FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Friday, July 18, 2014

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ እርዳታ ፖሊሲ ተግባራዊነት እንዲፈተሽ ታዘዘ

dfid


የእንግሊዝ የባሕር ማዶ ትብብር ኤጀንሲ ለኢትዮጵያ ድጋፍ ሲሰጥ ከራሱ የሰብዓዊ መብቶች ፖሊሲዎች ጋር በተጣጣመ መልክ መሆንና አለመሆኑ እንዲፈተሽ አንድ የእንግሊዝ ፍርድ ቤት መወሰኑን የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂዩማን ራይትስ ዋች አድንቋል፡፡
ሌስሊ ሌፍኮው - የሂዩማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ መርኃግብር ምክትል ዳይሬክተር
ሌስሊ ሌፍኮው – የሂዩማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ መርኃግብር ምክትል ዳይሬክተር
የእንግሊዝ የባሕር ማዶ ትብብር ኤጀንሲ ለኢትዮጵያ ድጋፍ ሲሰጥ ከራሱ የሰብዓዊ መብቶች ፖሊሲዎች ጋር በተጣጣመ መልክ መሆንና አለመሆኑ እንዲፈተሽ አንድ የእንግሊዝ ፍርድ ቤት መወሰኑን የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂዩማን ራይትስ ዋች አድንቋል፡፡
የእንግሊዝ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትናንት፤ ሐምሌ 7/2006 ዓ.ም ባሣለፈው ውሣኔ የዓለም አቀፍ ትብብር መሥሪያ ቤቱ ለኢትዮጵያ ድጋፍ ሲሰጥ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በበቂ ሁኔታ አይፈትሽም ሲባል የቀረበበት ክሥ ሙሉ የፍርድ ቤት ምርመራ የሚያስፈልገው ነው ብሏል፡፡
የሂዩማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ መርኃግብር ምክትል ዳይሬክተር ሌስሊ ሌፍኮው ለዝግጅት ክፍላችን በሰጡት ቃል ይህ የእንግሊዝ ፍርድ ቤት ውሣኔ ገና የመጀመሪያ እርምጃና ሊደነቅ የሚገባው ነው ብለዋል፡፡
በጋምቤላ፣ በሶማሌ ክልልና በደቡብ ኦሞ እየተፈፀሙ ናቸው ያሏቸው አድራጎቶችም የቅርብ ፍተሻ የሚያስፈልጋቸው መሆናቸውን የጠቆሙት ሚስ ሌፍኮው ልማት ከሰብዓዊ መብቶች መከበር ጋር አብሮ መታየት እንደሚገባቸው ለጋሾች ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል ሚስ ሌፍኮው፡፡
መሠረታዊ የልማት ድጋፍ ይቁም የሚል አቋም ሂዩማን ራይትስ ዋች እንደሌለው ሌፍኮው አመልክተው የእንግሊዝ መንግሥት ለኢትዮጵያ በሚሰጠው እርዳታ ሰብዓዊ መብቶችን የሚረግጡ ፕሮጀክቶችን የሚያስፈፅሙ ባለሥልጣናት ደመወዝ እንደሚከፈል አመልክተዋል፡፡ጋምቤላ
በሌላ በኩል ደግሞ በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ አስታያየት እንማይሰጥ የተናገረው የእንግሊዝ የዓለምአቀፍ ልማት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የሠፈራ መርኃግብር የገንዘብ ድጋፍ ሰጥታ እንደማታውቅ ገልጿል፡፡
“መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለመጠበቅ የምንሰጠው ድጋፍ የሚውለው እንደ ጤናጥበቃ፣ ትምህርት ቤቶች እና ንፁህ ውኃን ለመሳሰሉ አገልግሎቶች ነው” ብሏል መሥሪያ ቤቱ በኢሜል በሰጠን ምላሽ፡፡
የኢትዮጵያ ባለሥልጣናትም የሠፈራ መርኃ ግብሩ የሚካሄደው በሠፋሪዎቹ ፍቃደኝነትና በግልፅነት መሆኑን ይናገራሉ፡፡
ሰዎች በቀልን በመፍራት ምክንያት አስተያየቶቻቸውን ለመግለፅ እንደማይፈልጉና መንግሥቱ በመገናኛ ብዙኃን ላይ በተከታታይ አፈና እየፈፀመ መሆኑን የሂዩማን ራይትስ ዋች መግለጫ አመልክቷል፡፡
እንግሊዝ ለኢትዮጵያ በየዓመቱ የ300 ሚሊየን ፓውንድ እርዳታ እንደምትሰጥ ሂዩማን ራይትስ ዋች የጠቀሰ ሲሆን ሌፍኮው በሰጡት ቃል “የሃገሪቱ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ግን በተከታታይ እያሽቆለቆለ ነው” ብለዋል፡፡
“የእንግሊዝ የውጭ ተራድዖ መሥሪያ ቤት የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ግድ የሚሰጠው ከሆነ በመንደር ምሥረታ መርኃግብርና በሌሎችም አሠራሮች የሚፈፀሙ ብርቱ የመብቶች ጥሰቶችን ለማስቆም የሚያስችል ጫና ሊፈጥር በሚችል ሁኔታ የክትትልና ግምገማ ሥርዓቱን መልሶ መፈተሽና ሙሉ በሙሉ ማስተካከል ይኖርበታል” ሲሉ ሌስሊ ሌፍኮው አሳስበዋል፡፡
ለተጨማሪና ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል እዚህ ላይ በመጫን ያዳምጡ:: (ምንጭ: የ አሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ)
የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂዩማን ራይትስ ዋች ያወጣው ዘገባ እንዲህ ይነበባል::
Ruling Permits Review of Development Agency’s Compliance; July 14, 2014
(London) – A UK High Court ruling allowing judicial review of the UK aid agency’s compliance with its own human rights policies in Ethiopia is an important step toward greater accountability in development assistance.
In its decision of July 14, 2014, the High Court ruled that allegations that the UK Department for International Development (DFID) did not adequately assess evidence of human rights violations in Ethiopia deserve a full judicial review.
“The UK high court ruling is just a first step, but it should be a wake-up call for the government and other donors that they need rigorous monitoring to make sure their development programs are upholding their commitments to human rights,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “UK development aid to Ethiopia can help reduce poverty, but serious rights abuses should never be ignored.”
