FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Saturday, March 29, 2014

ጎሠኛነትና ሽብርተኛነት (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

የጎሠኛነት አጭር ትርጉም ዓለምን በራሱ ጠባብ ኢምንትነት የሚለካ ሰው ነው፤ ለኪው መለኪያው ነው፤ መለኪያውም ለኪው ነው፤ ጎሠኛነት የዘረኛነት የባሕርይ ልጅ ነው፤ ዘረኛነትም ሆነ ጎሠኛነት መሠረታቸው ድንቁርና ነው፤ የድንቁርናው ዓይነተኛ መገለጫ ‹‹ንጹሕ›› የሚለው ቃል ነው፤ ለዚህ ዋና ምስክር አድርጌ የማቀርበው አዶልፍ ሂትለርን ነው፤ ስለ‹‹አርያን ዘር›› ማንነትና ‹‹ንጹሕነት›› የሂትለር Mien Kampf የሚለውን መጽሐፍ ነው፤

Prof. Mesfin Woldemariam
የሰው ልጆች ባህል የሚባለው ሁሉ፣ ዛሬ የምናየው የሥነ ጥበብ፣ የሳይንስና የሳይንስ ጥበብ (ቴክኖሎጂ) ውጤት ሁሉ የአርያን ዘር የፈጠራ ውጤቶች ናቸው፤ … ‹ሰው› የሚባለውም እሱ ብቻ ነው።
የሂትለር ዘረኛነት የሰውን ልጅ ሁሉ ጉድጓድ ውስጥ ከተተው፤ አርያኑን ከንጹሕ የሰው ዘርነት ወደብቸኛ የሰው ዘርነት አሸጋገረው፤ ይህ ንጹሕ ድንቁርና ነው፤ የጎሠኞችም መነሻና መድረሻ፣ መንገዱም ይኸው ነው፤ በቅርቡ በፌስቡክ ላይ የታየው የቋንቋ ንጽሕና ክርክር የዚሁ የዘረኛነትና የጎሠኛነት ድንቁርና ቅጥያ ነው፤ ስለቋንቋዎች ባሕርይ ምንም ዓይነት እውቀት ሳይኖረው ቋንቋውን በማንገሥ እሱ ራሱ የነገሠ እየመሰለው ይደሰታል፤ ዓባይን ያላየ ምንጭ ያመሰግናል እንደሚባለው፤ ሙት ቋንቋ ካልሆነ በቀር ቋንቋ እንደሰው ልጅ ይጋባል፤ ይዋለዳል፤ ይለወጣል፤ በ1944 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ አገር ለማየት ከአዲስ አበባ የወጣሁት በጣልያን ትሬንታ ኳትሮ (34) ከባድ የዕቃ መጫኛ መኪና ላይ ተጭኜ ነው፤ ደብረ ማርቆስ ስገባ የሚናገሩት አይገባኝም ነበር፤ እኔ ከለመድሁት የሸዋ አማርኛ ጋር በጣም የተራራቀ ነበር፤ ወሎም ሄጄ አንደዚያው ነበር፤ ዛሬ ከስድሳ ዓመታት በኋላ ሌላ ነው፤ ዘረኛነትም ሆነ ጎሠኛነት የእውቀት፣ የመሻሻልና የእድገት ጸር ነው፤ ቆሞ-ቀር ነው፤ የአእምሮው እይታ አጠገቡ ካለው ወንዝና ጉብታ አያልፍም፤ ራሱ በፈጠረው ግርዶሽ መተናፈሻውንና መንቀሳቀሻውን ያጠበበ ነው፤ ተንጋሎ የተፋ ለራሱ ከፋ!
ዘረኛነትና ጎሠኛነት ከስጋትና ከፍርሃት የመነጨ ነው፤ አልጋው ፍርሃት፣ ትራሱ ስጋት ስለሆነ ጭንቀቱ እያባነነው እንቅልፍ አይወስደውም፤ ሲያቃዠው ያድራል፤ ለየት ያለና ትንሽም ሻል ያለ ነገር ሲያይ ሆን ብሎ እሱን ለማኮሰስ ወይም ለማሳነስ የመጣበት እየመሰለው ይደነግጣል፤ ስለዚህም ከሱ የተሻለውን በማጥፋት እሱ ወደትልቅነት የሚሸጋገር ይመስለዋል፤ ስለዚህም ዘረኛነትና ጎሠኛነት የሽብርተኛነት ምንጭ አንዱና ዋናው ምክንያት ከሱ የተለየውን ለማጥፋት ያለው ዝንባሌ ነው፤ ዘረኛነትና ጎሠኛነት ልብን በጥላቻ ያቆሽሻል፤ አእምሮን በክፋት እየመረዘ ያደነዝዛል፤ ሰውነትን ወደርኩስ መንፈስነት ይለውጣል፤ በባነነና በቃዠ ቁጥር የሚታየው ማታለል፣ ማጥፋት፣ ማፍረስ፣ ማዋረድ፣ ማጎሳቆልና ማደህየት ብቻ ነው፤ ለዘረኛና ለጎሠኛ እድገት ማለት የሌሎች መቀጨጭና መሞት ነው፤ ማደህየት፣ ማሰቃየት፣ ማቀጨጭና መግደል፣ ንብረትንም ማውደም የሽብርተኛነት መገለጫው ነው፤ የሽብርተኛነት ማለትም የዘረኛና የጎሠኛ የደነዘዘ አንጎል ጥፋትን እንደልማት፣ መቀጨጭን እንደእድገት ይመለከታል።
የዘረኛና የጎሠኛ ሽብርተኛነት የሚፈጥረው የደነዘዘ አንጎል ራስንም አይምርም፤ ለራሱ ልጆችና ቤተ-ዘመዶች አያስብም፤ በዙሪያው ያለውን ከሱ የተለየ ዓለም በሙሉ ወደአንጠርጦስ ሲከታቸው የሱም ወገኖች አብረው አንጦርጦስ ቢወርዱ ግድ የለውም! አይጸጽተውም! የተረፉት በሙታኑ መቃብር ላይ አሸብርቀው ሕያዋን መስለው ይታያሉ፤ እነሱ ባያዩትም የቆሙበት መቃብር ጠርንፎ ይዟቸዋል፤ ሕያዋኑና ሙታኑ ተቆራኝተዋል፤ ሙታኑ በተፈጥሮ ሕግ ይበሰብሳሉ፤ ሕያዋን የሚመስሉት በገዛ ሥራቸው ይበሰብሳሉ።
ዘረኛም ሆነ ጎሠኛ ሂሳቡ ምንጊዜም ጅምላ ነው፤ የዘረኛነትም ሆነ የጎሠኛነት የደነዘዘ አንጎል የሚያየው ጅምላ ነው፤ የጥፋቱ ሁሉ መሠረት የሚሆነውም ጅምላውን ደፍጥጦ አንድ አድርጎ ማየቱ ነው፤ ስለዚህም ጥፋቱ ጅምላ ነው፤ የሽብርተኛነት ሂሳብም ጅምላ ነው፤ ዘረኛም ሆነ ጎሠኛ ወይም ሽብርተኛ ራሱንም የሚያየው የጅምላ አካል አድርጎ እንጂ ራሱን የቻለ ነጻ ሰው አድርጎ አይደለም፤ ብቻውን አይደለም፤ ራሱን የሚያየው በጅምላ ከሌሎች መሰሎቹ ከሚላቸው ጋር ነው፤ ከአሱና ከመሰሎቹ የተለዩ ግለሰቦችንም ሲያይ በነጠላ ሳይሆን በጅምላ ነው፤ ለዚህ ምክንያት አለው፤ ራሱን በጅምላ የሚያየው ምሽጉ ውስጥ ሆኖ ከፍርሃት ነጻ ለመሆን ነው፤ ከእሱ የተለዩትንም በጅምላ የሚያየው ሁሉም ኢላማ ስለሆኑ ነው፤ ይህንን ሁነት በትክክል ለመገንዘብ አንድ ሀ ና ለ የሚባሉ ጎሣዎች አሉ እንበል፤ እነዚህ ጎሣዎች ውስጥ ሁ፣ ሂ፣ ሃ፣ ሄ፣ ህ፣ ሆ የሚባሉ አባሎች አሉ፤ ደግሞም ሉ፣ ሊ፣ ላ፣ ሌ፣ ል፣ ሎ የሚባሉ አባሎች አሉ፤ በትክክል ማሰብ የሚችል ሰው ሁሉ በአንዴ እንደሚገነዘበው ሉ የአንዳቸውንም የሌሎቹን የለ ጎሣ አባሎች ተግባር ሊፈጽም አይችልም፤ ሌሎቹም ሉ ን ሊሆኑ አይችሉም፤ የዘረኛና የጎሠኛ መሠረታዊ ድንቁርና እነዚህን ልዩነቶች ማየት ሳይችል በ‹ሀ› በ‹ለ› መሀከል ያለው ልዩነት በጣም ጎልቶ ይታየዋል፤ የድንቁርናውም፣ የጥላቸው፣ የፍርሃቱም፣ የክፋቱም፣ የተንኮሉም፣ የሽብርተኛነቱም መነሻ ይኸው ራሱን ማሰብ እንደሚችል ሰው ያለዘር ወይም ያለጎሣ ምርኩዝ መቆም የማይችል ዝልፍልፍ ደካማ መሆኑ ነው።
በድንቁርናው ከዝልፍልፍነትና ከደካማነት ያወጣኛል ብሎ የመረጠው መንገድ የጎሣ ምሽጉ ውስጥ ገብቶ በ‹ሀ›ና በ‹ለ› መሀከል ያለውን ልዩነት መስበክ ነው፤ በ‹ሀ› ውስጥ ያለ ጎሠኛ በ‹ሁ›ና በ‹ሂ› መሀከል ያለው ልዩነት፣ በ‹ለ› ውስጥ ላለ ጎሠኛም በ‹ሉ›ና በ‹ሊ› መሀከል ያለው ልየነት አይታየውም፤ ስለዚህም ድንቁርናው ከጥላቻውና ከክፋቱ ጋር እየተጋገዘ ወደቀላሉ የጅምላ ውሳኔ ይመራዋል፤ የሽብርተኛነትም ዋናው የድንቁርና ዘዴ ጥፋት በጅምላ ነው።
በዘረኞችና በጎሠኞች አመለካከት አንድም አህጉር ውስጥ የተለያዩ ሰዎች አይኖሩም ነበር፤ የትም ቦታ ቢሆን ሰዎች እንደሰዎች እየተገናኙ እየተፋቀሩ አይጋቡምና አይዋለዱም ነበር፤ በደቡብ አፍሪካ የነጮች ዘረኛ አገዛዝ ‹የክልሶች ክልል› አይፈጠርም ነበር፤ የሰው ልጅ ሰው ሲሆን የሚያደርገው ያስደንቃል፤ በአንድ የአውሮፓ አገር አንድ ወያኔን እንደክፉ በሽታ የሚጠላ ሰው አውቃለሁ፤ ሚስቱ ወያኔ ነች! በአፍሪካ አዳራሽ ይሠራ የነበረ አንድ ግብጻዊ አውቃለሁ፤ ሚስቱ የአሜሪካን ይሁዲ ነበረች! እስክንድር ነጋ ሚስቱ ትግሬ ነች፤ ርእዮት ዓለሙ ጓደኛዋ ትግሬ ነው፤ የሰው ልጅ ሰውነቱን የሚያሳየው ለራሱ አስቦ፣ ከጅምላው ወጣ ብሎ ለብቻው ሲቆም ነው፤ ስለዚህም ለሽብርተኛነት ተፈላጊ የሆነው ነገር ሁሉ ድንቁርናም ሆነ ጥላቻና ክፋት ከጅምላ አመለካከት ጋር ርእዮትና እስክንድር የለባቸውም ብሎ በእርግጠኛነት ለመናገር ይቻላል፤ ስለከሳሾቹ ሳይታለም የተፈታ ነው፤ እነሱው ይናገሩታል፤ ደፍረው የማይናገሩት አሸባሪነታቸውን ብቻ ነው።
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11605/

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ደማቅ የተቃውሞ ትእይንት ተደረገ::

ሳዲቅ አህመድ

በአዲስ አበባ ታላቁ አንዋር መስጂድን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ ዋናዋና ከተሞች ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!›› በሚል መሪ ቃል ህዝበ ሙስሊሙ እያካሄደው ያለው መስጂድ ተኮር የዘመቻ እንቅስቃሴ አካል የሆነው እና የዘመቻው ማጠናቀቂያ የጁምኣ የተቃውሞ ትእይንት በደመቀ መልኩ ተካሂዷል::
Ethiopian Muslims protest, Addis Ababa (March 28, 2014)
ህዝቡን ከመስጂዱ ለመነጠል በመንግስት በኩል እየተሰራ ያለውን ህገ ወጥና ኢ-ህገ መንግስታዊ ስራም ለራሱ ተረድቶ ላልሰሙት ሁሉ በማሰማትና መስጂዶቹን በዒባዳ በማድመቅ ላይ ነው የሚገኘው፡፡ ይህ ወቅታዊና አንገብጋቢ የመስጂድ ባለቤትነትን የማረጋገጥ እንቅስቃሴ የመንግስትን እና የመጅሊስን ሴረኞች እንቅልፍ ማሳጣቱንም ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡ የውስጥ መረጃዎች እያጋለጡ ነው፡፡ ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!››ዘመቻ የዛሬው ጁሙአ ድረስ ቀጥሎ የቆየ ሲሆን በአዲስ አበባና በተመረጡ የክልል መስጂዶች ላይም አስቀድሞ የነበሩንን ቋሚ ትዝታ ጥለው ያለፉ ግዙፍ ተቃውሞዎችን በሚያስታውስ መልኩ የደመቀ የተቃውሞ ስነስርአት በማድረግ በሰላማዊ ሁኔታ ዘመቻው መጠናቀቁ ታውቋል::
በዚህም መሰረት ከቀኑ ስድሰት ጀምሮ በአዲስ ወደ አዲስ አበባ አንዋር መስኪድ እና በተለያዩ ከተሞች በሚገኙ የተቃውሞ ወደተመረጡ መስኪዶች የተመመው ህዝበ ሙስሊሙ የመስኪዶችን ውስጥ እና ደጅ በመሙላት መስኪዶቹ የራሱ ሃብት መሆናቸውን እና ሙስሊሙ ህዝብ ሰላም ፈላጊ መሆኑን በደመቀ ተቃውሞ ነጭ ምልክቶችን በማውለብለብ ገልጿል::
ህዝበ ሙስሊሙ ዘመቻውን በተሳካ መልኩ በማድረግ ሰላማዊ ተቃውሞውን አሰምቶ ከኮሚቴው ጎን ዛሬም ቃሉን አክብሮ እንደቆመ በማሳየት በሰላም መመለሱን ለማረጋገጥ ተችሏል:: [ተጨማሪ ፎቶዎችን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ] [ቪዲዮዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ]
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11586/

