FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Friday, October 31, 2014

“ይህ አገዛዝ በቃው! አንፈልገውም! 27 ዓመት + 1 አንቀበልም!”

ቡርኪናፋሶ ከአምባገነን ወደ አምባገነን?

burkina-faso-1


ቡርኪናፋሶን ያለገደብ ሲመሩ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ ለተጨማሪ ዓመታት ሥልጣናቸውን ለማራዘም ያደረጉት ሙከራ በመክሸፉ ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ ገለጹ፤ ለአንድ ዓመት የመሸጋገሪያ መንግሥት ተመስርቶ ምርጫ እስከሚደረግ በሥልጣን እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡ ሕዝቡና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ግን ይህንን የሚቀበሉበት ትከሻ እንደሌላቸውና የኮምፓዎሬ አገዛዝ አሁኑኑ መውረድ እንዳለበት በተቃውሟቸው እየገለጹ ነው፡፡ ከ27ዓመት አምባገነናዊ ሥርዓት በኋላ ቡርኪናፋሶ ወደ ሌላ አምባገነናዊ ሥርዓት ልትሄድ እንደምትች ተጠቆመ፡፡
በቀድሞው ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራ ዘመን የመንግሥት ባለሥልጣንና የሳንካራ ወዳጅ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ፤ ቶማስ ሳንካራ ባልታወቀ ሁኔታ በመፈንቅለ መንግሥት ከተገደሉ ከዛሬ 27ዓመት ጀምሮ ቡርኪናፋሶን መግዛት ጀመሩ፡፡ መፈንቅለ መንግሥቱን በመምራት የተሳተፉት ኮምፓዎሬ የሳንካራን መገደል በወቅቱ “ድንገተኛ” በማለት ከመጥቀስ በስተቀር ምርመራ እንዲካሄድ አላዘዙም፤ ምስጢሩም እንዳይወጣ ተደርጎ ቆይቷል፡፡
ቶማስ ሳንካራን ከሥልጣን ካስወገዱ በኋላ ለሦስት ዓስርተ ዓመታት ያህል የዘለቀውን አገዛዛቸውን የጀመሩት ኮምፓዎሬ እኤአ በ1990ዎቹ በተደጋጋሚ የተመረጡት ሲሆን የአገሪቱ ሕገመንግሥት ከተሻሻለ በኋላ በሁለት ሺዎቹም ሁለት ጊዜ ተመርጠዋል፡፡
burkina-faso-blaise1
ብሌዝ ኮምፓዎሬ
በአገዛዝ በቆዩበት ዘመን ሁሉ የአውሮጳውያንና የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሥልጣናቸው ሳይደፈር በአምባገነንነት ለመቆየት ችለዋል፡፡ አክራሪ እስላማዊነትን እዋጋለሁ በማለት የአሜሪካ ወዳጅነታቸውን ያጠናከሩት ኮምፓዎሬ በላይቤሪያና ሴራሊዮን እጅግ አስከፊ ጭፍጨፋ ያካሄዱትን እና በአሁኑ ወቅት 50ዓመት እስራት የተበየነባቸው የቀድሞው የላይቤሪያ መሪ ቻርልስ ቴለር የቅርብ ወዳጅ ነበሩ፡፡ ሳንካራን ለመገልበጥና ለመግደል የቴይለር ጦር እንደተሳተፈና በምላሹ ኮምፓዎሬለቴይለር ወደ ሥልጣን መምጣትና ከዚያ ጋር ተያይዞ ለተፈጸመው ወንጀል ተባባሪ ናቸው በማለት ሁኔታዎችን የሚያገናኙ ወገኖች አሉ፡፡
በአገራቸው የሚነሱ ተቃውሞዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድና በምዕራባውያን ድጋፍ ሲያከሽፉ የኖሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ በአካባቢው አገራት ዘንድ የሰላም ዘንባባ አቅራቢ፣ አስታራቂ፣ አስማሚ፣ ሸምጋይ፣ … ሆነው ምስላቸውን እና ማንነታቸውን ሲገነቡ ቆይተዋል፡፡ በአምባገነንነት በቆዩባቸው ዓመታት በሙስና በተለይም ከአልማዝ ሽያጭ ከሚገኘው ገንዘብ ያላቸው ተሳታፊነት ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል፡፡
በቀጣዩ የአውሮጳውያን ዓመት 2015 ሥልጣናቸው የሚያበቃው ኮምፓዎሬ “ደህና ሁኑ” ብለው ለመሄድ የተዘጋጁ አልነበሩም፡፡ በመሆኑም የአገሪቱን ሕገመንግሥት በማሻሻል እንደገና ለመመረጥ ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ፡፤ ፓርላማቸውን አሰብስበው ሕገመንግሥቱ እንዲሻሻል በማድረግ ሂደት ላይ እያሉ ሕዝቡ “በቃኝ” አለ፡፡