The case involves Mr. O (not his real name), a farmer from Gambella in western Ethiopia, who alleges that DFID violated its own human rights policy by failing to properly investigate and respond to human rights violations linked to an Ethiopian government resettlement program known as “villagization.” Mr. O is now a refugee in a neighboring country.
Human Rights Watch has documented serious human rights violations in connection with the first year of the villagization program in Gambella in 2011 and in other regions of Ethiopia in recent years.
A January 2012 Human Rights Watch report based on more than 100 interviews with Gambella residents, including site visits to 16 villages, concluded that villagization had been marked by forced displacement, arbitrary detentions, mistreatment, and inadequate consultation, and that villagers had not been compensated for their losses in the relocation process.
People resettled in new villages often found the land infertile and frequently had to clear the land and build their own huts under military supervision. Services they had been promised, such as schools, clinics, and water pumps, were not in place when they arrived. In many cases villagers had to abandon their crops, and pledges of food aid in the new villages never materialized.
The UK, along with the World Bank and other donors, fund a nationwide development program in Ethiopia called the Promotion of Basic Services program (PBS). The program started after the UK and other donors cut direct budget support to Ethiopia after the country’s controversial 2005 elections.
The PBS program is intended to improve access to education, health care, and other services by providing block grants to regional governments. Donors do not directly fund the villagization program, but through PBS, donors pay a portion of the salaries of government officials who are carrying out the villagization policy.
The UK development agency’s monitoring systems and its response to these serious allegations of abuse have been inadequate and complacent, Human Rights Watch said. While the agency and other donors to the Promotion of Basic Services program have visited Gambella and conducted assessments, villagers told Human Rights Watch that government officials sometimes visited communities in Gambella in advance of donor visits to warn them not to voice complaints over villagization, or threatened them after the visits. The result has been that local people were reluctant to speak out for fear of reprisals.
The UK development agency has apparently made little or no effort to interview villagers from Gambella who have fled the abuses and are now refugees in neighboring countries, where they can speak about their experiences in a more secure environment. The Ethiopian government’s increasing repression of independent media and human rights reporting, and denials of any serious human rights violations, have had a profoundly chilling effect on freedom of speech among rural villagers.
“The UK is providing more than £300 million a year in aid to Ethiopia while the country’s human rights record is steadily deteriorating,” Lefkow said. “If DFID is serious about supporting rights-respecting development, it needs to overhaul its monitoring processes and use its influence and the UK’s to press for an end to serious rights abuses in the villagization program – and elsewhere.”
http://www.goolgule.com/british-high-court-ruling-to-review-dfid-policy-implementation-when-giving-aid-to-ethiopia/

ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ ፍ/ቤት ሳይቀርቡ የምርመራ መዝገቡ መዘጋቱ ሕገወጥና አደገኛ መሆኑ ተገለጸ

"አሁን ታስረው የሚገኙበት ሁኔታ ሕገወጥና አደገኛ ነው" ጠበቃ አመሐ መኮንን

zone9 free


በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በክስ ላይ የሚገኙት ሦስት ጋዜጠኞችና ስድስት ጦማርያን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ፖሊስ ‹‹ምርመራዬን ስለጨረስኩ መዝገቡ ይዘጋልኝ›› በማለት መዝገቡ እንዲዘጋ ማድረጉ ሕጉን ያልተከተለና አደገኛ መሆኑን ጠበቃቸው አስታወቁ፡፡
ተጠርጣሪ ጋዜጠኞች ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሳዬና ጦማሪያንና የሕግ መምህር ዘለዓለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃኔ ሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የሚቀርቡበት ዕለት ነበር፡፡ እንደወትሮው ሁሉ የተጠርጣሪዎች ቤተሰቦች፣ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ጋዜጠኞች፣ ጓደኞቻቸውና የተለያዩ የችሎት ታዳሚዎች በጠዋት ማልደው በፍርድ ቤት ግቢ የተገኙ ቢሆንም፣ እስከ ቀኑ 5፡30 ሰዓት ድረስ ፖሊስም ሆነ ተጠርጣሪዎቹ ወደ ችሎቱ አልመጡም፡፡ ከ5፡30 ሰዓት በኋላ ሌሎች ፍርድ ቤት የሚቀርቡ ተጠርጣሪዎቹና ፖሊስ ችሎት ቆይተው ሲወጡ፣ የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ አመሐ መኮንን፣ ደንበኞቻቸው ፍርድ ቤት መቅረብ አለመቅረባቸውን ለማጣራት የዕለቱን ተረኛ ዳኛ ለማነጋገር ገቡ፡፡ ጠበቃው ስለደንበኞቻቸው ፍርድ ቤቱን ሲጠይቁ፣ ፖሊስ ምርመራውን መጨረሱን በማሳወቅ መዝገቡ እንዲዘጋለት ጠይቆ መዘጋቱን ሲያስረዳቸው፣ ‹‹እንዴትና በምን ሁኔታ?›› የሚል ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ከመዘጋቱ ውጪ ምንም ምላሽ ሊያገኙ አለመቻላቸውን ተናግረዋል፡፡
እስረኛ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ የምርመራ መዝገቡ ሊዘጋ እንደማይችል የሚናገሩት ጠበቃ አመሐ፣ ተጠርጣሪዎቹ ከሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር ላይ መሆናቸው፣ በሕግ አግባብ በፍርድ ቤት ምንም ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ በመሆኑ ድርጊቱ ሕገወጥና አደገኛ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ፖሊስ ምርመራውን ካጠናቀቀ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ይዞ በመቅረብ ለፍርድ ቤቱ ማስረዳትና ክስ እስከሚመሠረትባቸው ድረስ በዋስ እንዲቆዩ ወይም የሕግ ሥርዓቱ በሚፈቅደው መሠረት ስለሚቆዩበት ሁኔታ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ መስጠት እንደነበረበት አስረድተዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ባልሰጠበት ሁኔታ ተጠርጣሪዎቹ ባሁኑ ወቅት የት እንዳሉ እንደማይታወቅ የሚናገሩት ጠበቃው፣ በወንጀል ሕጉና በሕገ መንግሥቱ በተጠሰው አካልን ነፃ የማውጣት መብት (ሐቢየስ ኮርፐስ) ክስ ሊመሠርቱ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡
በሌላ የምርመራ መዝገብ የተካተቱት ጦማሪያን ማህሌት ፋንታሁን፣ አቤል ዋበላና በፈቃዱ ኃይሉ ደግሞ ፍርድ ቤት መቅረብ የነበረባቸው ሐምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. የነበረ ቢሆንም፣ ተጠርጣሪዎቹም ሆኑ መርማሪ ፖሊስ ሳይቀርቡ መቅረታቸውን ጠበቃው ጠቁመዋል፡፡
ዘጠኙም ተጠርጣሪዎች ‹‹የመብት ተሟጋች ነን›› ከሚሉ የውጭ ኃይሎች ጋር በሙሉ ሐሳብና ገንዘብ በመስማማት ሕዝብን የማተራመስ፣ አገርንና መንግሥትን የማፍረስ ዘገባ በኢንተርኔትና በተለያዩ ድረ ገጾች ያልሆነ መረጃ ሲያስተላልፉ ተገኝተዋል በሚል ፖሊስ ሚያዝያ 17 እና 18 ቀን 2006 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር እንዳዋላቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ለሁለት ጊዜ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቆ ከተፈቀደለት በኋላ፣ በሦስተኛው የፍርድ ቤት ቀጠሮ የተጠርጣሪዎቹ ጉዳይ ውስብስብና ድርጊቱም የሽብርተኝነት ድርጊት መሆኑን በመጥቀስ፣ ለተጨማሪ ምርመራ 28 ቀን እንዲፈቀድለት የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉን በመጥቀስ ተፈቅዶለት መመርመር ላይ መሆኑን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ 78 ቀናት ሞልቷቸዋል፡፡(ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር ጋዜጣ)

በጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ ላይ የተከፈተው የጊዜ ቀጠሮ ፋይል ተዘጋ

“ደንበኞቼ አሁን ያሉበት ሁኔታ ሕገ-ወጥ ነው” ጠበቃ አመሃ መኮንን
ፖሊስ በሽብር ወንጀል ጠርጥሮ በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ፤ በማኅበራዊ ድረ-ገጾች መረጃዎችን ሲለዋወጡና በውጪ ሀገራት ከሚገኙ ተቋማት ጋር ስልጠና ወስደው፤ ህዝባዊ አመጽ ለመቀስቀስ የገንዘብ ድጋፍ አግኝተው፤ በሕጋዊ መንገድ ስልጣን የጨበጠውን መንግስት በሕገ-ወጥ መንገድ ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ በሚል ከሁለት ወራት በላይ አስሮ በማዕከላዊ ምርመራ ላይ የቆዩት ዘጠኙ ጋዜጠኞችና የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን በፖሊስ ተከፍቶባቸው የነበረው የጊዜ ቀጠሮ ፋይል ተዘግቶ፤ ወደ ዐቃቤ ሕግ መመራቱን በድንገት ስለመስማታቸው የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አመሃ መኮንን አስታወቁ።zone9 ers
ባሳለፍነው ቅዳሜ እና ሰኞ (ሐምሌ 5 እና 7 ቀን 2006 ዓ.ም) በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት፤ በሁለቱ ቀናት ተለዋጭ ቀጠሮ የነበራቸው ዘጠኙ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ባልቀረቡበት፤ የአያያዝ ሁኔታቸውን በግልፅ ለችሎቱ ባላስረዱበትና የዋስትና መብታቸውን ጠይቀው ምላሽ ባልተሰጠበት አኳሃን ጠበቃቸው ሲቀርቡ ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮ ፋይሉን ስለመዝጋቱና በቀጣይ ጉዳዩ ለፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ደርሶ ክስ ሊመሠረትባቸው መሆኑን ከችሎት መስማታቸውን የሚናገሩት ጠበቃ አመሃ መኮንን፤ በፍርድ ቤቱ ፋይሉ የተዘጋበትን ሁኔታ በተመለከተ “የተለመደ አሠራር ነው” የሚል ምላሽ ማግኘታቸውን ያስረዳሉ። ጠበቃው ሒደቱን ስርዓቱን ያልተከተለና የደንበኞቻችንንም ሕጋዊ መብት የጣሰ ነው