የቀድሞው የጋምቤላ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፈኑ

“ወያኔ እጅ ገብተዋል”

south sudan juba


የጋምቤላ ክልልን ሲመሩ ቆይተው ባለመስማማት የኮበለሉት የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፍነው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ዜናው በገለልተኛ ወገን ባይገለጽም ኖርዌይ በስደት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይ በኢህአዴግ በጥብቅ የሚፈለጉ ሰው ነበሩ።
በመለስ ዜናዊ ውሳኔ በአኙዋክ ተወላጆች ላይ በጅምላ የተከናወነውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ተቃውሞ በማሰማት የኮበለሉት አቶ ኦኬሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ከማምራታቸው በፊት ኬንያ እንደነበሩ፣ ከኬንያ ወደ ደቡብ ሱዳን ለምን እንደተጓዙ የዜናው ምንጮች በይፋ ከመናገር ተቆጥበዋል።
ስማቸው እንዲደበቅላቸው የጠየቁ የጋምቤላ አስተዳደር ባልደረባ ለጎልጉል የአካባቢው ዘጋቢ እንደተናገሩት አቶ ኦኬሎ ደቡብ ሱዳን ሆቴል በተቀመጡበት መታፈናቸውን አረጋግጠዋል። “ወያኔ እጅ ገብቷል” ሲሉ ያከሉት እኚሁ ሰው “አቶ ኦኬሎ ብረት በማንሳት ወያኔን ለመታገል ከተነሱ ጋር ተቀላቅለዋል በሚል ስማቸው መመዝገቡንና ወደ ደቡብ ሱዳን ማቅናታቸው በመታወቁ ህወሃቶች እጅ ሊወድቁ ችለዋል” ብለዋል። ምንጩ ይህንን ይበሉ እንጂ አቶ ኦኬሎ አክዋይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀኑበትን ምክንያት በርግጠኛነት ሃላፊነት ወስዶ የገለጸ ወገን አልተደመጠም። ኢህአዴግም ቢሆን የቀድሞውን ሹመኛ ስለመያዙ ይፋ ያደረገው ነገር የለም።
ከደቡብ ሱዳን ቀውስ ጋር በተያያዘ የኑዌር ተወላጅ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጦር ጋር በመሰለፍ የሳልቫ ኪርን ሃይል ሲወጉ ከተገደሉ ወታደሮች መካከል የኢህአዴግን ሰራዊት መለያ የለበሱ ኑዌሮች መገኘታቸው ውዝግብ አስነስቶ እንደነበር ያመለከቱት ምንጭ “ደቡብ ሱዳን እየወጋት ካለው ኢህአዴግ ጋር አብራ የቀድሞውን የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳደር ከምድሯ ላይ እንዲታፈኑ መፍቀዷ ቅሬታ ያስነሳል” ብለዋል።
ከቤተሰባቸው ተነጥለው በስደት ከሚኖሩበት ኖርዌይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያመሩት የቀድሞው የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ደቡብ ሱዳን በህወሃት ሙሉ ቁጥጥርና ፈቃድ የምትንቀሳቀስ አገር መሆኗን እያወቁ ወደዛ ማቅናታቸውን ባለሥልጣኑ “ታላቅ ጥፋት” ብለውታል። ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። በቅርቡ አቶ ኦሞት ኦባንግ መኮብለላቸውና በብዙዎች ዘንድ አውሮጳ እንዳሉ ቢነገርም በትክክል ያሉበት አገር በይፋ አለመታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።
http://www.goolgule.com/okello-akway-arrested-in-south-sudan/

ኢህአዴግ የእምነት ተቋማትን በጥብቅ የሚቆጣጠርበት ህግ ሊያጸድቅ ነው

ህጉ ጣጣ እንዳያመጣ የሰጉ ኢህአዴግን እየመከሩ ነው

religions


ኢትዮጵያን ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ እየገዛ ያለው ኢህአዴግ የሃይማኖት ተቋማትንና ምዕመናኑን በጥብቅ የሚቆጣጠርበትን ህግ ለማጽደቅ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ። የህጉ ረቂቅ የደረሳቸው ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ኢህአዴግን አበክረው እየመከሩና በሚያመጣው አጠቃላይ መዘዝ ዙሪያ እያስጠነቀቁ ነው።
ጎልጉል ከዲፕሎማት ምንጮቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ኢህአዴግ በእምነት ተቋማት ላይ ቁጥጥሩን የሚያጠብቅበትንና ከሃይማኖት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውጭ መሰብሰብን፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግንና የተቃውሞ ድምጽ ማሰማትን የሚከለክል ህግ አዘጋጅቷል።
የዜናው ምንጮች ዝርዝር ህጉን ለጊዜው ይፋ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ የሚደነገገውን አዲስ ህግ ጥሰዋል በሚል የሚከሰሱ ምዕመኖች እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ የሚያዝ አንቀጽ አለበት። አዲሱ ህግ ከሽብርተኞች ህግ ጋር የሚጣቀስ እንደሆነም የጠቆሙት ክፍሎች ኢህአዴግ “ከእምነት ነጻነት” ጥያቄ ጋር በተያያዘና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ውስጥ ውስጡን እየነደደ ያለው ችግር ስላስጨነቀው ይህንን ህግ ለማውጣት መገደዱን አስረድተዋል። በሌላ በኩልም እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የሙስሊሞች ጥያቄ ከዚያም ጋር ተከትሎ የተከሰተው ደም መፋሰስ ወደፊት ሊያመጣ በሚችለው ጉዳይ ላይ ኢህአዴግን በብርቱ አሳስቦታል፡፡
ኢህአዴግ ከቀን ወደ ቀን ቀውስ እየተደራረበት እንደሆነ የተረዳችው አሜሪካ በከፍተኛ ባለስልጣኖቿ አማካይነት ኢህአዴግን እየመከረች እንደሆነ ከዲፕሎማቶች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከፖለቲካው ቀውስና በቀጠናው ካለው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አሜሪካ በተደጋጋሚ የህወሃትን ሰዎች በተናጠል እያነጋገረች እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። ዲፕሎማቶቹ እንደሚሉት አሜሪካ መለስ “ከተሰዉ” በኋላ አገሪቱን ማን እየመራት እንደሆነ በቅጡ ለመረዳት በሚያስቸግር ሁኔታ የስልጣን መዛነፍና ደረጃን የጠበቀ የስልጣን ተዋረድ አለመኖሩም አሳስቧታል። ኢህአዴግ ለህልውናዬ ያሰጋኛል በሚል መንግሥታዊ ባልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች /መያዶች/ ላይ ያወጣውን አፋኝ ህግም ጠቅሰዋል። ዲፕሎማቶቹ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ወቅቱ አሁን እንዳልሆነ አመልክተዋል።

Thursday, March 27, 2014

“ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም” ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሁለት ወር በፊት ወደ አሜሪካና የአውሮፓ አገራት ለስራ ጉብኝት ሄደው ነበር፡፡ አሁንም ወደ አሜሪካ ጉዞ ሊያደርጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ፡፡ የአሁኑ ጉዞ አላማ ምንድን ነው?