የ27 ዓመታት አገዛዝ የመረራቸው ዜጎች ሐሙስ ዕለት ፓርላማውን ጥሰው በመግባት ድምጽ እንዳይሰጥ ከማድረግ አልፈው በእሣት አጋዩት፡፡ ተቃውሞ በየቦታው ፈነዳ፡፡ ቡርኪናፋሶ መጋየት ጀመረች፡፡ ሁኔታው ያላማራቸው ኮምፓዎሬ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጁ፡፤ ሰሚ ግን አላገኙም፡፡ ሕዝቡ “ይህንን አገዛዝ አንፈልግም፣ በቃን” አለ፡፡ ሕዝባዊ ዓመጽ በየቦታው ተቀጣጠለ፡፡ በተለይ ዋና ከተማዋ ዖጋዱጉ የዓመጹ ዋና ማዕከል ሆነች፡፡
መንግሥት ሥራ አቆመ፣ ፓርላማውም ፈረሰ፡፡ ድህነት ያስመረራቸው ዜጎች አሁንም ተቃውሟቸውን ቀጥሉ፡፡ ኮምፓዎሬን ማየትም ሆነ መስማት በጭራሽ አይፈልጉም፡፡ ወታደሮች በየአካባቢው ሥነሥርዓት ለማስጠበቅ እየጣሩ ቢሆንም ዓመጹ ግን ቀጥሏል፡፡ ንብረት እየወደመ ነው፤ ባንኮችምተዘርፈዋል፡፡
ዛሬ አርብ ዳግም ለመመረጥ ሲመኙ የነበሩት ኮምፓዎሬ ሥልጣን በቃኝ፤ መንግሥት ፈርሷል፤ ፓርላማውም አይሰራም፤ ከሥልጣኔ እለቃለሁ ነገር ግን በ2015 ምርጫ እስከሚካሄድ የሽግግር አስተዳደር ተመስርቶ ሁሉም ነገር መረጋጋት አለበት በማለት አስቀድሞ በተቀዳ የቴሌቪዥን መልዕክት ቢያስተላልፉም ሰቆቃ የመረራቸው፣ ኑሮ ያቃጠላቸው፣ ነጻነት የጠማቸው ዜጎች ግን አሁንም “አንሰማም” ብለው ተቃውሟቸውን በመቀጠል ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቀዋል፡፡
ሰላሳ አራት የሚሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ፕሬዚዳንቱ ያቀረቡትን ቅደመ ሁኔታ አንቀበልም ብለዋል፡፡ ለኮምፓዎሬ ምላሽ ሲሰጡም “አንድ የምንቀበለው አጭርና ግልጽ ቅድመ ሁኔታ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ብሌዝ ኮምፓዎሬ ከሥልጣን እንዲለቁ ነው” በማለት ተናግረዋል፡፡
ጦሩ ሥልጣኑን የተረከበ እንደሆነ እየተጠቆመ ሲሆን አገሪቱን በበቂ ሁኔታ ለማረጋጋት እንዳልቻለ ከዋና ከተማዋ የሚመጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡ የሕዝቡ ዓመጽም ወደ ሌሎች ከተሞች እየተዛመተ መሆኑን ከተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች እየተሰማ ነው፡፡
burkina generalsበአንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ከአረብ ጸደይ ቀጥሎ የተጀመረ “የአፍሪካ ጸደይ” ሊሆን ይችላል በማለት ግምት የሰጡበት የቡርኪናፋሶ ሕዝባዊ አመጽ ተመልሶ በአምባገነናዊ አገዛዝ እንዳይወድቅ ስጋት አላቸው፡፡ ለዚህም ጠንካራ ተቋማት መመሥረት አስፈላጊነትን ያሰምሩበታል፡፡ በተለይ ከአምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ሕዝባዊ ሥርዓት በሚደረግ ጉዞ በቅድሚያ የሚደረጉ መሰናዶዎች ሳይከናወኑ በጭፍን አምባገነኖችን ከሥልጣን እንዲወርዱ ማድረግ በበርካታ አገራት እንደተደረገው መልኩን የቀየረ አምባገነናዊ ሥርዓት ለመመሥረት እንደሚጋብዝ ይናገራሉ፡፡ ከዚህ አንጻር የሕዝብ ንቃተ ኅሊና መዳበር፣ የእርሰበርስ ውይይት መጀመር፣ የተቋማት መመሥረት፣ … ወሳኝነት ያላቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንደሆኑ ያሰምሩበታል፡፡
*********************
ይህንን ዘገባ ካጠናቀርን በኋላ ከቢቢሲ የተገኘው ዜና እንደሚያመለክተው ከሆነ ፕሬዚዳንቱ ሥልጣናቸውን ጥለው ከአገር እየወጡ እንደሆነ የጦሩጄኔራል ዖኖሬ ትራዖሬ በሕገመንግሥቱ መሰረት አገሪቷን እየመሩ እንደሆኑ አስታውቀዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱ ቦታ ባዶ እንደሆነና በ90 ቀናት ውስጥ ምርጫ እንዲካሄድ መነገሩን ቢቢሲ ጨምሮ ዘግቧል፡፡ ብሌዝ ኮምፓዎሬ አሁን ያሉበት ቦታ ባይታወቅም በአቅራቢያ ባለ አገር አቋርጠው ወደ አንድ አውሮፓ ምናልባትም ፈረንሳይ የስደት ህይወታቸውን መምራት ይጀምራሉ የሚል ግምት እንዳለ እየተነገረ ነው፡፡
http://www.goolgule.com/it-is-over-for-this-regime-burkinafaso/