ሲሉ ይናገራሉ። በተለይም በሰኞው ዕለት (ሐምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም) ቀጠሮ በፍርድ ቤት ግቢ ውስጥ ቀደም በማለት ተገኝተው እንደነበር ያስታወሱት ጠበቃው፤ ሦስቱም ተከሳሾች ማለትም በዕለቱ የተቀጠሩት ማህሌት ፋንታሁን፣ በፍቃዱ ኃይሉና አቤል ዋበላ ባልቀረቡበት፤ እንዲሁም አንድም የመርማሪ ቡድኑ አባል ባልተገኘበት ከመዝገቡ ጋር ተያያዞ በቀረበ ወረቀት አማካኝነት ብቻ መዝገቡ መዘጋቱንና ወደመደበኛ ክስ ለመግባት ዐቃቤ ሕግ ክስ እስኪመሰረት እየተጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል።
መርማሪ ቡድኑ መዝገቡን አጠናቅሮ ከቀረበለት የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ በቀጣዮቹ አስራ አምስት ቀናት ውስጥ ክሱን መስርቶ በፍርድ ቤት መቅረብ እንደሚኖርበት የአሠራር ሂደት መኖሩን የጠቆሙት ጠበቃ አመሃ መኮንን፤ ደንበኞቻቸው መቼና የት እንደሚቀርቡ አሁን ድረስ አለማወቃቸውን አስረድተዋል። ደንበኞቼን በሙሉ ማግኘት አልቻልኩም። ለዚህም እስረኞቹን ለመጐብኘት ከዕረቡና ከአርብ ቀን ውጪ ክልክል መሆኑና በአንድ ቀን አንድ ሰው አንድ ደንበኛን ብቻ የማግኘት ገደብ መኖሩን እንደመሰናክል በመጥቀስ አሠራሩ ችግር እንዳለበትም አክለው ገልፀዋል።
“ደንበኞቼ አሁን ያሉበት ሁኔታ ሕገ-ወጥ ነው” የሚሉት ጠበቃው፤ ለዚህም የጊዜ ቀጠሮውን ሲሰማ የነበረው ፍርድ ቤት ታስረው ይቆዩ የሚል ትዕዛዝን ባልሰጠበት፤ አልያም ክስ ተመስርቶባቸው ክሱን የሚሰማው ፍርድ ቤት በእስር ሆነው ጉዳያቸውን ይከታተሉ ባላለበት ሁኔታ ውስጥ ከቅዳሜው 4 ሰዓት እና ከሰኞው 8 ስዓት ጀምሮ ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ ታስረው የሚቆዩበት ሁኔታ ሕጋዊ መሠረት የለውም” ሲሉ አስረድተዋል። ከዚህ ቀጣይ እርምጃቸው የሚሆነው አካልን ነፃ የማውጣት ክስ በመመስረት ደንበኞቻችን ነፃ እንዲሆኑ ለማስቻል እየተዘጋጀን ነው ብለዋል። (አሸናፊ ደምሴ፤ ሰንደቅ ጋዜጣ)
http://www.goolgule.com/the-case-of-zone9ers-and-journalists/