Eng. Yilkal Getnet Semayawi party chairman with Negere Ethiopia newspaper
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
ኢንጅነር ይልቃል፡- መጀመሪያ ያደረኩት ጉዞ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም፣ የሰራናቸውን እንዲሁም ወደፊት ልንሰራቸው ያሰብናቸውን ስራዎች፤ ሰማያዊ እንደ አዲስ ኃይል ሲመጣ የቆመላቸው ሀሳቦችና እምነቶች ምን እንደሆኑ ለማስተዋወቅ ታስቦ የተደረገ ነበር፡፡ የአሁኑ ግን ከበፊቱ የተለየና ለሰማያዊ ሊቀመንበር በሚል በቀጥታ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት የተደረገ ግብዣ ነው፡ ፡ የአሁኑ ወጣት የአፍሪካ መሪና ወደፊትም ለአገራቸው መሪ ሊሆኑ የሚችሉ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ጥሩ ስራ የሰሩ፣ በውድድር ከተመረጡ በኋላ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት በሚደረግ ምርጫ መመዘኛዎቹን ለሚያሟሉ ሰዎች የሚሰጥ እድል ነው፡፡ በመመዘኛዎቹ መሰረት በማሸነፌ የአሜሪካ መንግስት ሙሉውን ወጭ ሸፍኖ ለሶስት ሳምንት በአሜሪካ የመንግስት አወቃቀርና ዴሞክራሲን ጨምሮ በተግባር የሚሰጡ ስልጠናዎችን የማግኘትና፣ የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣናትም ባሉበት ከተለያዩ ተቋማት ጋርም ለመገናኘት እድል ይኖረኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መሪዎች ጋር ተወዳድረው ነው ያሸነፉት ማለት ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አዎ! ግን ሌሎች ያሸነፉ ተጨማሪ ሰዎች ይኑሩ አይኑሩ አላውቅም፡፡ ይህ የፕሬዝዳንቱም ‹ኢኒሸቲቭ› ይመስለኛል፡፡ ለእኔ ግን የተሰጠኝ አዲስ ትውልድ አመራሮች፣ ወደፊትም በአገራቸው መሪ መሆን የሚችሉ፣ ስትራቴጅካሊ የሚያስቡ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይም ሆነው መልካም ስራ ለሰሩ ሰዎች የሚሰጥ ልዩ የጉብኝት እድል ነው፡፡ በአጠቃላይ ውድድርም ተደርጎ የሚወሰድ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ይህንን እድል ሲሰጥ እርስዎ እንደ መሪም ሆነ ሰማያዊ እንደ ፓርቲ ያሸነፋችሁበትን ዋና ዋና መመዘኛዎች ነግረዋችኋል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሲመርጡኝ ዝርዝር መረጃዎችን ወስደዋል፡ ፡ መሰረታዊ የሚባሉትን ለምሳሌ ያህል የፖለቲካ ቆይታዬ፣ የትምህርት ዝግጅቴን፣ በፖለቲካው ውስጥ የነበረኝን ተሳትፎ የመሳሰሉትን መረጃዎች ለእጩነት በቀረብኩበት ወቅት ከእኔ ወስደዋል፡፡ ከዛ በኋላ ያስመረጠኝን ዝርዝር መስፈርት አላውቅም፡፡ ነገር ግን ወጣት (እስከ 45 አመት ባለው ውስጥ)፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ መልካም ስራ የሰራ፣ ወደፊትም የአገሩ መሪ ሊሆን የሚችል የሚሉት ዋና ዋና መመዘኛዎች እንደሆኑ አውቃለሁ፡ ፡ ይህም በተለይ ከሰማያዊ አንጻር ከሁለት ነገሮች አኳያ እንድናየው ያደርጋል፡፡ አንደኛው በምስራቅ አፍሪካ ያለውን ፖለቲካና እስካሁን ጠቅልሎ የያዘው ኢህአዴግ ነበር፡፡ ሌላ አማራጭ እንደሌለ አድርጎ ነበር የሚያየው፡፡ ሆኖም እንደዚህ አይነት እድል እንደ አሜሪካ ባለ ትልቅ መንግስት የተቃዋሚ መሪ የተለየ ስራ ሰርቷል ተብሎ ሲጋበዝ ሰማያዊ ፓርቲ አዲሱንና ወደ ፖለቲካ ያልመጣውን ትውልድ ወደ ፖለቲካው ለማምጣት በሚያደርገው ጥረት እንደ አንድ ማበረታቻ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ይህ በሌሎች መስኮች ከምናደርጋቸው የዲፕሎማሲ ስራዎች በተጨማሪ ለሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ ይህኛው ግብዣ ሲደረግለት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
ከአሁን በፊት ለሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በአሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ የ35 አገራት ኤምባሲዎች የ‹ኢትዮጵያ ፓርትነርስ ግሩፕ› የሚባለው ሲደረግ በአመታዊ ስብሰባቸው ላይ ዋና ተናጋሪ ሆኜ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካና ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ዋና የትግል እንቅስቃሴና የወደፊት አላማችን እንዳስረዳ የተለየ እድል ተሰጥቶኛል፡፡ ይህም ለፓርቲው ሌት ተቀን ለሚሰሩ ወጣቶች፣ እንዲሁም ሁል ጊዜም ቢሆን ወጣቱ ተከታይና ጀሌ እግረኛ ከመሆን አልፎ ራሱ ኃላፊነት የሚወስድ፣ መምራትና የራሱን መሪዎች ማውጣት የሚችል ትውልድ መምጣቱን የሚያሳይ መልካም ጅምር ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ከ9/11 እንዲሁም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ሶማሊያ ውስጥ ባለው ጥቅም ኢህአዴግ ላይ እስከመጨረሻ ግፊት ማድረግ አልቻለም ነበር፡፡ አሁን ለእርስዎና ለፓርቲዎ ይህን እድል ሲሰጥ ለኢህአዴግ የሚያስተላልፈው መልዕክት ምንድን ነው? የተቃውሞ ጎራውም ቢሆን እስካሁን የሚመራው በ1960ዎቹ ፖለቲከኞች ነው፡፡ አሁን የአሜሪካ መንግስት ይህን እድል ለእርስዎ እንደ መሪና ለሰማያዊ እንደ ወጣት ፓርቲ ሲሰጥ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚኖረው አንድምታ ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እንግዲህ ይህን ጉዳይ ህዝቡም ሆነ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ማህበረሰቡ እየተረዳው የመጣ ይመስለኛል፡፡ ባለፈው አርባ አመት በገዥውም ሆነ በተቃዋሚው ያለው በአንድ አይነት እድሜና የግራ ርዕዮት የሚሽከረከር ነበር፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ፖለቲካም ሆነ ኢትዮጵያን በሁሉም መመዘኛዎች ወደ ፊት ሊያራምድ አልቻለም፡፡ እንዲያውም ጥላቻ፣ ቂምና ቆርሾ፣ የእስር በእርስ መጠላፍና የዜሮ ድምር ፖለቲካ ሆኖ ቆይቷል፡ ፡ ያ ትውልድ ያላመጣውን ውጤትም ወጣቱ ያመጣዋል የሚል ነው፡ ፡ ኢትዮጵያ የወጣት አገር ነች፡፡ 70 ከመቶ የሚሆነው ከ35 አመት በታች ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ ክፍል በውክልና ደረጃም ሆነ አዲስ አስተሳሰብና ከበድ ያለ ነገር ይፈልጋል፣ ከዓለም ከተለያየ አቅጣጫ መረጃ ያገኛል፣ በአስተዳደጉም አንጻራዊ ነጻነት አለው፣ በአመለካከትም ቢሆን ይህ የህብረተሰብ ክፍል ወደ ፊት እየመጣ ነው፡፡ ከዚህም አንጻር በታክቲክም ሆነ በአመለካከት ይህን የህብረተሰብ ክፍል መደገፍ የሚያዋጣና አይቀሬነቱን የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡
ዋናው የኢህአዴግ የፖሊሲ መሰረት ማታለል ነው፡፡ ‹‹እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ ትበታተናለች፡፡›› በሚል የምስራቅ አፍሪካንም ሆነ የሶማሊያን የሽብር ሁኔታ እንደ ማታለያ እየተጠቀመ፤ እነሱ የስጋት ፖለቲካ ውስጥ መግባታቸውን ስለሚያውቅ እሳት የማጥፋት ስራ ነበር የሚሰራው፡ ፡ ይህ ግን መሰረታዊ መፍትሄ የሚያመጣ ሳይሆን ነገሮችን እያዳፈነ፣ ችግሩን እያባባሰ በመሆኑ እንዲሁም የጠቅላይነት ፖለቲካን ለቀጠናውም ሆነ ለኢትዮጵያ እየጠቀመ አለመሆኑ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ኃይሎች ተረድተውታል፡፡ አማራጭ የፖለቲካ ኃይልና መሰረታዊ የሆኑ የዴሞክራሲ መመዘኛዎችን ማምጣት፣ መሰረታዊ የሆኑ የዜጎች ልማትና ዴሞክራሲ ማፋጠን፣ በአቻነት የተመሰረተ ግንኙነትን ካልሆነ በስተቀር በጉልበትና በጠብመንጃ የሚደረገው አገዛዝ እንደማያዋጣ የተረዱበት ጊዜ ነው፡፡ አሜሪካኖች አባቶቻቸው የሞቱበት ነገር (the ideals of ower founding fa­thers) የሚሉት የሰውን ልጅ መብትና የሰብአዊ መብት ማክበር ለሁሉም አገራት መድሃኒት መሆኑን ራሳቸው አፍጋኒስታንና ኢራቅ ውስጥ በነበሩበት ወቅት አይተውታል፡፡ በየመን፣ በምስራቅ አፍሪካዋ ሶማሊያም ቢሆን ተመሳሳይ የእሳት ማጥፋት ፖለቲካ ለውጥ እንዳላመጣ ተገንዝበውታል፡፡ በየ ደረጃው በህዝብ ተሳትፎ የሚያድግ ዴሞክራሲና በዜጎችም ይሁን በአገራት መካከል በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት መምጣት ካልቻለ አፋኝነት እንዳልጠቀመ የተረዱበት ጊዜም ይመስለኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- እስካሁን ድረስ ዲያስፖራውም ሆነ አገር ውስጥ ያው የተቃውሞ ኃይል ድምጹን ለማሰማት ሲሞክርም የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ትኩረት አናሳ እንደነበር ይታወቃል፡፡ እናንተ ይህንን አጋጣሚ ስታገኙ ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በስርዓቱ ላይ ትኩረት እንዲሰጥ በአጽንኦት የምታስረዱት ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አንደኛ ከመንግስት ጋር መስራት በሚሉት መርህ ላይ ኢህአዴግ ስልጣን ስላለው ብቻ በአጭር ጊዜ የጮሌነት ግንኙነት፣ ከዛም በኋላ ለአሸነፈውና የኃይል ሚዛኑ ካደላው ጋር ግንኙነት የማድረግ ዋናው የዘመኑ መገለጫ፣ ስግብግብነትን መሰረት ያደረገ የካፒታሊዝም መርህ ስለሆነ በየትኛውም መንገድ ተሂዶ የአገርን ጥቅም ማስጠበቅ የሚባለው እንደማይጠቅም ማስረዳት እንፈልጋለን፡፡ መንግስት ቢያልፍም በህዝብ ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍን እያዩ እንዳላዩ ማለፍ ለዘላቂ የአገራቸው ጥቅም እንደማይበጅ፣ ሁል ጊዜም ቢሆን ግንኙነት መመስረት ካለበት ከአገሪቱና ከአገሪቱ ህዝብ ጋር እንደሆነ፣ ግንኙነቱ ታሪካዊና የህዝብን መሰረታዊ መብቶች ጠብቆ የሚደረግ እንጅ ከአንድ ቡድን ጋር የሚደረግ ግንኙነት ኢትዮጵያን ለመሰለ ታሪክና ክብሩን ለሚወድ ህዝብ ውሎ አድሮ የማይጠቅም መሆኑን፣ በአጠቃላይም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ፣ መሰረታዊ መብቶችና ሀሳቦች በሚከበርባቸው መልኩ የሚያራምድ አይነት አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ ግንኙነት እንዲያደርጉ ነው በዋነኛነት ማሳሰብ የምንፈልገው፡ ፡ ከአንድ ቡድን ጋር የሚደረግ የአጭር ጊዜ ግንኙነት ራሳቸውንም እንደሚጎዳቸው፣ በቀጠናው ይገኛል የሚባለውን መረጋጋትና ሰላምም ሊያመጣ እንደማይችል እንዲረዱት እንፈልጋለን፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ከዲያስፖራው ጋር በመገናኘት የምትሰሩት ሌላ ድርጅታዊ ስራስ ይኖር ይሆን?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ባደረገልኝ ግብዣ ላይ ለሶስት ሳምንት እቆያለሁ፡፡ የትኬትና ተመሳሳይ ጉዳዮችን ከሚሰሩት የአሜሪካ ሰዎች ጋር ስንነጋገር ከዚህ ውጭ አንድ ወር ያህል አሜሪካን አገር እንደምቆይ ገልጨላቸዋለሁ፡፡ በዚህም አጋጣሚ ባለፈው በአየር ንብረትና በድካም ምክንያት ያላዳረስኳቸው ቦታዎች ላይ ስብሰባ የማካሄድ ሀሳብ አለኝ፡፡ ምን አልባትም ወደ ለንደንና ካናዳ ልሄድ የምችልበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡ ይህ እንግዲህ ከዚህ ካለው ስራ፣ ከጉዞ ሰነዶችና ከጊዜም ጋር ተደማምሮ በሂደት የምናየው ይሆናል፡፡ በድርጅታዊ ጉዳይ ላይ ለመስራት እቅዱም ሀሳቡም አለን፡፡ እዚያው ያሉት ደጋፊዎቻችንም በጉዳዩ ላይ እየሰሩበት ይገኛሉ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ወደ ሌላ ርዕሰ-ጉዳይ ልውሰድዎትና፣ ባለፈው እሁድ ሴቶች በተሳተፉበት የታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስታችኋል በሚል ከተያዙ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ‹‹መረጃን ለማሰባሰብ›› በሚል ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ይህን እንዴት ያዩታል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- በዚህ ጉዳይ ከማዘንና ከማፈር ውጭ የምለው ነገር አይኖርም፡፡ ኢህአዴግ በዴሞክራሲ እየማለ፤ ለዜጎች እኩልነት፣ ለጎሳና ሀይማኖት እኩልነት፣ ለሴቶች እኩልነት ጠብመንጃ አንስተን በመዋጋት የልጅነት እድሜያችንን በበርሃ አጥፍተናል እያሉ፤ 23 አመት ቆይተው ግን ሴቶች ለነጻነት በተሰለፉበት ቀን ስለ አገራቸው አንድነትና ስለ መሰረታዊ መብቶች የጠየቁ ሰዎችን እስር ቤት ሲያጉሩ ምን ያህል የማይማርና ወደ ኋላ እየተንደረደረ የሚገኝ፣ የራሱን ሞት እየጠበቀ ያለ መንግስት እንደሆነ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ ከዚህ ውጭ ምንም አዲስ ነገር ባላይበትም ትግሉ ውስጥ መግባታችን ምን ያህል ትክክል እንደሆነ ግን አረጋግጦልኛል፡፡ እሱ የማይፈልገው ሀሳብ ከሆነ ለምንም ነገር የማይመለስና ሴት፣ ህጻን፣ ህጋዊም ሆነ አልሆነ ለእሱ ምኑ እንዳልሆነ፣ በስልጣኑ ላይ ለመጣ ወደኋላ የማይመለስ መንግስት መሆኑን ተረድተንበታል፡፡ ይህም ዘላለም ለመጨቆን የተዘጋጀ መንግስት በመሆኑ ወደ ትግል መግባታችን ትክክል መሆኑ እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ ይህም ለትግሌ መሰረት ስንቅ ከመሆኑ በተጨማሪ በኢህአዴግ ላይ አዝኛለሁ፣ አፍሬያለሁ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ባለፉት ሁለት አመታት አረቦቹ አብዮት አካሂደዋል፡፡ ዩክሬን ውስጥ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለውጥ ነበር፡፡ ለባለፈው አንድ አመት ተኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥም የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ በአንጻራዊነት እየተጠናከረ ነው፡፡ አመጽ እየተለመደ ከመምጣቱ፣ የኑሮ ውድነትና ጭቆናው ከመባባሱ ጋር ተዳምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣይነት የሚመጣውን ለውጥ እንዴት ነው የሚያዩት?
ኢንጅነር ይልቃል፡- መቼም እኔ የምናገረው ምኞቴንና የምሰራበትን ነገርም ነው፡፡ ከዛ ውጭ ያለውን ነገር ብንወደውም ባንወደውም ራሱ መምጣቱ ስለማይቀር፣ ስለ እሱ መናገር ለእኛ አወንታዊ አስተሳሰብ ስለማይበጅም ሆነ እርግማት ተናጋሪ ስለሚያሰኝ ማድረግ የሚቻለውን በጎ ነገር እያደረግን ብንሄድ የተሻለ ነው የሚሆነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ አይነት በዓለም የመጨረሻ ድሃ ለሆነ፣ ብዙ የጎሳና የእምነት መቃቃር በተፈጠረበት አገር፣ በሩቅም በቅርብም የኢትዮጵያን መረጋጋት የማይወዱ አካላት ባሉት ቀጠና ላይ ሆነን፣ እርስ በራሳችንም በተለያዩ የታሪክ ግጭቶች ውስጥ እያለን እንዲህ አይነቱ ለውጥ ባይኖር ደስ ይለናል፡ ፡ ነገር ግን አልፈለግነውም ማለት አይከሰትም ማለት አይደለም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲህ አይነት ጉዳይ እንዳይከሰት የተጠና፣ አስቀድሞ በድርጅቱ የተመራ፣ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ የሚካሄድ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር ሌት ተቀን ይሰራል፡ ፡ ሆኖም ገዥው ፓርቲ በጠቅላይነትና ባታላይነት እቀጥላለሁ ካለ ህዝቡ ውስጥ መሰላቸት በግልጽ ይስተዋላል፣ ችግሮች ከዕለት ዕለት እየተደራረቡ ነው፣ ህዝብ አገሩ ውስጥም ሆነ በአካባቢው የለውጥ ምሳሌዎችን እያየ ነው፣ ችግሩ መሸከም ከሚችለው በላይ ሆኖበታል፡፡