አዲስ አበባ ውስጥ ሌሊት የሚለጠፉ ወረቀቶችን ተከትሎ ውጥረት ነግሷል

“መረጃ ለአንድ ለአምስት ማቀበል አለባችሁ” ፖሊስና ካድሬዎች

addis p


  • የበር መብራት ማጥፋት ክልክል ነው፤ በሕግ ያስቀጣል
  • “መውጫና መግቢያ ሰዓታችሁ መመዝገብ ይጀመራል ተብለናል” ነዋሪዎቹ
ከትናንት በስቲያ በጨርቆስ አካባቢ አንድ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ መገኘቱን እና ሌሊት ላይ በቦሌ አካባቢ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችን የሚያስተጋቡ ወረቀቶች በየግድግዳውና የኤሌክትሪክ ምሶሶ ላይ ተለጥፈው መገኘታቸውን ተከትሎ በከተማዋ ውጥረት መንገሱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
“አንድ የጨርቆስ አካባቢ ነዋሪ ተገድሎ መገኘቱን ተከትሎ ‹የጨርቆስ ወጣቶች› ተሰባስበው ይህን ድርጊት ይፈጽሙ ይሆናል ብለው በገመቱት ላይ ቁጣቸውን ገልጸው ነበር፡፡ በተለምዶ ካታንጋ ወደሚባል ስፍራ ሄደው ገዳዩን አውጡ ብለዋል፡፡ መኪኖችን ሰባብረዋል፡፡ ካታንጋ ምንም ፍንጭ ሲያጡ ወደ ፊላሚንጎ አምርተዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ፖሊስ የተወሰኑትን ይዟል፤ ያመለጡም አሉ፡፡ እስካሁንም ውጥረቱ አለ” ስትል አንዲት የአካባቢው ነዋሪ ለነገረ ኢትዮጵያ ተናግራለች፡፡
ቀደም ብሎ ተለጥፎ በተገኘው ወረቀትና በሟቹ ምክንያትም ፖሊስና የኢህአዴግ ካድሬዎች የተለያዩ ጫናዎችን በነዋሪዎች ላይ ማሳደር መጀመራቸው ታውቋል፡፡ “ለስድስት ወራት ችላ ብለውት የነበረው የአንድ ለአምስት አደረጃጀት ስብሰባ አሁን እንደገና ጀምረውታል፡፡ አደረጃጀቱ ስራውን ካቆመና ስብሰባ ካደረግን 6 ወራት አልፈውት ነበር፡፡ ከትላንት ጀምሮ ግን በግዳጅ ጀምረውታል” ሲሉ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
ምንጮች አክለው እንዳስታወቁት ነዋሪዎችን ፖሊስና ካድሬዎች በስብሰባ በመያዝ የተለያዩ የማሳመኛ ሰበቦችን እንደሚያነሱ ተገልጾአል፡፡ “ምርጫ ደርሷልና አብረን እንስራ፡፡ 97 የሆነውን ታውቃላችሁ፡፡ ያ እንዲሆን አንፈልግም፡፡ ስለሆነም ሙሉ ሌሊቱን በራችሁ ላይ መብራት ማብራት አለባችሁ፤ የተከራይ መታወቂያ ማየት አለባችሁ፡፡ እያንዳንዷን መረጃ ለፖሊስና ለአንድ ለአምስት አደረጃጀቱ ማቀበል አለባችሁ” እንዳሏቸውም ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በየስብሰባዎቹ በአብዛኛው የሚገኙት ሴቶች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ነዋሪዎች በግዳጅ በተፈጠሩት የአንድ ለአምስቱ አደረጃጀቶች መሪ ለመሆን የሚፈልግ አለመኖሩንም ምንጮች ተናግረዋል፡፡
“እያንዳንዱ ሰው የሚወጣ የሚገባበትን ሰዓት መመዝገብ ይጀመራል ተብለናል” የሚሉት ነዋሪዎቹ፣ “አከራዮች ተከራዮቻችሁ የሚገቡበትን ሰዓት ገደብ ማስቀመጥ አለባችሁ፤ የበር መብራቱንም ማጥፋት ክልክል ነው፡፡ ሌሊቱን ሙሉ መብራት ያላበራ ይቀጣል፤ ፍርድ ቤት ሁሉ ሊቀርብ ይችላል” ተብሎ በየስብሰባዎቹ እንደተነገራቸው የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጨምረው አስረድተዋል፡፡ (ምንጭ፡ ነገረ ኢትዮጵያ)
http://www.goolgule.com/tension-is-escalating-in-addis-citizens-self-surveillance-imposed/

