋር “በፍቅር” ዓለም ውስጥ ያሉትን ሳልቫ ኪርን “ዲንኮክራሲ” (የዲንካ ጎሣ የበላይነት) የዘር ፖለቲካ የሚያራምዱ፣ አምባገነን፣ ወዘተ እያሉ ከኑዌር ጎሣ የሆኑት ሬክ ማቻር ቢከሷቸውም፤ እርሳቸውም ከዚሁ የዘርና ለሥልጣን የመስገብገብ ባህርይ ውጭ እንዳልሆኑ የቀድሞ ታሪካቸው ይመሰክራል፡፡ እንዲያውም በትጥቅ ትግሉ ወቅት “የቦር ዕልቂት” እየተባለ የሚጠቀሰውን በመምራት ኑዌሮች ከ2ሺህ በላይ ዲንካዎች ለጨፈጨፉበት ወንጀል ዶ/ር ሬክ ማቻርን የሚከሷቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ቀጥሎም ከአልበሽር ሱዳን ጋር በመስማማት የካርቱምን ስምምነት በመፈረማቸው “በከሃዲነት” የሚወነጅሏቸውም የዚያኑ ያህል በርካታ ናቸው፡፡ ሥልጣን አልያዙም እንጂ ከሚወቅሷቸው ሳልቫ ኪር ባልተናነሰ መልኩ ዘረኛና የሥልጣን ጥማተኛ በመሆናቸው መንበሩን ቢቆጣጠሩ “የተማረ አምባገነን” ከመሆን እንደማያልፉ የደቡብ ሱዳንን ጉዳይ የሚከታተሉ ተንታኞች ይናገራሉ፡፡ ሬክ ማቻር ትምህርታቸውን ስኮትላንድ የተከታተሉ ሲሆን በስትራቴጂክ ዕቅድና ኢንዱስትሪ የዶክትሬት ዲግሪ አላቸው፡፡
s sudan cease fireቀናትን ያስቆጠረውና “በርካታ ድርድር” ተካሄደበት የተባለው ስምምነት ባፈው አርብ እንደተፈረመ ህወሃቶቹ ስዩም መስፍንና ቴድሮስ አድሃኖም ትጉ ሠራተኞች መሆናቸውን በማስመስከር “መለስ ባይኖርም እኛ አለን” የሚያስብል ታዛዥነታቸውን ለምዕራብ አለቆቻቸው አብስረዋል፡፡ “የባድመ ድል አብሳሪ” አቶ ስዩም በዚህ ብቻ አላበቁም፤ “በመልካም እምነት የሚፈረሙ የሰላም ስምምነቶች በርካታዎች ናቸው፤ ተሳክቶላቸው ተግባራዊ የሚሆኑት ግን ጥቂት፣ በጣም ጥቂቶች ናቸው … በደቡብ ሱዳን ግን ይህ እንዲሆን አንሻም” አሉ፡፡ ምክርም አከሉበት፤ ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲሆን ነጥቦች ጠቀሱ “በግጭቱ ምክንያት የተፈናቀሉትን በሺዎች የሚቆጠሩትን መልሳችሁ አቋቁሙ፤ የፖለቲካ ውይይቱን በመቀጠል ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ ዕርቅ እንዲሆን እንሠራለን” አሉ፡፡ ከሳዑዲ አረቢያ ከተፈናቀሉት ኢትዮጵያውያን ጋር አብሮ ምሳ በመብላት መልሶ የማቋቋም ችሎታቸውን ያስመሰከሩት ቴድሮስ አድሃኖምም ከልምድ የምክሩ ተካፋይና አካፋይ ነበሩ፡፡