በመሆኑም እነዚህ ለለውጥ መሰረት የሆኑ ነባራዊ ሁኔታዎች እየመጡ ስለመሆኑ የፖለቲካ ተንታኝ መሆን አያስፈልግም፡፡ በዚህ ሁኔታ አገዛዙ ውስጥ ያሉት ሰዎች የሚፈተኑት ከመግዛትና ከመጨቆን አስተሳሰባቸው ወጥተው ወደ እውነታው ቀርበው ለለውጥ ይዘጋጃሉ ወይንስ በተለመደው ግትርነት ይቀጥላሉ? በሚለው ነው፡፡ በሌላ በኩል እኛም ደግሞ አማራጭ ሆነን፣ እነሱን ሳናስደነብር፣ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲፈጠር መቻቻልና ይቅር ባይነቱ ኖሮን አገራችንን ማዳን የምንችልበት ሆደ ሰፊነትና አስተዋይነት ፖለቲካ በሁለታችንም በኩል ይጠበቃል፡፡ ግን ይህን ታሪካዊ ጉዳይ ከሁለታችን አንዳችን ከሳትነው ሂደት በተፈጥሮ የሚያመጣው ጉዳይ አለ፡፡ ሁሌም ታሪክም፣ ስልጣኔም፣ የሰው ልጅም ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይለወጣል፡፡ ልቡን የደፈነ ሰው ካልሆነ በስተቀር ለውጥ አይቀሬ ስለመሆኑ የሚጠራጠር ያለ አይመስለኝም፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ምን ያህል ንብረት ይወድማል፣ ምን ያህል የሰው ነፍስ ይጠፋል፣ በሂደቱ ምን ያህል የተጠና እና ለአገራችን የሚጠቅም ለውጥስ ይመጣል የሚለው ነው እንጂ የሚያስጨንቀኝ ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ይህ ለውጥ ቢከሰት ለውጡን በሚገባው መልኩ ለማስተናገድና ለመምራት ትክሻ ያለው አካልስ አለ ብለው ያስባሉ?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኛ ሰማያዊ ይህን ለውጥ መሸከም የሚችል ትክሻ አለው ብለን ነው የምናምነው፡፡ በእኛ አገር ይህንን አይነት ነገር ደፍረን ስንናገር በሁሉም ወገኖች ዘንድ አይወደድልንም፡ ፡ ለምን እንደማይወደድም ይገባናል፡፡ ባይወዱትም መናገር አለብን፡፡ ከማይወደድበት ምክንያት የመጀመሪያው በጭቆና መንፈሳችን መላሸቁ ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹ይቻላል!›› ማለት እንደ ቅዠትና እብደት ይቆጠራል፡፡ ይህም ‹‹ይቻላል›› የሚለውን ከመጥላት፣ ከጭቆናው መብዛት፣ በተደጋጋሚ ከመክሸፍ የመጣ የአቅመ ቢስነት ችግር እንጅ የእኛ ችግር አይደለም፡፡ እነዚህ በጭቆና አስተሳሰብ ስር የወደቁት የእኛን አመለካከት እንዲይዙ ጥረት በማድረግ በተደጋጋሚ ስለ ጉዳዩ እንናገራለን፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ድርጅት ሆነን ስንቋቋም እኛ የተሻለ አማራጭ አለን፣ አገርና ህዝብን ወደተሻለ ደረጃ እናደርሳለን ብለን ነው፡፡ ስለሆነም ስለ ራሳችን ስለ ድርጅታችን በሙሉ ልብ ‹‹እንችላለን!›› ስንል፣ ሌሎች ድርጅቶች ቅር ይላቸዋል፡፡ ይህ ከፖለቲካ እውቀት ማነስ የመጣ ነው፡፡ እኛ እንደ ድርጅት ተቋቁመን ‹‹እንችላለን!›› ካላልንና ህዝብና አገርን ወደ ተሻለ ደረጃ እንደምናደርስ መናገር ካልቻልን ህዝቡ እንዴት ሊከተለን ይችላል? ለምንስ ጊዜያችንን እናጠፋለን?
ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው አንድ አመት ተኩል የፖለቲካ ነገር በቀላሉ የማይመዘን ሆኖ እንጅ መብት መጠየቅን፣ መነቃቃትን፣ ከአይቻልም ባይነት ይቻላል ባይነትን፣ አዲሱ ትውልድ የራሱን እጣ ፈንታ ለመወሰን በድርጅት የመታቀፍንና የመታገልን በአዲስ መልክ ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ይህም ለረዥም ጊዜ በወደቀና በከሸፈ የፖለቲካ አመለካከት ውስጥ በጣም ረዥም ጊዜን የሚጠይቅ ስራ ነው፡ ፡ ይህም በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን በርካታ የሰማያዊ ወጣቶች የራሳቸውን የህይወት አማራጭ ትተው በዚህ ጉዳይ ላይ ጥርሳቸውን ነክሰው፣ በግልጽ የፖለቲካ አመለካከት ሌት ተቀን ከአገዛዙ ጋር እየተጋፈጡ፣ እየታሰሩ፣ ዋጋ እየከፈሉ የመጣ ነገር ነው፡፡ በዚህ ሂደታችን ውስጥ ወጣቶች ወደ ፖለቲካው እንዲመጡ ማነቃቃት ችለናል፡ ፡ ከትልልቅ የአደባባይ ምሁራን፣ ከዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮች፣ ከውጭም ከአገር ውስጥም ክብርና ይሁንታን አግኝተናል፡፡
ከክርስትናም ሆነ እስልምና ሀይማኖት መሪዎችና አማኞች አካባቢም መከበር ችለናል፡፡ ከዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም ቢሆን እንደሚታየው ወጣትና ወደፊት አገራቸውን መምራት የሚችሉ ተብለን መወደስና መሸለም ችለናል፡፡ የዓለም አቀፉም ሆነ የአገር ውስጥ ሚዲያው እንደ አንድ የፖለቲካ ኃይል አይቶናል፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ለስልጣን መሰረት የሆኑት ነገሮች እነዚህ ናቸው፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ወጣቶች፣ የአደባባይ ምሁራን፣ ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡና ሚዲያው ሰማያዊን እንደ አንድ የፖለቲካ ኃይል ማየት ችሏል፡፡ በእነዚህ ኃይሎች ተቀባይነት ካገኘ አገሪቱን ለመምራት የሚያቅተው ምንም ነገር አይኖርም ማለት ነው፡፡ የራሱ አላማ፣ የራሱ ፕሮግራም አለው፡፡ ይህን ለማስፈጸም የሚችል ቆራጥ አመራር አለው፡፡ በእርግጥ ኢትዮጵያ ትልቅ አገር ብትሆንም ሰማያዊ ለውጥን በአግባቡ ለመረከብና ለመምራት የሚያስችል አቅም እንዳለው መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ዲያስፖራው የገንዘብም፣ የመረጃና የእውቀትም አቅም እንዳለው ቢታመንም ከ1997 በኋላ ግን ለአገሪቱ ፖለቲካ አሉታዊ ጎን እንደነበረው በስፋት እየተጠቀሰ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት እናንተ ከዲያስፖራው ተቀባይነት እያገኛችሁ ነውና መልካም ጎኑንና ፖለቲካውን ላይ አለው የሚባለውን አሉታዊ ተጽዕኖ እንዴት ነው የምታስታርቁት?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ አንድን አካል በቅራኔ መድቦ መታገል የተለመደ ባህል አይደለም፡፡ ለምሳሌ ሰማያዊ ፓርቲ ወጣቱ ላይ ያተኩራል ሲባል፤ በየትኛውም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ግን የሽማግሌዎችን፣ የአደባባይ ምሁራንንና የትልልቅ ሰዎችን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የሰማያዊ አመራር አገር ውስጥ ቢሆንም የራሳቸው የፖለቲካ ፋይዳ፣ ካፒታል፣ አንጻራዊ ነጻነት ያላቸው፣ የአገራቸውን ነጻነት በቀናነት የሚመኙ፣ በመረጃው በኩል ቅርብ በመሆናቸው በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ እገዛ ከሚያደርጉት በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ተቀባይነት አለው፡፡ ይህን ጉዳይ ሚዛናዊ በመሆነ መልኩ የመምራት ችግር ካልሆነ በስተቀር በውጭ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ከሚገኙት የተለዩ አይደሉም፡፡ አገር ውስጥ እንዳለው ሁሉ ውጭ ያለውም የአገሩ ሁኔታ ያሳስበዋል፡፡ የአገር ውስጡ የራሱ ሚና ይኖረዋል፡ ፡ በውጭ የሚኖረው ደግሞ የራሱ የሆነ ሚና ይኖረዋል፡፡
እነዚህን ሁለት ጉዳዮች አገር ውስጥ ያለው በተገቢው መንገድ ማስተባበር ይኖርበታል፡፡ አገር ውስጥም ውጭም ያለውን አጣጥሞ የማስኬድ ስራ ነው የምንሰራው፡፡ መሪነት ሲባል እኮ የሰዎችን አቅም ለግብ መጠቀም ነው፡፡ የትኛውም የማህበረሰብ ክፍል፤ አርሶ አደር፣ ነጋዴ፣ ውጭ ያለ፣ አገር ውስጥ የሚገኝ፣ የተማረም ይሁን ያልተማረ፣ ሁሉ ጥቅምና ፍላጎት አጣጥሞ ወደፊት መምራት ነው ዋናው ስራችን፡፡ ዲያስፖራውንም እንደ አፈንጋጭ፣ እንደ አጥፊና ለኢትዮጵያ ችግር ተጠያቂ አድርጎ ማየት በሰማያዊ ፓርቲ የተለመደ አይደለም፡፡
ባለፈው ጉብኝት ባደረኩበት ወቅት የዲያስፖራውን ድክመትና ስህተቶች ያልኳቸውን በአደባባይ ተናግሬያለሁ፡፡ እነሱም ከጊዜ ብዛትና ከመውደቅ መነሳት ብዙ የተማሩት ነገር አንዳለ ተረድቻለሁ፡፡ ይህን ጉዳይ አጣጥሞ የሚመራ አስተዋይ፣ ብልህና ሆደ ሰፊ መሪ ያስፈልጋል፡፡ ይህ እኛ እንደ ድርጅት አዲስ ብንሆንም በፖለቲካው መውደቅ መነሳት ከ1997 ዓ.ም ጀምረን የነበርን ሰዎች በመሆናችን የተፈጠሩትን ነገሮች በቅርበት እናውቃቸዋለን፡፡ ባገኘነው በቂ ልምድም ጉዳዩን በጥበብ መያዝ ችለናል፡፡ ወደፊትም በጥሩ ሁኔታ እንሄዳለን የሚል እምነት አለኝ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የዲያስፖራውን ጉዳይ ካነሳን አይቀር፤ ከ1997 በኋላ በነበረው ፖለቲካ ተስፋ ከመቁረጡም ባሻገር በቅንጅት አባል ፓርቲዎች መካከል ተከፋፍሎ እንደነበር ይነገራል፡፡ ባለፈው ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ዲያስፖራውን እንዴት አገኙት? አሁንስ ምን አዲስ ነገር ይጠብቃሉ?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኔ ስሄድ የምጠብቀው አነስ ያለ ነገር ነው፡፡ ትግል ውስጥ ስትገባ ያለውን አስቸጋሪ ነገር ቀይሬ ከዚህኛው ወደዚህኛው አሻሽለዋለሁ ነው እንጂ፣ ይህኛው አለኝ ብለህ አትኩራራም፡፡ የዓለም የመጨረሻ ድሃ አገር ነን፡፡ የፖለቲካ ባህላችን አስቸጋሪ ነው፡፡ የእምነት አገር ነው፡፡ የ1966 አብዮት የፈጠረው ችግር አለ፣ 1997 የፈጠረው ችግር አለ፡፡ እንደ ፖለቲከኛ ይህን ችግር እለውጣለሁ የሚል እምነት ይዤ ነው የተነሳሁት፡ ፡ ከላይ የተጠቃቀሱት ችግሮች በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት መኖራቸውን ብገነዘብም አንድ መልካም ነገር መኖሩ ሌሎቹን ችግሮች ያቃልላቸዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል የኢሳት መኖር በአገሩ ጉዳይ ተስፋ ቆርጦ የነበረውን የዲያስፖራ ማህበረሰብ መረጃ እንዲኖረውና ተነቃቅቶ እንዲጠብቅ በማድረግ መልካም ስራ አከናውኗል፡፡ በተለይ የሰማያዊ ወጣቶች ‹‹አይቻልም!›› በተባለበት አገር ትንሽም ነገር ሲሰሩ ሲታይና ይህም የማህበረሰባዊ ድህረ- ገጾችን ጨምሮ ለበርካታ ሰዎች መድረሱ አድናቆት አስገኝቶልናል፡፡
እንዲያውም እኛን ከልክ በላይ የማወደስና ነጻ አውጭ አድርጎ የማየት እንጂ በእኛ ላይ ቅሬታ ያለው ሰው የለም፡፡ ለዚህም እድሜያችን እንደመልካም አጋጣሚ ሊታይ የሚችል ነው፡ ፡ እድሜያችን፣ በኢህአፓ፣ በደርግ፣ በመኢሶን የተቋሰለው ትውልድ አለመሆናችን ለፍረጃ ክፍተት አልሰጠም፣ ሰውም እንዲጠላን ምክንያት አልሆነም፡፡ ይህ በእኛ ስራ ሳይሆን በትውልድ ያገኘነው መልካም አጋጣሚ ነው፡፡ እንዲያውም በሰማያዊ በኩል እንደ ችግር ይቆጠራል ከተባለ ሁሉም ኃይል የራሱ ለማድረግ ስለሚሞክር ሚዛን የማስጠበቅና ማዕከል ላይ ሆኖ የማሰባሰብን ሚና ነው እየተወጣ የሚገኘው፡፡
ከዚህ ውጭ ከርቀት ሆነው ወጣትነታችን ሲያዩ የቆዩና ትውልዱ ጫታም፣ ስደተኛና ይህ ነው የሚባል ቁም ነገር የማይሰራ የሚመስላቸው የነበሩ ሰዎች ስንቀራረብ ትልቅ አድናቆት ችረውናል፡፡ መጀመሪያ ላይ በሆይ ሆይታና በጮኸት የተሰባሰብን ቢመስላቸውም ስለ እኛ ካወቁ በኋላ ‹‹እንዲህ አይነት ወጣትም አለ?›› በሚል ተገርመውብናል፡፡ በመልካም ሁኔታም ነው የተቀበሉን፡፡ እስካሁን ያለው ተስፋ ሰጭ ቢሆንም አሁንም ትልቅ ስራ ይጠይቃል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ያለፉት የፖለቲካ ውድቀቶች በመፍራት ወጣቱም ሆነ ዲያስፖራው ፓርቲዎችን ለመቅረብ ይፈራል፡፡ ‹‹ምንድን ነው ማረጋገጫችን?›› የሚል ጥያቄም በስፋት ሲነሳ ይስተዋላል፡፡ ለዚህ ጥያቄ እናንተስ መልሳችሁ ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኛ የምንሰራው ለአገራችን ብለን እንጂ ማንም እንዲያወድሰንና እንዲያምነን ብለን አይደለም፡፡ የሰራነው ነገር ሲያሳምነው ይከተለናል፤ ያምነናልም፡፡ ባለፈው 10 አመት ውስጥ ፖለቲካው ውስጥ ስለነበርን በመውደቅ በመነሳቱ ላይም አልፈናል፡፡ የራሳችንን ታሪክ ያለን እንጂ ከምንም ዱብ ያልን ፖለቲከኞች አይደለንም፡፡ የሚያከብሩን ሰዎች አሉ፣ በቅርብ የተማርንባቸው ሰዎችም አሉ፣ በተግባር ውጣ ውረድ ውስጥም አልፈናል፡፡ ይህ ለመታመን በቂ ይመስለኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰማያዊን የመሰረትን ሰዎች ስብሰባ ላይ በአጋጣሚ የተገናኘን ሳይሆን ከእነ ድክመትና ጥንካሬያችን ለረዥም ጊዜ የምንተዋወቅ ሰዎች ነን፡፡ በጎሳ፣ በወንዝ ልጅነት ሳይሆን ነጻ በሆነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ተገናኝተን በደንብ የተዋወቅን ሰዎች በመሆናችን በቀላሉ እንዳንፈርስ መልካም እድል ይሰጠናል፡፡
በተጨማሪም ይህ አስተሳሰብ ከመውደቅ የመጣ እንጂ ከእኛ ጥፋት የመጣ አይደለም፡፡ ስጋቱ ቢኖርም እኛ በመታመን እንሰራለን እንጂ አያስጨንቀንም፡፡ ምክንያቱም ችግሩ ከእኔ አሊያም ከአንዱ ጓደኛዬ ድክመት የመነጨ ስላልሆነ ነው፡፡ አገራችን ውስጥ አለመተማመን በመኖሩ፣ ሰዎች ደጋግመው በመውደቃቸው፣ አጠቃላይ ክሽፈት በመብዛቱ የተፈጠረ የወል ስነ ልቦና ነው፡፡ ይህ እንደ አገር የጋራ ችግራችን በመሆኑ ይህን ባህል ለመቀየር እንሰራለን እንጂ አንድ ሰው ለምን አላመነኝም ብዬ አልጨነቅም፡፡ ይህን የወል ስነ ልቦና በድፍረት፣ ከራስ ወዳድነትና ከዝርክርክነት ወጥተን፣ አርዕያና ታማኝ በመሆን፣ የውሳኔ አሰጣጥም ሆነ የገንዘብ አወጣጥን ተጠያቂነት በተሞላበት መንገድ በመፈጸም፣ ከአባላት ጋር የቅርብ ግንኙነት በመመስረት፣ የስልጣን ልዩነትን በማጥፋት ሰው ከአሉባልታ ይልቅ በሳይንስና በምክንያታዊ ነገር እንዲመዘን ማድረግ ይቻላል፡፡
እኛ ልናደርግ የምንችለው ሰውን ተስፋ ያስቆረጡትንና ለመለያየት ምክንያት የነበሩትን ነገሮች መቀነስ ነው፡፡ አለመተማመኑ ግን ደጋግሞ የመክሸፉ ችግር እንጂ የሰማያዊ ልጆች ችግር አይደለም፡፡ የሰማያዊ ልጆች ከአሁን በኋላ ምንም ይምጣ እስካሁን ባደረጉት ነገር ብቻ ሊደነቁ ይገባቸዋል፡፡ ባለፈው አስር አመት ውስጥ የግል ህይወታቸውን መኖር እየቻሉ ለአገርና ለወገን ሲሉ ብዙ ስቃይን የሚቀበሉ ልጆችን ማፍራት ችለናል፡፡ ለነጻነታቸው የሚዘምሩ ወጣት ሴቶችን ማፍራት ችለናል፡፡ የወደቀውንና አይቻልም የሚለውን መንፈስ ማነቃቃት ተችሏል፡፡ የወደፊቱ እንዳለ ሆኖ በእስካሁንም ቢሆን ሊመሰገኑ ይገባቸዋል፡ ፡ አለመተማመኑ በውድቀት የመጣ እንደመሆኑ እሱን መቀየር የሚቻለው በስራ ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ለነበረን ቆይታ አመሰግናለሁ::
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11572/