“ተፌ!”

tefera w


ታጋይ፣ ከንቲባ፣ መከላከያ ሚ/ር፣ ምክትል ጠ/ሚ/ር፣ አቅም ገንቢ፣ አቅም ተገንቢ … ከዚህ ሁሉ አልፈው አሁን አቅማቸው ተገንብቶ የስፔስ (ሕዋ) ሳይንስ “አቅም ግንባታ” ለመሆን የበቁት ጡረተኛው ተፈራ ዋልዋ “የኢትዮጵያን የሕዋ (ስፔስ) ሳይንስ ሶሳይቲን” ገንብተው በሪፖርተር በኩል ብቅ ብለዋል፡፡
“አቅም ገንቢ ሚ/ር” በነበሩበት ወቅት “ሂድና ከአባዱላ ተማር የአንተ አቅም ግንባታ እንኳን አቅም ሊገነባ ያለውንም ሊያስቀጥል አልቻለም” ተብለው በአቶ መለስ የተገመገሙት አቶ ተፈራ አቅማቸው ተገንብቶ ለስፔስ መድረሱን “ባለራዕዩ መሪ” ሳያዩና ሪፖርተር ላይ ሳያነቡ መሰዋታቸው አቶ ተፈራን እጀ ሰባራ አድርጓቸዋል፡፡
የአላሙዲን “ወዳጅ” ሪፖርተር የአቶ ተፈራን አንደበት ገድቦት ነው እንጂ ተፈራ “ሼኸ፣ ዶ/ር፣ አቅም አስገንቢ … አላሙዲንን” ባነሱበት አንደበታቸው በግል ጄታቸው ገስግሰን ሁለተኛውን ሙት ዓመት “ነፍስ ይማር” በማለት አክብረን “በባለራዕዩ መሪያችን ስም በዚያውም ዛፍ ተክለን እና ፓርክ አቋቁመን እንዲሁም አንድ ፕላኔት በስማቸው አሰይመን” ተመልሰናል እንዳሉ ይገመታል – የሕዋው “አቅም ገንቢ” ተፌ! (ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®)
http://www.goolgule.com/tefera/