የፊርማ ቀለሙ ገና ሳይደርቅ ሁለቱም ወገኖች መካሰሳቸውን ቀጥለዋል፡፡ በተለይ የሳልቫ ኪር ወታደሮች ስምምነቱን እንደ ጊዜ መግዢያ በማድረግ ኃይላቸውን አጠናክረው መልሶ በማጥቃት በአብዛኛው የነዳጅ ቦታዎችን የተቆጣጠረውን የሬክ ማቻርን ኃይል እየደበደቡ መሆናቸው ተዘግቧል፡፡ የማቻር ኃይሎችም አጸፋ በመስጠት ጥቃቱ በጥቃት በመመለስ ጦርነቱን ቀጥለዋል፡፡ ከናይጄሪያና አንጎላ በመቀጠል ከሰሃራ በታች ካሉት አገራት በነዳጅ ክምችት ቀዳሚ የሆነችው ደቡብ ሱዳን በጎሣ ፖለቲካ እየነደደች ነው፤ ምድሪቱም ዳግም እያለቀሰች ነው፡፡Children displaced by the fighting in Bor county, who have just arrived, are standing on the side of a boat in the port in Minkaman
ቻይናን ለመምታት የተነደፈው የምዕራባውያን ዕቅድም እየሠራ ነው፡፡ በውጤቱም የሌሎች አገራት ነዳጅ ድርጅቶች መራራውን ጽዋ እየጠጡ ነው፡፡ የቻይናው ብሔራዊ የፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን ጨምሮ የሕንዱ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ኮርፖሬሽን በራቸውን ቆልፈው ሠራተኞቻቸውን ከደቡብ ሱዳን አስወጥተዋል፡፡
ከዲንካ፣ ኑዌር፣ ወዘተ ጎሣዎች አልፎ ለበርካታ አገራት የሚበቃ ነዳጅ ያላት ደቡብ ሱዳን በጭፍን ጎሠኝነት መርዝ ተነድፋ ለምዕራባውያን መጠቀሚያ ሆናለች፡፡ ነጻነት የናፈቀው ሕዝቧም ለማያቋርጥ ስደትና ሰቆቃ ተጋልጦዋል፡፡ ከጎሠኝነት ወደ ሰብዓዊነት ከማደግ ይልቅ ወደ ቤተሰብ ደረጃ መጥበብ፤ በነጻ አውጪነት ተነስቶ በሆደ ሰፊነት አገር ከመምራት ይልቅ የምዕራባውያን አሽከርና መጠቀሚያ መሆን ውጤቱ ምን እንደሚሆን ደቡብ ሱዳን ጥሩ ትምህርት ትሰጣለች፡፡
እንዲህ ያለውን ውጤት ለማየት እንደ ደቡብ ሱዳን ሁለት ዓመታት ብቻ ሊወስድ ይችላል፡፡ “ይህንን አልፈናል” በማለት ጭንቅላታቸው ላበጠባቸው ደግሞ ሁለት ዓስርተ ዓመታት ይወስድ ይሆናል፡፡ የቱንም ያህል ዘመን ይውሰድ ለአንድ ጎሣ ወይም ዘር የበላይነት መቆም በሌሎች ተበዳዮች ዘንድ ቂም ከማስቋጠር አልፎ የምዕራባውያን አሽከርና መጠቀሚያ የሚደርግ ሲሆን “መብቱ አስከብራለሁ” ያሉትን ዘር መልሶ ለሰቆቃ መዳረግም ነው፡፡
dinka nuerደቡብ ሱዳን ያላትን ሃብት በቅጡ ሳትጠቀም እዚህ ደርሳለች፡፡ ሳልቫ ኪርና ሬክ ማቻር በአምባገነኖችና በምዕራባውያን አስመሳይ ሸምጋዮች አደራዳሪነት ሳይሆን በማንዴላ ዓይነት ሆደሰፊነት የወደፊቱን ትውልድ በማሰብ በእውነተኛ ዕርቅ ላይ የተመሠረተ ሰላም ማምጣት ካልቻሉ የዘረኝነታቸውን ውጤት በገሃድ ያገኙታል፡፡ “መብቱን አስከብራለሁ” ብለው የተነሱለትን ጎሣ/ዘር የሚያዋረድና አንገት አስደፍቶ ለትውልድ የሚዘልቅ ታሪክ ይተዋሉ፡፡ አዲሷ አገር ደቡብ ሱዳንም ኅልውናዋ ከስሞ ዲንካ እና ኑዌር የተባሉ “አገራት” በመሆን የአፍሪካ “ኅብረትን” ይቀላቀላሉ፡፡ የጎሣ ፖለቲካው አዙሪትም ወደ አውራጃና ቤተሰብ ደረጃ እየጠበበ መድረሻ ወደሌለው አዘቅት ይወርዳል፡፡

http://www.goolgule.com/south-sudan-and-tribal-politics/