በአዲስ አበባና አካባቢዋ የጅብ መንጋ ሰዎችን መብላቱ በምልኪነት እያነጋገረ ነው

ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)

ሙከራውን ማድረጉ ቢያንስ ኪሣራ የለውም፡፡ ውጤታማነቱን ግን እጠራጠራለሁ ብቻ ሣይሆን እንዲያውም መሣቂያ እንዳያደርጉን እሰጋለሁ፤ ክፉዎችና በሰው ስቃይ የሚደሰቱ ስለሆኑ በእሪታችን ቢሣለቁብን ማን ይከሳቸዋል? ከስም ባለፈ የሰላምን ምንነት ከማያውቅ ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ችግርንHyena's in Addis Ababa causing problems ማስረዳትና መፍትሔ ለማግኘት መመኘት ከምኞትና ከህልም አያልፍም፡፡ እናም ወያኔን በእሪታ ለማስበርገግ የሚቻል አይመስለኝም፤ ተስፋ ለማስቆረጥ አይደለም – ተስፋ ብሎ ነገር ቀድሞውንም ከሀገራችን ከጠፋች ሰንብታለችና ማንም ማንንም ተስፋ ሊያስቆርጥ አይቻለውም፡፡ መቼም የጨነቀው እርጉዝ ያገባል ነውና ወደአእምሯችን የመጣልንን ዘዴ ሁሉ አሟጠን መጠቀሙን የመደገፍ የሞራል ግዴታ ስላለብን እንጂ በአራት ከተሞች አይደለም በአራት መቶ ከተሞች እሪታችንን ብናቀልጠው ወያኔ ንቅንቅ አይልም፤ በጩኸታችን ከማላገጥም በዘለለ አንጀቱ በሀዘኔታ አይላወስም፡፡ የጅቦች ስብስብ በጩኸት እሩምታ ሣይሆን በአልሞ ተኳሽ አናብስት ነው የማያዳግም እርምጃ ሊወሰድበት የሚገባ፡፡ ዓሣማው ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ይወገዳል ወይም በምርጫ ሥልጣኑን ያስረክባል ብላችሁ ተጃጅላችሁ የምታጃጅሉ ወገኖች ካላችሁ – እንዳላችሁም ይታወቃል – ሕዝብን ከምታነሆልሉ ሌላ አማራጭ ብትፈልጉ ይሻላልና ጊዜና ምኞትን አታባክኑ፡፡ ሕዝቡ በዚህ ከዳሎል እሳተ ገሞራ ይበልጥ በሚያቃጥል የኑሮ ውድነት እየተቀቀለና እየተገነፈለ በግፍ አገዛዝ እየተሰቃዬ ባለበት ወቅት ወደ ተቃዋሚ ጽ/ቤቶች በብዛት የማይጎርፈው ለምን እንደሆነ መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ የደነዘዘ የመሰለው የሚተማመንበት አታጋይ ድርጅት ያገኘ መስሎ ስላልታየው ሆን ብሎ አድፍጦ እንጂ አንድ ሁነኛ ድርጅት ቢያገኝ በደቂቃዎች ውስጥ ምን ሊሠራ እንደሚችል በበኩሌ ይገባኛል – ሚያዚያ 30/97ን እዚህ ላይ ማስታወስ ይቻላል፡፡ ነገር ግን ሕዝቡ እንደዚያች  “ሙሽራው እየመጣ ነው፤ በተሎ ተዘጋጂ!” እየተባለ በተደጋጋሚ እንደተነገራትና የሚባለው ውሸት መሆኑን ስትረዳ “ካልታዘልኩ አላምንም” እንዳለችው ዕድለቢስ ሙሽሪት ሆኗልና እንዳንዳንድ የዋህ ታዛቢዎች ለነፃነት የመታገል ፍላጎቱ እንደተቀዛቀዘ የሚነገርለት ሕዝብ የሚያዋጣ መስሎ የሚታየው ታግሎ የሚያታግል ድርጅት ቢያገኝ ምን ተዓምር ሊሠራ እንደሚችል በቅርብ የምናየው ይመስለኛል፡፡ መነሻየ ወዳልሆነ ነገር ለምን ገባሁ?
አሣዛኝ ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አዲስ አበባና አካባቢዋ በጅብ መንጋ እየተወረረች ብዙ ዜጎች እየተበሉ ነው፡፡ በፉሪ ቆሼ ተራ በሚባለው አካባቢ፣ በአራት ኪሎ ግንፍሌ አካባቢ፣ ኮተቤ አዲሱ መንገድ አካባቢ ወዘተ. ሰዎች በጅብ መንጋ እየተጠቁ ሕይወታቸውን እያጡ ነው፡፡ ፍየልና በጎችማ በቀንም ሣይቀር እየተበሉ ነው፡፡ ጅብ ተፈጥሯዊ የሌሊት ይትበሃሉን ለውጦ ቀን ከሰው ጋር እየተጋፋ ያሻውን እያደረገ ነው፡፡ ከፍተኛ አደጋ ውስጥ ነን፡፡ “አንበሣን ፈርቼ ዛፍ ላይ ብወጣ ነብር ጠበቀኝ” እንደሚባለው የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማጥቃት ከወያኔ እስከ ዐረብ ጀማላ፣ ከ“ፌዴራል” ሠራዊት እስከ ጅብ አራዊት፣ ከተፈጥሮ ድርቅ እስከ ሰው ሠራሽ የቤተ ሙከራ ቫይረስ ሁሉም ይህን ዘመን ዳግም የማያገኘው ያህል በመቁጠር ይመስላል አናት በአናት ይረባረብበት ይዟል፡፡ የመጨረሻ ያድርግልን፡፡ ይሄ ሰሞነኛ የተፈጥሮ የጅብ መንጋ ደግሞ በሚገርም ሁኔታ ከወያኔ ጅቦች ላይ ተደምሮ ሕዝቡን መቆሚያ መቀመጫ እያሳጣ ይገኛል – ሕጻናትን ከጉያ እየነጠቀ መውሰድም ይዟል፡፡ ምን ዓይነት ፍርጃ ነው ጎበዝ!
እስኪ ይህችን ሴት እንዘንላት፡፡ በጀግንነቷና በአስተዋይነቷም እናክብራት፡፡ ነፍሷንም በነያዕቆብና በነአብርሃም ነፍሳት ጎን ለጎን እንዲያስቀምጥ ፈጣሪን እንለምንላት፡፡ የጀግንነት መገለጫ በግድ የመሣሪያ ተኩስና ግዳይ ማስቆጠር ብቻም አይደለም፡፡ እንዲህ ነው ታሪኩ፡፡
ድርጊቱ ከተፈጸመ አንድ ወር አልሞላውም፡፡ ሴትዮዋ ሥራ ለመግባት እንደወትሮዋ ማለዳ ላይ ትነሣና ትራንስፖርት ወደምታገኝበት ቦታ ጉዞዋን ትጀምራለች፡፡ ከቤቷ ወጥታ ጥቂት እንደተጓዘች ግን በጅቦች ትከበባለች፡፡ ይህች ቆራጥ ሴት የምታደርገውን ብታጣ ሞባይሏን ታወጣና ለባለቤቷ እንዲህ ትላለች፤ “ … አደራህን ከማንም ሰው ጋር እንዳትጣላ፡፡ ሰው ገደላት ብለህ ማንንም እንዳትጠረጥር፡፡ በጅቦች ተከብቤያለሁ፤ ሊበሉኝ ስለሆነ በጭራሽ አልተርፍምና እስከወዲያኛው ደህና ሁኑልኝ፤ ልጆቼንም ሣምልኝ፡፡…” ብላ ንግግሯን ከመጨረሷ የከበቧት ጅቦች ዘረጠጧት፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ቤተሰብና ጎረቤት ሲደርስ ከፀጉሯና ከጥፍሯ በስተቀር ሌላ የረባ የሰውነት ክፍል አላገኙም፡፡ በዚህ መልክ በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባና አካባቢዋ በጅብ መንጋ እየደረሰ ያለውን ያልተለመደ ወረራና ጥቃት ብናይ ምን መቅሰፍት ታዘዘብን የሚያስብል ትንግርት እንታዘባለን፡፡
ይህ ሁሉ ከወያኔ ጅቦች ያለፈ የእውነተኛ ጅቦች አስቀያሚ ድርጊት ምን ያመለክታል? ምልኪው ምንድን ነው?
ትናንት ማታ የሆነ ቦታ ከትላልቅ ሰዎች (elders)  ጋር እጫወት ነበር፡፡ ከልምድና ከአያት ከቅድመ አያት ከሰሙት ተነስተው የተገነዘቡትን ሲነግሩኝ ፈራሁ፡፡ የፈራሁት እኔም ከአንዱ ቦታ ስመጣ ወይም ወደ አንዱ ቦታ ስሄድ ጅብ እንዳያነክተኝ በመስጋት አይደለም፡፡ እንዲያ ብቻ ቢሆን ዕዳው ገብስ በሆነ – ያንድ ሰው ጉዳይ ነውና፡፡ ምልኪው ጥሩ ስላልሆነ ነው ክፉኛ የደነገጥሁት፡፡ ባህላችን በምልኪ ያምናል፤ እኔም፡፡
የጅቦች ባልተለመደ ሁኔታ እንደዚህ በጠራራ ፀሐይ ሣይቀር ሰዎችን መተናኮልና መቆርጠም ምልኪው በግምባር ክፉ ዘመን የሚመጣ መሆኑን በግልጽ የሚያመለክት ነው ይላሉ አብረውኝ ያመሹ “የምልኪ ኤክስፐርቶች”፡፡ ድርቅ ሊሆን ይችላል፤ ጦርነት ሊሆን ይችላል፤ የተፈጥሮ መቅሰፍት ሊሆን ይችላል፡፡ ብቻ አደጋ አለ አሉኝ፡፡ ለነገሩ የወያኔን የመጨረሻ ሰዓታት እየጠበቀ ላለ እንደኔ ያለ ሞኝ ዜጋ የወደፊቱ ጊዜ ከእስካሁኑ አሳሳቢ እንደሚሆን ቢገምት አይፈረድበትም፡፡ ባህላዊ ሥነ ቃሉም እኮ “እንዲህ ጨሶ ጨሶ የነደደ እንደሆን፤ ያመዱ ማፍሰሻ ሥፍራው ወዴት ይሆን” ይላል፡፡ ስለሆነም የምልኪውን መፃኢ ውጤት ማለትም አደጋውን ፈጣሪ ቀለል እንዲያደርግልን መጸለይ እንጂ ወደፊት – በጣም በቅርቡ – መሬትን ከሰማይ የሚደባልቅ ከፍተኛ ሀገራዊ ቀውስና ሚሌኒየማዊ የሪከርድ ደረጃ ሊሰጠው የሚችል አደጋ ሊከሰት እንደሚችል ከግምት ባለፈ እርግጠኛነት መተንበይ ይቻላል፡፡ አሁን እኮ ፊሽካው በኦፊሴል ባለመነፋቱ እንጂ ወያኔንና ጥምብ ሥርዓቱን የሚያስወግደው ሕዝባዊ ጦርነት ተጀምሯል፡፡ “እኔም በአንድ ቀን አልተቆመጥኩም” ብላለች አንዷ አክስቴ – ለልጇ፡፡ ጓዶች! ደርግ የወደቀው ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም ነው እንዴ? ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ መሆኑ ቀረ እንዴ? የነበረ አለ፤ ያልነበረ እንደ አዲስ አይመጣም፡፡ ወያኔዎች ሲወድቁ የተፈጠሩባትን ዕለት እንደ ኢዮብ አምርረው እንደሚራገሙና – ሊያውም ለመራገምም ዕድል ካገኙ ነው – ከዚያም ባለፈ እንደጪስ በንነው እንደሚጠፉ ቅንጣት ልንጠራጠር አይገባም፡፡ እናያለን!! ምን ቀረው?
ልብ አድርጉ፡፡ በቦቅቧቃነቱ የሚታወቀው ጅብ ልብ አግኝቶ እንኳንስ የቆመ ሰው ሊጥል ሞቶ አሳቻ ቦታ ላይ የወደቀን የሰው ሬሣ ለመብላት ራሱ ስንትና ስንት የመጠጋትና የመፈርጠጥ maneuvering ካደረገ በኋላ ነው እንደምንም ደፍሮ የሚጠጋና የሚበላ የነበረ፡፡ ጥላውን እየፈራ እንትኑን የትም እየዘራ አይግባኙን የሚሸመጥጥ ጅብ በርግጥም አንዳች ምልኪያዊ ነገር የልብ ልብ ካልሰጠው በስተቀር እንዲህ ያለ ድፍረት ሊያገኝ አይችልም፡፡ ለማንኛውም እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሀገራችንንና ሕዝቧን ይባርክ፤ ከጠላቶቿ ወጥመድም ይጠብቃት፡፡ ግን ግን አሁንም ፈራሁ …
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11577/

Wednesday, March 26, 2014

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር – 5 ቁልፍ አገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮችን ይዛ እነሆ በPDF ያንብቧት

Click here for PDF

- መዝሙረ ኢህአዴግ! (በላይ ማናዬ)Negere Ethiopia Semayawi Party Newspaper Issue5
- የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ከአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት በተደረገላቸው ግብዣ ወደ አሜሪካ ያመራሉ፡፡ በጉዞው ዓላማና በተለያዩ የአገራችን ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
-  ኢትዮጵያና የዩክሬኑ ግጥምጥሞሽ
- ባለ ቀለሙን አብዮት ማን ይመራዋል? (በጌታቸው ሺፈራው)
- አዲስ ጠብመንጃ በምንሽር፤
አገዳደሉ ሆድ የሚያሽር፡፡
(በዝክረ ታሪክ አምድ፡- አቶ ታዲዎስ ታንቱ)
- “የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ዘመቻ” (ግርማ ሞገስ)
- ኑሮ ሆነብን እሮሮ (ጋሻው መርሻ)
- የኢትዮጵያ ፖለቲካና የሴቶች ተሳትፎ (ኤልሳቤት ወሰኔ)
- ሰላማዊ ትግሉ መሪዎቹን ይሻል (ታምራት ታረቀኝ)
- ኢትዮጵያዊነት ለእኔ! (አፈወርቅ በደዊ)
- እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራሞች የሚተዋወቁበት ገጽ አለልዎት
መልካም ንባብ!
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11565/

Tuesday, March 25, 2014

የአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በተፈናቃዩች ተጥለቀለቀ

ፍኖተ ነጻነት

ተፈናቃዩቹ ከጎንደር አካባቢ ተነስተው ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ወደ ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ በመውረድ በእርሻ ስራ የተሰማሩ ገበሬዎች ናቸው፡፡ከ1996ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ደረጃ ‹‹ክልላችንን ለቅቃችሁ ውጡ››ሲባሉ ቆይተዋል፡፡Displaced Amharas from Ambo
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማስፈራሪያው ወደ ግድያ፣ድብደባና ወከባ በማደጉ ለአቤቱታ አካባቢያቸውን ጥለው አዲስ አበባ ለመግባት ተገደዋል፡፡ከተፈናቃዩቹ መካከል የተወሰኑት ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃን ጽ/ቤት በማምራት አፈ ጉባኤውን ለማናገር ቢሞክሩም ሊያገኟቸው አልቻሉም፡፡የአፈ ጉባኤው ጸሐፊ ጉዳያችሁ ታይቷል ወደ መጣችሁበት ተመለሱ››ያለቻቸው ቢሆንም ተፈናቃዩቹ ‹‹ብንመለስ ሊገድሉን ስለሚችሉ አንመለስም››የሚል አቋም ይዘዋል፡፡
ከ26 የሚልቁ ሰዎች በአደባባይ ድብደባ ደርሶባቸው እጅና እግራቸው እንደተሰበረ የሚናገሩት ተፈናቃዩቹ‹‹አቶ ጌጡ ክብረት የተባለ ግለሰብ በገበያ ቦታ በገጀራ ተቆራርጦ ህይወቱ ማለፉን በሀዘን ስሜት ተውጠው ይናገራሉ፡፡
በአዲስ አበባ ማረፊያ ባለማግኘታቸው ለችግር መጋለጣቸውን የሚገልጹት ተፈናቃዩቹ ወደ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ጽ/ቤት በመምጣት ‹‹ፍትህ እንድናገኝ ለኢትዩጵያ ህዝብ ሰቆቃችንን አሰሙልን››በማለት ተማጽነዋል፡፡
የአንድነት ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አቶ ስዩም መንገሻ ‹‹ህገ መንግስቱ በግልጽ እያንዳንዱ ዜጋ በፈለገው ክልል በመሄድ ንብረት ማፍራት እንደሚችል ቢደነግግም መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን ህገ ወጥና አስቸጋሪ ነው››ብለዋል፡፡
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11559/

የእሳት ፖለቲካ በኢትዮጵያ (Fire Politics in Ethiopia)