Thursday, October 23, 2014

የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ

"ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል" የቴሌኮም ዳይሬክተር

eth telecom


ኢትዮ ቴሌኮም ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የሞባይል ማስፋፊያ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ አገልግሎቱ አሁንም በሞባይል አገልግሎት ላይ የሚታየውን ችግር ሊቀርፍ ባለመቻሉ፣ በተለይ ሰሞኑን ከአገልግሎት ጥራት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው በተወሰኑ ቦታዎች እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ይላል፡፡
በተለይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማዋ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች፣ የሞባይል መቆራረጥና የጥሪ መስተጓጎል ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም ባለፉት አምስት ቀናት ግን ችግሩ ይበልጥ መባባሱን አመልክተዋል፡፡
ካለፈው ዓርብ ማምሻውን ጀምሮ በሞባይል ስልኮች ለመጠቀም ከፍተኛ ችግር እንዳጋጠማቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሞባይል ጥሪ ቅዳሜና እሑድም ተባብሶ መቀጠሉን ደንበኞች በምሬት ገልጸዋል፡፡ ከጥሪ አገልግሎትም በተጨማሪ በአጭር ጽሑፍ መልዕክትና የሒሳብ መጠየቂያና የቅድመ ክፍያ ካርዶችን ለመሙላት እንኳን አዳጋች ሆኖ ነበር፡፡
የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አብዱራሂም አህመድ  ሰሞኑን የባሰበትን የሞባይል አገልግሎት መስተጓጎልና መቆራረጥ አምነው፣ ‹‹በአሁኑ ጊዜ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
በተለይ በአራዳ ክፍለ ከተማ አካባቢ የኃይል መቆራረጥ በማጋጠሙ ኦሲኤስ (OCS) የተባለው ኃይል አስተላላፊ ሥራ በማቋረጡ ችግሩ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ እንደ እሳቸው ገለጻ ችግሩ የተስተዋለው የቅድመ ክፍያ አገልግሎት የሚሰጡ (Prepaid) የሞባይል መስመሮች ላይ ነበር፡፡
አቶ አብዱራሂም ይህንን ቢሉም፣ ጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ከማለዳ ጀምሮ የጥሪ ችግሩ በሞባይል ስልኮች ላይና በመደበኛ የስልክ አገልግሎቶች ላይ ተስተውሏል፡፡ በተመሳሳይም ችግሩ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በዱከም፣ በቢሾፍቱና በአጎራባች ከተሞች ጭምር መከሰቱን ደንበኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
‹‹ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል የማስፋፊያ ሥራዎችን አጠናቅቄያለሁ፤ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን ቀርፌዋለሁ ባለ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ችግሩ በድጋሚ ተከስቷል፡፡ አሁን ደግሞ እንደሚታየው ላለፉት አምስት ቀናት ያህል ጭራሽ ኔትወርኩ ሞቷል፡፡ ወይ አንድ ፊቱኑ ሞባይል የሚባለውን ነገር ቢተውት ይሻላል፤›› ሲል ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚጓዝ ታክሲ ላይ ሪፖርተር ያነጋገርነው ተሳፋሪ ገልጿል፡፡
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ተከናውኗል ያለውን የሞባይል ማስፋፊያ ሥራ ሙሉ ለሙሉ በቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ አማካይነት ማከናወኑንና የነበሩት የአገልግሎት ችግሮች መቀረፋቸውን ኢትዮ ቴሌኮም መግለጹ ይታወሳል፡፡ ከመደበኛው የሞባይል ማስፋፊያ በተጨማሪ ‹‹3G›› እና ‹‹4G›› የተባሉት አገልግሎቶች መጠናቀቃቸውንና ለተጠቃሚዎች ዝግጁ መሆናቸውም ጨምሮ አስታውቆ ነበር፡፡ የ‹‹3G›› አገልግሎት የተጀመረ ቢሆንም እስካሁን የ‹‹4G›› አገልግሎት ግን አልተጀመረም፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም ከቻይናዎቹ ሁዋዌ እና ዜድቲኢ ኩባንያዎች የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት በፊት ተፈራርሟል፡፡ እስካሁን ግን በስምምነቱ መሠረት የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ቢጀመርም፣ መላ አገሪቱን የሚያዳርሰው ግን አለመጀመሩ ይታወቃል፡፡
ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች እያንዳንቸው የ800 ሚሊዮን ዶላር ሥራ የተረከቡ ሲሆን፣ ዜድቲኢ የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ሙሉ በመሉ ለተቀናቃኙ ዜድቲኢ መሰጠቱ እንዳላስደሰተው እየተነገረ ነው፡፡ ረዥም ጊዜ የወሰደ ተጨማሪ ውይይት ከመንግሥት ጋር እያደረገ እንደነበር በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በዜድቲኢ ሥራ አለመጀመርና በአዲስ አበባ ተጠናቋል በተባለው ፕሮጀክት በመንግሥትና በኢትዮ ቴሌኮም ላይ የሕዝብ ጥያቄ እየተነሳ ነው፡፡
ባለፈው ዓመት ፓርላማው ጭምር በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ሲነሱበት መቆየቱም ይታወሳል፡፡ በተለይም ከመደበኛ ስብሰባዎች በተጨማሪ የመሠረተ ልማት፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የድርጅቱን ኃላፊዎች በተደጋጋሚ በመጥራት ማብራሪያ መጠየቁና ማሳሰቢያም መስጠቱ ይታወሳል፡፡
አቶ አብዱራሂም አህመድ፣ በተደጋጋሚ ወደ ሕዝብ በመውጣት ድርጅቱን በሚመለከት በሕዝብ የሚነሱ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት በመገናኛ ብዙኃን ብቅ ማለታቸው የተለመደ ቢሆንም፣ ነገር ግን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አንዱአለም አድማሴንና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ቀርበው ያለውን ሁኔታ አለማስረዳታቸው የድርጅቱን አጠቃላይ አሠራር ግልጽ እንዳይሆን ተፅዕኖ ማድረጉንና በድርጅቱ አቅም ላይም ብዥታን እየፈጠረ መሆኑን የሚገልጹ አስተያየት ሰጪዎች አሉ፡፡
ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ በቀረው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መጨረሻ በአገር አቀፍ ደረጃ የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር 59 ሚሊዮን ለማድረስ የታቀደ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተጠቃሚዎች ቁጥር 29 ሚሊዮን መድረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)
http://www.goolgule.com/tele-service-interruption-escalated-to-more-than-a-week/