ይሄይስ አእምሮ፣ አዲስ አበባ

በሃይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ዙሪያ ሰሞኑን አንዲት መጣጥፍ ጽፌ ለድረ ገፆች ልኬ ነበር፡፡ ለኅሊናቸው ተገዢ የሆኑ አወጡት – አስነበቡን፤ እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ ለባህልና ለይሉኝታ ያደሩት እንዲሁም እነሱ በሚፈልጉት ሙዚቃ ብቻ ታንጎና ማሪንጌ መደነስ የሚፈልጉት ወደቅርጫታቸው ከተቱት – ይክተቱት፡፡ ሁሉም የመሰለውን የማድረግ መብት አለውና ያነበበም ያስነበበም፣ ያፈነም ያሳፈነም የኅሊናው ዳኝነት ይፍረደው ከማለት ውጪ በዚህ በውዥንብር ዘመን መወቃቀሱም ሆነ መካሰሱ ፋይዳ የለውም፡፡ ግን ግን የእውነት አምላክ ለሁላችንም እውነተኛውን የልቦናና የኅሊና ሚዛን እንዲሰጠን እጸልያለሁ፡፡ ሁለትና ሁለት ሲደመር አራት ብቻ የሚሆንበት ሃቀኛ ዘመን እንዲመጣልንም እንዲሁ፡፡ በተረፈ የልጆቼ ልጆች “Mother stomach is ranger.” ሲሉ እሰማለሁና በዚያ “ሜጀር” የተቃኘ የቅሬታ ዘፈኔን ጋብዣቸው በገዢዎቻችን አነጋገር ንቅድሚት እላለሁ፤ ሕይወት እንዲህ ናትና፡፡This is the third time Harar experienced a deadly fire.
አንድ የብዕር ወዳጄ ያቺን መጣጥፍ ካነበበ በኋላ በነካ እጄ በዚህች ወያኔያዊ የእሳት ፖለቲካ ላይ ጥቂት ነገር እንድል አሳሰበኝ፡፡ ርዕሲቱንም የሰጠኝ እርሱ ራሱ ነው – Please take the credit dear Mr. Thingummy, wherever you may be.
ሀገራችን ተመልካች ያጣ የሕዝብ ብዛት ብቻ ሣይሆን ጭንቅት የሚያዞሩ እጅግ በርካታ ችግሮች የሚርመሰመሱባት በመሆኗ አንባቢን ላለማስቸገር ወይም ብዙ አንባቢ የለም በሚል ተስፋ መቁረጥ ወይም “አድማጭና የእርምት እርምጃ ወሳጅ ኃላፊነት የሚሰማው ጤናማ ወገን በሌለበት የኳስ አበደች ሀገራዊ ምስቅልቅል ሁኔታ ውስጥ ተነቦስ ምን ፋይዳ ሊያመጣ?” ከሚል ብሶት የተነሣ ሆን ብለን እየተውነው እንጂ መጻፍ የምንፈልግ ዜጎች የምንጽፈበት ጉዳይ በሽበሽ ነው፤ በበኩሌ አድማጭ ቢኖር ሃያ አራት ሰዓት ብጽፍ የማይደክመኝና የሚያጽፍ ጉዳይም ሞልቶ የተረፈ መሆኑን የምገልጸው የሚያፍኑኝን ድረ ገፆች ደስ አይበላቸው በሚል የመከፋት ስሜት ሳይሆን ተናግረን አድማጭ ባለመኖሩ ሳቢያ በእጅጉ የምቆረቆር መሆኔን በሚጠቁም የቁጭት ስሜት ነው፡፡ የወያኔው የዘረኝነት አባዜ ካስከተለብን ተነግሮ የማያልቅ ሰቆቃና የግፍ አስተዳደር ጀምሮ እነሚሚ ስብሃቱን የመሳሰሉ የሥርዓቱ ዘውጋዊ አባላትና እበላ ባይ ሆዳም ደጋፊዎቻቸው ባቋቋሟቸው የሠራተኛ አስቀጣሪ ድርጅቶች አማካይነት የሚካሄደውን ዘመናዊ ባርነት ብንመለከት ጉዳችን በጽሑፍም ሆነ በቃል ተዘርዝሮ የማያልቅ አስገራሚ ፍጡራን ሆነናል – እኛ “ኢትዮጵያውያን”፡፡ ቴዲ አፍሮ “እዚህ ጋ’ም እሳት፣ እዚያ ጋ’ም እሳት፣ እሳት፣ እሳት፣እሳት…” ሲል እንዳቀነቀነው ሀገራችን ወያኔያዊ እቶን ላይ ተጥዳ በየአቅጣጫው እንደባቄላ አሹቅ እየተንገረገበች ናት፡፡ ፖለቲካው እሳት፣ ሃይማኖቱ እሳት፣ ፌዴራሉ እሳት፣ ፖሊሱ እሳት፣ ቀኑና ሣምንቱ እሳት፣ ወሩና ዓመቱ እሳት፣ ኑሮው እሳት፣ ባለሥልጣናቱ እሳት፣ ነጋዴው እሳት፣ ዳኛው እሳት፣ በሽታው እሳት፣ ርሀቡ እሳት፣…፡፡ ሁሉም በእሳት አለንጋ ይጋረፋል፤ ይጠብሳል፤ ይሸነቁጣል፤ የት እንድረስ? የትስ እንግባ? ከነዚህ ከሲዖል ካመለጡ ሽፍቶች የሚታደገን ማን ነው? አምላከ ኢትዮጵያ ወዴት አለ? ኤሎሄ! ኤሎሄ! ኤሎሁም!  በዚህ መከራችን ላይ ነው እንግዲህ ወያኔ በሐረርም በአዲስ አበባም እንደዚያች ተዘውትራ እንደሚነገርላትና “እዚህ አካባቢ እሳት ይነሳል ብያለሁ” ብላ ባስጠነቀቀች ማግስት ራሷ እንደምትለኩሰው የደሴዋ ዕብድ ሴት በሹምባሾቹ አማካይነት በሚፈልጋቸው ቦታዎች ላይ እሳት እየለኮሰ፣ እንዳይጠፋም ከልካይ ዘብ እያቆመ በሀገር ሀብትና በሕዝብ ዕንባ እየተዝናና የሚገኘው፡፡ ለማንኛውም አስታዋሼን ላመስግንና በጠቆመኝ ሃሳብ ዙሪያ እንዳመጣብኝ ትንሽ ልብከንከን፡፡  እውነትን ላለማየት ዐይነ ኅሊናቸው የታወረ፣  እውነትን ላለመስማት ዕዝነ ልቦናቸው የተደፈነ፣ አእምሯቸው በፀረ-ለውጥ ቫይረስ ለፈውስ ባስቸገረ ሁኔታ  “corrupted” ለሆነ የ“ሚዲያ ሰዎች”ም የቮልቴርን አባባል ባስታውሳቸው ቅር አይለኝም – ቮልቴር እንዲህ አለ አሉ፡- “በምትናገረው ሁሉ ባልስማማም መናገር የምትፈልገውን ጉዳይ በነፃነት መናገር እንድትችል ግን ሕይወቴንም ቢሆን እገብርልሃለሁ!” አይ ኢትዮጵያ! በሁሉም ድሃ፡፡ ግን ተስፋ አለኝ – ትልቅ ተስፋ፡- ወደፊት አንድ ቀን ይህ ሁሉ ድንቁርናችንና ከንቱ ትምክህታችን እንደጤዛ ሲረግፍልን ሰው እንደምንሆን፡፡
በዓለማችን የፖለቲካ ዓይነቶች ብዙ መሆናቸው ከናንተ የተሠወረ አይደለም፡፡ የድንበር ፖለቲካ፣ የውኃ ፖለቲካ፣ የዘር ፖለቲካ፣ የዘውግ ፖለቲካ፣ የውጭ ብድርና ዕርዳታ ፖለቲካ፣ የሀገር ውስጥ የድርቅ ጊዜና የርሀብ ወቅት ዕርዳታ ፖለቲካ፣ የሃይማኖት ፖለቲካ፣ … ዝርዝሩ ብዙና ኪስን ሳይሆን አንጎልን የሚቀድ ነው፡፡ ወያኔ በኢትዮጵያ ላይ ያልሞከረው የፖለቲካ ዓይነት ደግሞ የለም፡፡ እርግጥ ነው ወያኔ ብቻውን አይደለም፡፡ ይህ ቀረሽ የማይባል ሁለንተናዊ ድጋፍ ለወያኔዎች በገፍ እየሰጡ በ17 ዓመታት ውስጥ የሰው ኃይሉን ከሰባት ሰውነት ወደሚሊዮንነት በማሳደግ ፀረ-ኢትዮጵያ አቋማቸውን በተግባር የገለጡት የውጭ ጠላቶቻችንም በዚህ ኢትዮጵያን ወደፖለቲካዊ ቤተ ሙከራነት የመለወጡ ሂደት ውስጥ ያሳዩት ጉልህ ተሳትፎም ለአፍታ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ከዓለም ሕዝቦች መካከል እኛ ኢትዮጵያውያን ላይ ያልተፈተሸ ፖለቲካዊ መርዝ የለም፡፡ ባጭሩ የወያኔ ብቻ ሣይሆን የፈረንጆቹም guinea pig ሆነን የቀረን ብቸኛ መዘባበቻ ዜጎች ብንኖር እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡ እርግጥ ነው እነኢራቅንና አፍጋኒስታንን ብንረሳ አግባብ አይደለም – እኛን እየገረፈን ያለው የኃያላኑ የእሳት ወላፈን እነሱንም እየጠበሰ ነውና፡፡ “አልማሊኪ ቡሽ፣ ካርዛይ ቡሽና መለስ ቡሽ እያሉ ሃቀኛ ሰላም አይኖርም፡፡”
ወያኔ ተግባር ላይ ካዋላቸው ሕዝብን የማሰቃያና ሀገርን የማውደሚያ መንገዶች አንደኛው እሳት ነው፡፡ እንዲህ የምላችሁ ወዳጄ አሁን ስላስታወሰኝ ብቻ እንዳይመስላችሁ፡፡ ከጥንትም በሚገባ አውቀዋለሁ፡፡ ለነገሩ ጨካኝና አምባገነን መንግሥታት ለዓላማቸው ስኬት የማያደርጉት ነገር የለም፡፡ ደርግም በተወሰነ ደረጃ ይህን የእሳት ፖለቲካ ይጠቀምበት እንደነበር በጊዜው ሰምቻለሁ፡፡ ሞኙ ደርግ እሳትን ይጠቀምበት የነበረው ኮንትሮባንድን ከመቆጣጠር አንጻርና በጣም በጥንቃቄ እንደነበር በወቅቱ የነበሩ አሁን ድረስ ያስታውሳሉ፡፡ የወያኔ ግን የተለዬ ነው፡፡
በመሠረቱ ወያኔ ምን እንደሆነ መናገር የዐዋጁን በጆሮ ነው፡፡ ይሁንና ወያኔዎች በተጣባቸው የትውልድ መርገምት ምክንያትም ይሁን በሌላ ከሆዳቸውና ያሻቸውን እንዲሠሩ ከሚጠቅማቸው የጨበጡት ሥልጣን በስተቀር የኢትዮጵያዊነት ስሜት በጭራሽ የሌላቸው፣ እንዲያውም ከያዙት ጥቅምና ሥልጣን ያስወግደናል ብለው የሚፈሩት በቀን ሰመመንና በሌት ቅዠት የሚያባትታቸው የኢትዮጵያዊነት ስሜት በመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚልን ዜጋ ሁሉ በየሄደበት እያሳደዱና እየገደሉ በደም ባሕር እየዋኙ የሚኖሩ፣ ጥላቸውንም የማያምኑ የከተማ ወሮበሎች መሆናቸውን እዚህም ላይ በድጋሚ ማስታወሱ በአሰልችነት ሊያስወቅስ አይገባም፡፡ እናም አስታውሱ – ወያኔ የዜጎችን የላብ ውጤት የሆነ ሀብትና ንብረታቸውን ማቃጠል ብቻም ሣይሆን ሕዝብን በሠልፍ ኮልኩሎ እንደሂትለር የኦሽትዊዝ ቻምበር የማይፈልጋቸውን በጋዝ እየለበለበ ቢፈጃቸው የሰይጣናዊ ተፈጥሮው የሞራል ምሰሶ ክፋትና ጥፋት ነውና ደስታን የሚያስገኝለት እንጂ ሰብኣዊነት የሚሰማው ሩህሩህ ፍጡር አይደለም፡፡ ሰብኣዊነትና ወያኔ ዐይንና ናጫ ናቸው፡፡
ወያኔዎች እንደገቡ ሰሞን የምንሰማቸው ብዙ የእሳት አደጋዎች ነበሩ፡፡ እነዚያ እሳቶች እንደሰሞነኞቹ የሕዝብን አንጡራ ሀብትና ገንዘብ ለማቃጠል የታለሙ ሣይሆኑ ጫካና ደን የማያውቁት መደዴዎቹ ወያኔዎች ደቡብ ኢትዮጵያንም እንደሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለማራቆት የታቀዱ ደኖችን የማቃጠል ወያኔያዊ የክተት ዘመቻዎች ነበሩ፡፡ በርካታ የደቡብና የኦሮሞ ብሔር መኖሪያ አካባቢዎች በነዚያ ወያኔ በቀሰቀሳቸው የሰደድ እሳቶች ተቃጥለዋል – አንጀታቸው ለተፈጥሮም የሚጨክን አረመኔዎች ናቸው፡፡ በምክንያትነት ሲቀርብ የነበረው ግን የኦነግን ሸማቂዎች ከምንጫቸው ለማድረቅና መደበቂያ ቦታ ለማሳጣት የሚል ነበር፡፡ ትግራይ ውስጥ ወያኔን ሊደብቅ የሚችል ዋሻ ካልሆነ በስተቀር ደንና ጫካ እንዳልነበረ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን ጫካ ቢኖር ኖሮ ወያኔን ለማጥፋት በሚል ሰበብ የደርግ መንግሥት ነዳጅ በቦቴ መኪናዎች ጫካ ውስጥ እየደፋ በአብሪ ጥይትም በአሻጋሪ እየለኮሰ ሀገር ለማቃጠል የሚያበቃው የሞራል ድቀት ውስጥ እንዳልነበረ ያንጀቴን እመሰክራለሁ – ሰው ካልሞተ ሚስትም ካልተፈታች ወይ ካልሞተች አይመሰገኑም ወንድማለም፡፡ ደርግ ዜጎችንና ሀገርን በእሳት አይቀጣም፤ ደርግ ኢትዮጵያዊ ጨካኝ እንጂ እንደወያኔ ወፍዘራሽ የባንዳ ውላጅ አልነበረም፡፡ እሳት ባለጌ ነው፡፡ እሳት እጅግ መጥፎ ነው፡፡ ምሕረትን አያውቅም፡፡ እንኳንስ ዜጋህን ጠላትህንም ቢሆን በአግባቡ ውጋው እንጂ፣ በአግባቡ ቅጣው እንጂ ኢ-ሰብኣዊ በሆነ ሁኔታ በእሳት አትገርፈውም፡፡ እነሂትለርና ሙሶሊኒ እንኳንስ ዜጎቻቸውን ጠላቶቻቸውንም ቢሆን በሰደድ እሳት አልቀጡም፤ በእሳት መቅጣት የጀግና ሙያ ሳይሆን የፈሪ ዱላ ነው፡፡ ወያኔ ግን ከየትኛው የጀሃነብ ሰማይ እንደወረደብን አይታወቅም ይሄውና ጫካና ደንን ከማቃጠል አልፎ የምሥኪን ዜጎችን ቤትና ንብረት እንዳሻው በሚያዛቸው ኅሊናቢስ ጀሌዎቹ እያቃጠለ ይገኛል፡፡ ወያኔ እኮ በእሳትም ብቻ ሳይሆን እንደተራ ተንኮለኛ ዜጋ ምግብንና መጠጥን በመመረዝና የታወቀ ጠንቋይ ቤት ድረስም በመሄድ የሚጠላቸውን የሚያስወግድ ጉደኛ ፍጡር ነው፡፡ ኪሮስ አለማየሁ እንዴት ሞተ? አለማየሁ አቶምሳስ? በውነት ቆሻሾች ናቸው፡፡ ምን አድርገን ይሆን ፈጣሪ እነዚህ ለቅጣት የሰጠን ግን? እስኪ ወደዬኅሊና ጓዳችን እንግባና ራሳችንን በቅጡ እንመርምር፡፡
በዚያን ሰሞን ሐረር ውስጥ የተቃጠለው መንደር የዚሁ የወያኔን ዜጎችን በእሳት የመቅጣት የእሳት ፖለቲካ ያሳያል፡፡ የኢትዮጵያን ገንዘብ ለራሱ ፖለቲካ በመጠቀም ዜጎችን በአነስተኛና ቀጫጭን የሚባል አዲስ ፈሊጥ እያደራጀ አንዱን ርሃብተኛ ሌላውን ጥጋበኛ እያደረገ እናያለን፡፡ በጥቃቅን የማይደራጅን በጠላትነት በመፈረጅ በገቡበት እየገባ ያሳድዳቸዋል፡፡ ከወያኔ የተለዬ ነጋዴ ኑሮውና ግብሩ እሳት ሆነው እንዲያቃጥሉትና ከሀገር እንዲጠፋ ወይም በርሀብ አለንጋ ተገርፎ እንዲሞት ሲደረግ ወያኔን የተጠጋ ሆድ አደር ግን እምብርቱ እስኪገለበጥ እየበላና እየጠጣ ተንደላቅቆ ይኖራል፡፡ እንዲህ እንዲኖርም በመዥገሮች የተወረረችው እናት ሀገር በወያኔዎቹ አማካይነት ለአንዱ የእንጀራ እናት ለሌላው ደግሞ የእውነት እናት ሆና ለሆዳም ጥገኞቹ ሁሉንም ነገር እያመቻቸችላቸው ትገኛለች፡፡ ለምሳሌ በወያኔ ማኅበር ያልተደራጀ ዜጋ ሁለት በሁለት ለሆነች የንግድ ቤት ከገቢው ጋር ፈጽሞ የማይመጣጠን እጅግ ከፍተኛ ኪራይና ግብር እንዲከፍል ሲገደድ (ሂድ አትበለው እንዲሄድ ግን አድርገው በሚሉት ፈሊጣቸው) ለሆዳሞቹ ግን ካስፈለገ ካለኪራይና ካለአንዳች ግብር በሕዝብ ገንዘብ እንደፈለጉ ይሆናሉ፡፡ ባንኮች ሳይቀሩ ለነሱ የግል ጥገቶች ናቸው፡፡ የሀገር ስሜት ዛሬ ያልጠፋ ታዲያ መቼ ይጥፋ?
ይህ መሰሉና ሌላው ግፍ ሁሉ አልበቃ ብሎ ነው እንግዲህ የእሳቱ ፖለቲካ በሀገር ደረጃ እየተፋፋመ የሚገኘው፡፡ እንደሰማነው በሐረር ከአንዴም ሁለት ጊዜ ቃጠሎ ተነስቶ በብዙ ሚሊዮን የሚገመት ብርና ሀብትና ንብረት ወድሟል፡፡ ይህ የሆነው በወያኔው ፈቃድና ይሁንታ መሆኑን የምንረዳበት መንገድ ደግሞ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ሲደረግ አስቀድሞ የተዘጋጀው የወያኔ ጦር እሳቱን ከብቦ አላሰቀርብም ማለቱና የእሳት አደጋ ሠራተኞችም እሳቱ የሚፈለገውን ጥፋት ካገባደደ በኋላ ሥራቸውን እንዲሠሩ መፈቀዱ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ግፍ ከኢትዮጵያ ውጪ የሚደረግ አይመስለኝም፤ እንዲያውም አይደረግም፡፡ ምክንያቱም የሀገር ዜግነቱን የካደና ሀገር እየቸረቸረ የሚሸጥ የሀገር መሪ ከኢትዮጵያ ውጪ በየትም ሥፍራ ይኖራል ብዬ አላምንምና፡፡
የሐረሩ እሳት መንስኤው ወያኔ ሆኖ ዓላማው ደግሞ ቦታውን ለወያኔያዊ ባለሀብቶች ለመስጠትና በእግረ መንገድም ተቀናቃኝ ኢ-ወያኔያዊ ባለሀብቶችን ለማክሰም ነው – ይህን እውነት ለማወቅ ጠንቋይ መቀለብ አያስፈልግም፡፡ በጣም ግልጽ ነው፡፡ መንታ ዓላማ  ያነገበ ቃጠሎ ነበር ማለት ነው፡፡ አንደኛውና ዋነኛው በሥርዓቱ የማይፈለጉ ዜጎችን ማደኽት – ሁለተኛው በነሱ ቦታ ደግሞ ለሥርዓቱ ዕድሜ ቀን ከሌት ተንበርክከው ሰይጣንን የሚለምኑ ፍቁራን አባላትንና ደጋፊዎችን ማቋቋም፤ በቃ፡፡ በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ ይባላል፡፡ በኢትዮጵያ መሬት፣ በኢትዮጵያውያን ሀብትና ንብረት ፀረ-ኢትዮጵያ የሆኑ የመንግሥትን ሞሰብ ገልባጮችና ደጋፊዎቻቸው ይገባበዙበታል፤ ይጠቃቀሙበታል፡፡ እንግዴ ልጅ ሀገር ሻጭ ማዕዱን ሲጫወትበት ልጅ ከበይ ተመልካችነትም ወርዶ የሥቃይ ሰለባ ሆኗል፡፡ እየተራቡ በሀገር መኖርም ክልክል ሆኖ ለሞትና ለስደት መዳረግ ዕጣችን እንዲሆን ተፈርዶብናል፡፡ ይህን ቅሚያና ዘረፋ፣ ይህን የግፎች ሁሉ የበላይ የሆነ ግፍ በእሳት አማካይነት እውን ለማድረግ ደግሞ የኢትዮጵያን መለዮ ለባሽ ይጠቀማሉ -በዓይነቱ ልዩ የሆነ የታሪክ ምፀት ማለት ይህ ነው፡፡ ዋ እኔን! ይህች ቀን ልታልፍ እምቢልታው ሲነፋ እነዚህ ጉግማንጉጎች ምን ይውጣቸው ይሆን?
አዲስ አበባም ውስጥ በትንሹ ሁለት ያህል ቃጠሎዎች በነዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ ተከስተዋል፡፡ አንደኛው የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ሲሆን ሌላኛው በአንድ ግለሰብ ቤት የደረሰና የሦስት ሰዎችን ሕይወት የጠየቀ ቃጠሎ ነው፡፡ ያሳዝናል፡፡ ነፍሳቸውን ይማር፡፡ የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤቱ ግን ያጠያይቃል፡፡ እርግጥ ነው – ቃጠሎው ተፈጥሯዊ ሊሆን ይችላል፡፡ እንደማንኛውም አደጋ ሆን ተብሎ ሳይሆን ድንገት ሊነሳ የመቻሉ ዕድል እንዳለ ሆኖ ከወያኔ ባሕርይ ተነስተን ስንገምት መነሾው ፖለቲካዊ አንድምታም ሊኖረው እንደሚችል ብንጠረጥር “ጠርጣሪዎች(skeptics)” ተብለን ልንታማ አይገባም፡፡ እንዲያውም ስንትና ስንት ጥበቃ የሚደረግለት ትልቅ ድርጅት በቀላሉ ለእሳት ይዳረጋል ብሎ ከማሰብ አለማሰብ ይሻላል ብለን ብንከራከር የሚቻል ይመስለኛል፡፡ ስለሆነም ከድንገቴ አደጋነት ይልቅ የወያኔው ተንኮል እንደሚኖርበት መገመት አይከብድም፡፡ ወያኔ ለምን ብርሃንና ሰላምን ያቃጥላል? ምን ያገኛል? ከመገመት ባለፈ እውነተኛውን ነገር ማወቅ ሊከብድ ይችላል፤ መገመት ደግሞ ለማንም የማይከለከል የሁሉም መብት ነው፡፡
ከሁሉም በፊት ግን አንድ አጠቃላይ እውነት መኖሩን እንመን፡፡ ያም እውነት ወያኔ ቢቻል ቢቻል ኢትዮጵያ እንዳለች ብትቃጠል ወይም እንጦርጦስ ብትወርድ ደስ ይለዋል እንጂ የማይከፋ መሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ስሟ ሲነሳ የሚዘገንናቸውና ጠበል በመጠመቅ ያለ ሰው ላይ እንደተከሰተ ሰይጣን የሚያንዘረዝራቸው እነበረከትንና ሣሞራን የመሳሰሉ መፃጉዕ ዜጎች የሚገኙበት መንግሥታዊ መዋቅር የኢትዮጵያ ታሪክ የሚዘከርበትና አእምሯዊ ቅርስ የሚቀመጥበት ማዕከል ቢቃጠል አይደሰትም ብሎ ማሰብ የዋህነት ይመስለኛል፡፡ በዕንቆቅልሽ ሀገር ውስጥ ልንጠብቅ የማይገባንን ነገር ብንጠብቅ ብልህነት እንጂ ትዝብት ውስጥ ሊያስገባን የሚችል ሞኝነት አይደለም፡፡
በመሆኑም ወያኔ ይህን የእሳት ፖለቲካውን በመጠቀም ዜጎችን ራቁታቸውን ማስቀረቱንና ወደበረንዳ ሕይወት መለወጡን እንዲያቆም፣ የዘመናት ቅርሳችንን እያቃጠለ ታሪክ አልባ ሆነን እንድንቀር ማድረጉን እንዲገታና እስከተቻለ ደግሞ ነፃነታችንን እውን ለማድረግ የምንችልበትን የጋራ ሥልት መቀየስ እንድንችል የጋራ ጥረት እንድናደርግ ጥሪየን አቀርባለሁ፡፡ ሰላም፡፡
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11556/

የግብጽ ፍርድቤት 530 በሚሆኑ የሙስሊም ወንድማማች አባላት ላይ ሞት ፈረደ

ተከሳሾቹ ለአንድ ፖሊስ ኃላፊ መሞት ተጠያቂዎች ናቸው

egypt 5


* ውሳኔው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል
በሕዝብ ከተመረጡ በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣናቸው የተወገዱትን የቀድሞ የግብጽ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲን በመደገፍ በፖሊስ ጣቢያ ላይ አደጋ አድርሰው የነበሩ 529 ተጠርጣሪዎች ትላንት ሰኞ ዕለት የሞት ቅጣት ተበየነባቸው፡፡ የብይኑ ፍጥነትና የተፈረደባቸው ተከሳሾች ብዛት አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል፡፡ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ከሆነ ውሳኔው ለይግባኝ የሚቀርብ ሲሆን በሙስሊም ወንድማማች ላይ ሆን ተብሎ የተነጣጠረ ጥቃት እንደሆነ ዘግቧል፡፡
egypt 3በዓለማችን በቅርብ ጊዜያት ከተካሄዱ የሞት ፍርድ ብያኔዎች በብዛትም ሆነ በፍጥነት ለየት ያለ እንደሆነ የተጠቀሰለት ይህ የፍርድ ሂደት በግብጽ የሕግ የበላይነት እየከሰመ የሄደ መሆኑን የሚያመላክት ነው ሲሉ በርካታ የሕግ ምሁራን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ተከሳሾቹ በሙሉ የሙስሊም ወንድማማች አባላትና የቀድሞው ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ ደጋፊ መሆናቸው ብያኔው እውነተኛ የፍርድ ሂደት የተከተለ ሳይሆን ወደፊት ሊነሳ ለሚችል ተቃውሞ ማስተማሪያ እንዲሆን ታቅዶ የተከናወነ ነው ሲል የፍትሕ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ አሶሺየትድ ፕሬስ በተጨማሪ ዘግቧል፡፡
ተከሳሾቹ የቀረበባቸው ክስ ባለፈው ነሐሴ ወር ሚኒያ በተባለች የግብጽ ከተማ በሚገኝ የፖሊስ ጣቢያ ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በተከናወነ የነፍስ ግድያ፣ የግድያ ሙከራ፣ መንግሥትን ለመገልበጥ ሕገወጥ ቡድንን መቀላቀል እና የመንግሥትን የጦር መሣሪያ መስረቅ በሚሉ ወንጀሎች ናቸው፡፡ በወቅቱ በፖሊስ ጣቢያው ላይ በደረሰ ጥቃት የሚኒያ ከተማ ምክትል የፖሊስ ኃላፊ ሞሐመድ አል-አታር መገደላቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጥቃት በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዘው ወታደራዊው አገዛዝ በሙስሊም ወንድማማች ደጋፊና አባላት ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነና አሰቃቂ ጥቃት በማድረስ በዚያን ወቅት ብቻ ከ600 በላይ ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል፡፡
ከ545 ተከሳሾች ውስጥ 528ቱ ጥፋተኞች ሆነው በመገኘታቸው የሞት ፍርድ እንደተበየነባቸው የመንግሥት ሚዲያ ሲያስታውቅ አንዳንድ ባለሥልጣናት ቁጥሩ 529 እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 150 በሌሉበት ፍርዱ የተበየነባቸው ሲሆን የተቀሩት ግን በነጻ ተለቅቀዋል፡፡ በግድያው የተሳተፉት ብቻ ፍርድ ሊበየንባቸው ይገባል በማለት የሚከራከሩ ወገኖች እንደሚሉት በማስረጃነት የቀረቡት 20 የሚሆኑ የቪዲዮ ምስሎች እንደሚያሳዩት የተወሰኑ ሰዎች የፖሊስ አዛዡን በብረት በትር ሲደበድቡ እና አንድ ሐኪም ደግሞ በእሣት ማጥፊያ የኦክስጂን ሲሊንደር (ካንስተር) የፖሊሱ ጭንቅላት ሲፈረክስ ታይቷል ይላሉ፡፡
መሐመድ ሙርሲ
መሐመድ ሙርሲ
ሁለት ቀናት ብቻ በፈጀው በዚህ የፍርድ አሠጣጥ ሥርዓት ላይ የተከሳሽ ጠበቆች በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የማስረጃ ሰነዶችን ለመመልከትም ሆነ በቂ ጊዜ አግኝተው የደንበኞቻቸውን ጉዳይ ለፍርድቤቱ ለማስረዳት እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ከፍተኛ ባለስልጣን ለአሶሺየትድ ፕሬስ እንደገለጹት ከዚህ ዓይነቱ የሞት ብያኔ በኋላ ማንም በተመሳሳይ እንቅስቃሴ ውስጥ እንደማይሳተፍ ጠቁመዋል፡፡ የፍርዱን አካሄድ ሲገልጹም “ሁኔታው እጅግ ለየት ያለ ነው፤ እያንዳንዱን ተከሳሽ እየጠራን ክሱን እንዲከራከር፣ ጠበቃ እንዲያቆም፣ ወዘተ ለማድረግ በቂ ጊዜ የለንም” ብለዋል፡፡ በፍርዱ ሂደት ላይ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጣቸው በጠየቁ ጠበቆች ላይ ችሎቱ የመሩት ዳኛ ሰዒድ ዩሱፍ ጠበቆቹን በቁጣ መዝለፋቸው አብሮ ተዘግቧል፡፡
የሞት ፍርዱ በግብጽ ሙፍቲ (የአገሪቱ ከፍተኛ እስላማዊ ባለሥልጣን) መጽደቅ ያለበት ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የተከሳሽ ጠበቆች ይግባኝ በማለት ፍርዱን ለማስቀየር እየሠሩ መሆናቸው ተገልጾዋል፡፡
ሞሐመድ ባዴይ
ሞሐመድ ባዴይ
ሌሎች ወደ 700 የሚጠጉ የሙስሊም ወንድማማች ተከሳሾች ዛሬ ማክሰኞ ለፍርድ ይቀርባሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል የወንድማማቹ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞሐመድ ባዴይ እና ሌሎች ከፍተኛ ኃላፊዎች ይገኙበታል፡፡ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን የተወገዱት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሞሐመድ ሙርሲም በቅርቡ ለፍርድ የሚቀርቡ ሲሆን ዛሬ የሚቀርቡትን ጨምሮ ሙርሲም ሞት ሊፈረድባቸው ይችላል የሚል አስተያየት እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ዓለምአቀፍ ተጽዕኖን በመፍራት ሙርሲ ላይ ሞት የመፈረዱ ጉዳይ አጠራጣሪ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ አመልክተዋል፡፡
የሰኞ ዕለቱን ብያኔ ተቃውሞ የቀረበበበትን ያህል የፍርዱን ትክክለኛነት የደገፉ ግብጻውያንም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ አሚን ፍቱሕ የተባሉ የካይሮ ነዋሪ ለአሶሺየትድ ፕሬስ እንደተናገሩት “ቁርዓን እንደሚለው ገዳዮች ሞት ይገባቸዋል፤ እነዚህ ሰዎች ግድያ ስለፈጸሙ በአጸፋው መገደል ይገባቸዋል” ብለዋል፡፡
ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሂውማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል በሰኞው ዕለት ፈጣን የሁለት ቀን ብያኔና በቀጣይ የሚደረጉት የፍርድ ሂደቶች እጅግ ያሳሰቧቸው መሆኑ ገልጸዋል፡፡ አምነስቲ ብያኔውን “በቅርብ ዓመታት በዓለማችን ከተካሄዱ የሞት ብያኔዎች በዓይነቱ ብቸኛው” በማለት ሲገልጸው ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ደግሞ “ኅሊናን የሚያስደነግጥና የፍትሕ ውርጃ የታየበት” ነው ብሎታል፡፡ (ፎቶ: AP እና BBC)
http://www.goolgule.com/egyptian-court-issues-death-sentence-verdict-for-529-people/