Wednesday, October 15, 2014

የዝናብ ሀሳቦች

(ብሌን ከበደ)

storm-clouds


ዝናብ መች ይከፋል ቢዘንብ ምን አለ
መብረቅ ባያስከትል እያጉረመረመ
መዝነቡንስ ይዝነብ ማበስበሱን ቢተው
ቀን የጣለ አይደል ሌት የሚያዳልጠው።
★★★
ሌቱን ሲዘንብ አድሮ ቀኑን ብራ ዋለ
ለምን ይወቅሱታል ሰው መስራት ከቻለ
ሲጥልም አይጣል ነው ዶፉ ከወረደ
ማን አለብኝ ያለው ገደሉም ተናደ።
★★★
ዝናቡ ከመጣ “አህያ ማይችለው”
በጊዜ ‘ንጠለል ከወረደ አንዴ ነው
እዲህ ከሚፎክር መጣሁ ቀረሁ እያለ
ወርዶ ቢያሳርፈን እሱም እፎይ ባለ።
ተጻፈ 8/5/2014
http://www.goolgule.com/thoughts-of-rain/

Monday, October 13, 2014

“መፈንቅለ ዓለም ባንክ!”

ኢትዮጵያን ኦባንግ በብቸኝነት ወክለዋል

o at w b


ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ያህል የዓለም ባንክ በተለይ ከሲቪል ማኅበረሰቦች ጋር ሲያካሂድ የነበረው ስብሰባ “በመፈንቅለ ዓለም ባንክ” ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያን በተለያዩ ዓለምአቀፋዊ መድረኮች በመወከል ድምጻቸውን የሚያሰሙት ኦባንግ“በመፈንቅሉ” ከተሳተፉት የዓለም ሲቪል ማኅበረሰቦች መካከል ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ነበሩ፡፡
የዓለም ባንክ ስለሚሰጠው ብድርና ዕርዳታ በተመለከተ ሊያካሂድ ያሰበው የፖሊሲ ለውጥ ሰነድ አፈትልኮ ከወጣ ጀምሮ በርካታ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሟገቱ ዓለምአቀፍ የሲቪል ማኅበረሰቦችን ያስቆጣ ሆኗል፡፡ የፖሊሲ ለውጡ ግልጽነትና ተጠያቂነት በሌለው መልኩ ለታዳጊ አገራት ብድር ከመስጠት ባለፈ በተለይ አምባገነናዊ አገዛዝ በሰፈነባቸውና አገዛዞቹንም ለሚደግፉ ድርጅቶች ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ ገንዘብ መስጠትን የሚፈቅድ ነው፡፡
በዚህ አሠራር መሠረት ማንኛውም ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ለማድረግ የሚፈልግ ድርጅት ወደ አንድ ታዳጊ አገር ለመሥራት በሚፈልግበት ጊዜ ባንኩ ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ ሳይጠይቅ ብድር ይፈቅድለታል፡፡ ሆኖም ድርጅቱ በዚያ ታዳጊ አገር ላይ የሰብዓዊ መብቶችን በመርገጥ፣ ከአምባገነናዊ ሥርዓቶች ጋር በመመሳጠር የፈለገውን ሕገወጥ ድርጊት ቢያከናውን የሚጠይቀው አይኖርም፤ ይህም እንደ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦ ብድሩን አያስከለክለውም፡፡
ለምሳሌ፤ መሬት ያለአግባብ ቢነጥቅ፣ ነዋሪዎችን ከቦታቸው ቢያፈናቅል፣ ለስደት ቢዳርግ፣ ህጻናትን በሥራ በማሰማራት “ባርነት” ቢያካሂድ፣ … ማንኛውንም ሰብዓዊ መብቶችን የሚረግጥ ሥራ ቢሰራ ለኢንቨስትመንት እስከተንቀሳቀሰ ድረስ ባንኩ ተጠያቂ አያደርገውም፤ ብድርም አይከለክለውም፡፡ ይህ አሁን ባንኩ ካለውና በበርካቶች ከሚተቸው አሠራሩ እጅግ መረን የለቀቀ ነው፡፡
የብሪክሶችን (BRICS – Brazil, Russia, India, China and South Africa) አሠራርና አካሄድ ለማክሸፍ የተነጣጠረ ነው የተባለለት ይህ የዓለም ባንክ ፖሊሲ ለውጥ ከ750 በላይ ዓለምአቀፍ የሲቪል ማኅበረሰቦች ተቃውመውታል፤ አሠራሩ እንዲቀየርም የማሻሻያ ፖሊሲዎችን ነድፈው አቅርበዋል፤ ለሳምንት ያህል በተካሄደው ስብሰባ ላይ ለባንኩ አመራሮች ገለጻ አድርገዋል፡፡
obang against land grabገና ከጅማሬው በስብሰባው ላይ በመገኘት የኢትዮጵያውያንን ድምጽ በብቸኝነት ሲያሰሙ የነበሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በስልክ በሰጡት አስተያየት ሳምንት የፈጀውን ስብሰባ አስረድተዋል፤ እርሳቸውም ከመሬት ነጠቃ ጋር በተያያዘ ህወሃት/ኢህአዴግ እንደ ካሩቱሪ እና የሼኽ አላሙዲ ሳውዲ ስታር መሰል የንግድ ድርጅቶች ጋር በመመሳጠር በኢትዮጵያ እያደረሱ ያሉት ግፍ ከበርካታ ማስረጃዎች ጋር የሲቪል ማኅበረሰቡ አባላት በተሰበሰቡበት ለባንኩ ከፍተኛ ኃላፊዎች በዝርዝር አስረድተዋል፡፡