ለዜጎች ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ አፈናና እስራት ምላሽ አይሆንም! (ሰማያዊ ፓርቲ)

ከሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የወጣ የአቋም መግለጫ

የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት መጋቢት 14 ቀን 2006 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛ ዓመት አራተኛ መደበኛ ስብሰባው የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ በተገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት ላይ ፖሊስና ፍርድ ቤት በመተባበር የፈጸሙትን ሕገ መንግስት የጣሰ ተግባር፣ እንዲሁም ከአሜሪካ መንግስት በደረሳቸው ግብዣ መጋቢት 12 ቀን 2006 ዓም ምሽት ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ቦሌ አውሮፕላን ማረፈያ በተገኙት የፓርቲያችን ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ላይ ራሳቸውን ከህግ በላይ ያደረጉ የደህንነት ኋይሎች የፈጸሙትን አሳፋሪና ሕገ ወጥ ተግባር በመመርመር የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡Statement from Semayawi party of Ethiopia, regarding Nile issue.
1. የሴቶችን ቀን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ የተገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት በሩጫው ከተሳተፉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች የሚለዩት የነጻነትን ቀን ሊያከብሩ በተገኙበት ቦታ ስለ ነጻነት፣ስለ ፍትህ፣ስለዴሞክራሲ፣ስለ ሰብአዊ መብት ወዘተ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው በማሰማታቸው ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን በህገ መንግሥቱ አንቀጽ 29/2 «ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሀሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው» ተብሎ የተደነገገውን ከምንም ያልቆጠረውና ሕጉን ሳይሆን ጠመንጃውን ተማምኖ፣ የሙያውን ሥነ ምግባር ሳይሆን የአለቆቹን ትዕዛዝ አክብሮ እንደሚሰራ በተግባሩ ያረጋገጠው ፖሊስ እነዚህን የሰማያዊ ፓርቲ ሴት ወጣቶች አፍሶ ሲያስር አንዳችም ህጋዊ ምክንያት አልነበረውም፣ የፖሊስ ሕገ ወጥ ተግባር በዚህ ሳያቆም የታሰሩ የትግል አጋሮቻቸው የሚገኙበትን ቦታና ሁኔታ ለማወቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄዱ የፓርቲው አመራር አባላትንም አሰረ፡፡ ዋስትና ለማስከልከል አይደለም ለክስ የሚያበቃ ምንም ምክንያት ሳይኖረው ለፍ/ቤት ምርመራየን አልጨረስኩም የግዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ በማለት አባላቱ ለአስር ቀናት በጣቢያ እስር እንዲጉላሉ በማድረግ ሕግን ለማስከበር ሳይሆን የፖለቲከኞችን ፍላጎት ለማስፈጸም የቆመ መሆኑን በተግባር አረጋግጠ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ይህንን ሕገ መንግሥቱን በግልጽ የጣሰ የፖሊስ ተግባር በጽኑ እያወገዘ፣ፖሊስ የግለሰቦች ሥልጣን ጠባቂ ሳይሆን ሕግ አስከባሪ መሆኑን በተግባር እንዲያሳይ ይጠይቃል፡፡
2. የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 19/4 «የያዛቸው የፖሊስ መኮንን ወይም ህግ አስከባሪ በጊዜው ገደብ ፍርድ ቤት በማቅረብ የተያዙበትን ምክንያት ካላስረዳ ፍርድ ቤቱ የአካል ነጻነታቸውን እንዲያስከብርላቸው የመጠየቅ ሊጣስ የማይችል መብት አላቸው፡፡» ተብሎ የተደነገገውንእንዲያቀርቡ አዟል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምር ፍርድ ቤቱ ለህግ የበላይነት የሚሰራና በመተላለፍ ታሳሪዎቹን የዋስትና መብት ከልክሎ ለሁለት ግዜ ለፖሊስ የግዜ ቀጠሮ የፈቀደው ፍርድ ቤት፣ የእኔ ሥልጣን አይደለም መደበኛ ፍርድ ቤት አቅርቡዋቸው በማለት ካሰናበት በኋላ የምርመራ መዝገቡ ለክስ አይበቃም ተብሎ በአቃቤ ሕግ ውድቅ የተደረገበት ፖሊስ መልሶ እዛው ፍርድ ቤት ሲያቀርባቸው እያንዳንዳቸው 1300 ብርና የሰው ዋስ በጣምራ ለፍትህ መከበር የቆመ አለመሆኑን በተግባር ያረጋገጠበትን ይህን ተግባር እያወገዘ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 79/2 «በየትኛውም ደረጃ የሚገኝ የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግሥት አካል፣ከማንኛውም ባለሥልጣን ሆነ ከማንኛውም ሌላ ተጽዕኖ ነጻ ነው» እንዲሁም በአንቀጽ 79/3 ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በሙሉ ነጻነት ያከናውናሉ፣ከሕግ በስተቀር በሌላ ሁኔታ አይመሩም »ተብሎ የተደነገገው በተግባር እንዲገለጽ አጥብቆ ይጠይቃል፡፡
3. የፓርቲያችን ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ወደ አሜሪካ የሚያደርሳቸውን አስፈላጊ የጉዞ ሰነድ አሟልተው ሻንጣቸው አውሮፕላን ላይ ካስጫኑ በኋላ ፓስፖርታቸው በደህንንት ኋይሎች ተቀዶ ጉዞአቸው እንዲስተጓጎል ተደርጓል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ይህን ሕገ ወጥ ብቻ ሳይሆን እጅግ አሳፋሪ የሆነና የደህንነት ክፍሉን ብቻ ሳይሆን የአየር መንገዱንም ስም የሚያጎድፍ ተግባር በጽኑ እያወገዘ ድርጊቱን በፈጸሙት ማን አለብኝ ባዮች ላይ ከሕግ በላይ ሊሆኑ እንደማይችሉ የሚያሳይ ሕጋዊ ርምጃ አንዲወሰድ እንጠይቃለን፡፡ 
4. መንግሥት ለዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብት ጥያቄ እስራት አፈናና ማስፈራራት ምላሽ እንደማይሆን ከታሪክ በመማር ለዜጎች የመብት ጥያቄ ትክክለኛውን ምላሽ እንዲሰጥና ትግሉ ሰላማዊ፣ ዓላማው ሕዝባዊ ግቡ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እውን ማድረግ ከሆነው ሰማያዊ ፓርቲ ላይ የጥፋት እጁን እንዲያነሳ አጥበቀን እንጠይቃለን ፡፡
መጋቢት 14/2006 ዓም አዲስ አበባ
http://ecadforum.com/Amharic/archives/11523/

Monday, March 24, 2014

ኢህአዴግ ባደባባይ የወደቀውን ፈተና “በጓሮ” አለፈ

ግልጽነትና ተጠያቂነት ፈረዱ ወይስ ተፈረደባቸው?

short eiti eprdf


ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።
የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።
በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።
ማመልከቻው እንደገና እንዲታይና የቦርዱ የቀድሞ ውሳኔ እንዲገለብጥ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የቀድሞ የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ ትብብር ሚ/ር የሆኑት ክሌር ሾርት መሆናቸውን የድርጅቱ መግለጫው ይፋ አድርጓል። እኚህ ግለሰብ የአፍሪካ አምባገነኖችን በመደገፍ የሚታወቁ ሲሆን ይህ ከጥቅማቸው ጋር የተሳሰረው ግንኙነታቸው አሁንም ኢህአዴግን እንዲደግፉ እንዳደረጋቸው ይነገራል፡፡ እንዲሁም በሌሎች ኢህአዴግ ባቋቋማቸው ዓለምአቀፋዊነት ሽፋን በተላበሱ ድርጅቶች ውስጥ የአመራር አባል በመሆን ሚስ ሾርት እንደሚያገለግሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የእንግሊዝ ፓርላማ አባል በነበሩበት ወቅትም ያላወጡትን ወጪ አውጥቻለሁ በማለት በብዙ ሺዎች የሚገመት ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ መሆናቸው በወቅቱ ዴይሊ ቴሌግራፍ ባወጣው መረጃ አጋልጦ ነበር፡፡ የተወሰነውን ገንዘብ የመለሱ ቢሆንም ጋዜጣው በወቅቱ ያወጣው መረጃ ግለሰቧ የሕዝብን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው የተጠቀሙ “ሙሰኛ” መሆናቸውን ያስረዳል፡፡
clare
ክሌር ሾርት
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ከሆነ ባለፈው ረቡዕ ኦስሎ፤ ኖርዌይ ላይ ውሳኔው በተላለፈበት ወቅት ሚስ ሾርት በግልጽ የኢህአዴግ ደጋፊ በመሆን ተጽዕኖ በማድረግ ወደ ውሳኔ እንዲደረስ ግፊት አድርገዋል፡፡ ግለሰቧ ባላቸው ኃላፊነት በመጠቀም (የEITI የቦርድ ኃላፊ ናቸው) እንዲህ ዓይነቱ ግልጽና ወገናዊነት የታየበት ድጋፍ በማድረግ ከድርጅቱ አሠራር ውጪ ውሳኔ እንዲሰጥ ማድረጋቸው ለወደፊት በሚቀርቡ ማመልከቻዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የአሠራር ችግር እንደሚያስከትል ካሁኑ እየተጠቆመ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ከማዕድን ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ ማህበራዊ ቀውስ የደረሰባቸው አካባቢዎች እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት አካባቢዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ባልጸዳ የሽያጭ ሂደት ሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ የገዙት ሻኪሶ የወርቅ ማዕድን በህዝብ ላይ እያደረሰ ችግር የሚዘገንን ነው። በየጊዜው ግልጽ ባልሆነ የማስፋፊያ ውል የሚፈናቀሉና ከፋብሪካው በሚወጣው ዝቃጭ ለከፍተኛ ብክለት የተጋለጡ ዜጎች ድምጻቸውን ሲያሰሙ መታሰራቸው፣ መገረፋቸው፣ ለይስሙላ በተቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የተፈረደባቸው እንዳሉ ታዛቢዎች ያስታውሳሉ።
በጋምቤላ ኢንቨስትመንት ህዝብን እየበላ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች “ኢንቨስትመንት በከፍተኛ ደረጃ የሚደገፍና የሚበረታታ ተግባር ቢሆንም፣ ኢህአዴግ ፍትሃዊ በሆነ ደረጃ መጠቀም፣ ማስተዳደር፣ መምራትና ኢንቨስትመንቱን ህዝብ “የኔ” ብሎ በመቀበል እንክብካቤ እንዲያደርግ የሚያስችል ስርዓት አለማበጀቱን እንደ ዋንኛ ችግር ያነሳሉ። ኢህአዴግን ያዘጋጀው ህወሃት በራሱ ሰዎች አማካይነት ከውጪ ሰዎች ጋር እየተሻረከ ለህዝብ ጥቅም ሊውል የሚገባውን ሃብት ወደ ውስን ቋት እንደሚያግዝ የሚገልጹት እነዚሁ ክፍሎች” ይህ ዓለም የሚያውቀውን፣ ራሳቸው ህወሃቶችም የማይክዱትን እውነት ነው ብለዋል። ዜጎች የአገራቸው ሃብት ተጠቃሚ ከመሆን ይልቅ አካባቢያቸው ባደላቸው የተፈጥሮ ሃብት ሳቢያ መከራ ሲደርስባቸው፣ ሲሰቃዩ፣ ሲገረፉና፣ ሲገደሉ ማየት በተለመደባት ኢትዮጵያ ውስጥ ለኢህአዴግ የማይገባውን ካባ መደረብ ውሎ አድሮ የሚጋለጥ ክፉ ተግባር እንደሆነም አመልክተዋል።
አነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና ኢህአዴግ “ልማታዊ” የሚላቸው ኢንቨስተሮች ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሚመደብ መዋዕለ ንዋይ የሚያፈሱ ባለሃብቶች ኢንቨስት የሚያደርጉበትን አገር ለመምረጥ የመጀመሪያው መለያቸው የEITI ድረገጽ የአባል አገራት ዝርዝር እንደሆነ ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ኢህአዴግም አስፈላጊውን የምዝገባና የማመልከቻ መስፈርት በማሟላት የተቋሙን እውቅና የጠየቀው በድርጅቱ ድረገጽ ላይ ለመመዝገብ ነበር። የሁለት ጊዜ ሙከራው ቢከሽፋም በመጨረሻ ተሳክቶለታል። ስኬቱንና የስኬቱን መንገድ፣ በተለይም የዳይሬክተሯ ክሌር ሾርት ጉዳይና የተዘጋውን ፋይል በማንሳት ውሳኔው የተገለበጠበት አካሄድ ኦስሎ በሚገኘው ሃያ የቦርድ አባላት ባሉበት ተቋም ውስጥም ግራ ያጋባቸው እንዳሉ መረጃዎች አሉ።
ኢህአዴግ አጓድለሃል ተብሎ የሚከሰስባቸውን የዴሞክራሲ ግባቶችና የሰው ልጆች የተፈጥሮ መብቶች፣ አንዲሆም አፋኝ የተባሉትን ህጎች አጠናክሮ ተግባር ላይ ባዋለበት ሁኔታ፣ የዚሁ የአፈናው ሰለባዎች በተለያዩ ማጎሪያዎች ውስጥ ሆነው ድምጻቸውን በሚያስተጋቡበት ወቅት፣ EITI ከተቋቋመበት ዓላማና “መሰረቴ” ከሚለው የግልጽነትና ተጠያቂነት መርህ በተጻራሪ ግልጽነትና ተጠያቂነት በጎደለው መልኩ ለኢህአዴግ የደረበው ብሉኮ ጉዳይ እየተመረመረ አንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ጉዳዩን የሚከታተሉ “ግልጽነትና ተጠያቂነት በኦስሎ ተፈረደባቸው” ሲሉ ምጸት ሰጥተዋል፤ የክሌር ሾርትንም አካሄድ በEITI የህወሃት/ኢህአዴግ ተወካይ በማለት ተችተዋል። ይህንኑ ጉዳይ እመልክቶ ከሳምንት በፊት ለሪፖርተር አጭር መልስ የሰጡት የማዕድን ሚኒስትሩ EITI ውሳኔውን ያነሳል የሚል ጥርጣሬ እንዳለባቸው የሚያሳብቅባቸው መልስ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ዳያስፖራው እንደሚገባው አለመንቀሳቀሱ እንደ ሽንፈትና አቅጣጫ መሳት እንደሚቆጠር ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡ ዳያስፖራው ከጥቃቅንና ስሜታዊ ጉዳዮች በማለፍ በከፍተኛና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የማድረግ አመለካከቱን ማስፋት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ አለበለዚያ ኢህአዴግ እንደዚህ ዓይነቱን አጋጣሚ በመጠቀም የራሱን ገጽታ በዓለምአቀፍ መድረኮች እየወለወለ በማቅረብ የሥልጣን ዘመኑን እንደሚያራዝም ጠቁመዋል፡፡
http://www.goolgule.com/eiti-clare-short-and-eprdf/