“የኢትዮጵያ ተወካይ የለም” እየተባለ በሚገመትበት ቦታ ሁሉበብቸኝነት አገራቸውን በመወከል የአገራቸውን ጉዳይ ለዓለምአቀፍ መድረክ በማቅረብ በቀዳሚነት ስማቸው የሚጠራው “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ በኢትዮጵያ የሚካሄደው “የመሬት ነጠቃ” ሳይሆን “የህይወት ነጠቃ” ነው በማለት ተሰብሳቢውን የሲቪል ማኅበረሰብ ኃላፊዎች ያስደመመ፤ የባንኩ ባለሥልጣናትን አፍ ያስዘጋ መግለጫና ማብራሪያ በሳምንቱ የስብሰባ ቀናት ማቅረባቸውን ጎልጉል ያነጋገራቸው አንድ የሕንድ ሲቪል ማኅበረሰብና መቀመጫውን ሰሜን አሜሪካ ያደረገ የአካባቢ ጥበቃ ተንከባካቢ ድርጅት ተወካዮች ተናግረዋል፡፡
የስብሰባው መጠናቀቂያ ቀን በነበረው ቅዳሜ ዕለት የሲቪል ማኅበረሰቦቹ ባንኩ በተግባር ላይ ሊያውል ያሰበውን ፖሊሲ ባቀረቡት የማሻሻያ ነጥቦች መሠረት የማይቀይር ከሆነ ስብሰባውን ረግጠው እንደሚወጡ በኢሜይል በላኩት መልዕክት ገልጸው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት ከ750 በላይ የሲቪል ማኅበረሰቦች ኃላፊዎች እንዲሁም የባንኩ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት የመጨረሻ ቀን ስብሰባ ተቃሟቸውን እንዲያሰሙ ከተመረጡት መካከል ኦባንግ አንዱ ነበሩ፡፡ እርሳቸውም ከተናገሩት መካከል ባንኩ ግልጽነትና ተጠያቂነት በሌለው መልኩ፤ ስለ ሕዝብ የሚከራከሩ የሲቪል ማኅበረሰቦች እንዳይኖሩ በሕግ በተከለከለበት እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት በህወሃት/ኢህአዴግ የተፈጠሩ የሃሰት “ሲቪል ማኅበረሰቦች” ባሉበትና እነርሱ በሚሰጡት የአንድ ወገንና አገዛዙን የሚደግፍ መረጃ ላይ በመመርኮዝ ባንኩ የሰብዓዊ መብቶችን እንዲረገጡ በመፍቀድ ፖሊሲዉን ለመቀየር የሚያደርገው አካሄድ የሚወገዝ መሆኑን በአጽዕኖት መናገራቸውን ለጎልጉል ገልጸዋል፡፡
የሲቪል ማኅበረሰቡ በገባው ስምምነት መሠረት የመጨረሻ ተናጋሪ ህንዳዊው የሲቪል ማኅበረሰብ ተወካይo land grab ሶምያ ዱታ ነበሩ፡፡ እርሳቸውም የሲቪል ማኅበረሰቡን ድምጽ የሚወክል የተቃውሞ ጽሁፍ በንባብ አሰምተዋል፡፡ በንግግራቸውም ባንኩ የበርካታ ሕዝቦችን መብት የሚገፍፉ “የልማት” ተግባራትን ሲካሂድ እንደቆየ በመጥቀስ እንዲህ ያለውን አሠራር የሲቪል ማኅበረሰቦቹ ቢቃወሙም እስካሁን የተለወጠ ነገር አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡ ሲቀጥሉም ከዚህ አልፎ አሁን ደግሞ የአሰራር ለውጥ በማድረግ እጅግ በርካታ የዓለማችን ሕዝቦች የበለጠ ስቃይና መከራ እንዲደርስባቸው ባንኩ የፖሊሲውን ለውጥ እንዳያደርግ ሲወተውቱ መሰንበታቸውን አስረድተዋል፡፡ ሆኖም ለዚህ ሁሉ ውትወታ ባንኩ ጆሮ ዳባ ማለቱ እነዚህ ሁሉ በተሰበሰቡት ከ750 በላይ የሲቪል ማኅበረሰቦችና በሺዎች እነርሱ በሚወክሏቸው ስም የባንኩን ረቂቅ የማይቀበሉ መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ በመጨረሻም የሕዝባቸውን መብቶች ለማስከበር ከዓለም ጋር እንጂ ከባንኩ ጋር እንደማይቆሙ በመናገር በውጭ ያሉትን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች ለመቀላቀል ስብሰባውን ረግጠው እንደሚወጡ ይፋ አደረጉ፡፡
ቀጥሎም ጥቁር የተቃውሞ ሸሚዞቻቸውን በመቶዎች የሚቆጠሩት የሲቪል ማኅበረሰብ ተወካዮች በማሳየት ስብሰባውን አንድ በአንድ ረግጠው በመውጣት “መፈንቅለ ዓለም ባንክ” የተባለለትን ትዕይነት አሳዩ፡፡ ስብሰባውን የሚመሩት የዓለም ባንክ ከፍተኛ ባለሥልጣናትም በተከሰተው ትዕይንት ስብሰባውን መቀጠል ባለመቻላቸውና ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጪ በመሆናቸው ወሳኝ የነበረውን የዕለቱን ስብሰባ በይፋ ለመሰረዝ ተገድደዋል፡፡
ህንዳዊው በንባብ ያሰሙት ሙሉ ቃል እንዲህ ይነበባል፡-
It is nearly 3 years that you started this current review of your safeguards on Bank investments.  Affected communities and their support groups and many other CSOs from all over the world seriously & sincerely engaged with this and provided enormous amount of inputs about how the safeguard policies must be strengthened to ensure real protections for people and the planet.
Over these years, large sections of the people in poorer and developing countries faced the many threats from increasingly aggressive industrialization and extraction of ‘natural resources’, ever-more forceful evictions and land-grabs, dilution of labor rights & informalization, rapidly rising privatization of commons, discrimination against various marginalized communities.  Many of these were funded partly by the World Bank Group, where affected people looked for some basic minimum levels of protection, through the instrument of safeguards and expected improvements.  We have watched with rising concern that your new ‘safeguard’ proposals betrays these expectations and represent the opposite.
Instead of ensuring protection of vulnerable communities and the project affected people, your draft proposes dismantling of even existing protections that have been built over decades of hard work, hard won protections that people have fought and died for.
We cannot remain mute spectators of this regressive journey and must convey to you the rising frustration and anger amongst the many communities that are facing these impacts from Bank supported projects, and also within many people’s movements and supporting civil society groups, collectives and networks from around the world.
Even during the past few days of deliberations, we have watched with increasing dismay – the increasingly insensitive responses to the passionate appeals by cornered and distressed communities affected by bank supported projects.
We have watched the urgent pleas from our brothers and sisters from Guatemala and Cambodia – for minimum protection from rampant human rights abuses, being met with hawkish response like “not possible’.  We were frustrated by the cold shouldering of the sufferings of thousands of affected families of religious minorities from the western fringe of India, even after the confirmation by your own audit mechanism, of violations of performance standards and massive impacts.  And these are just a few examples.
We are also alarmed by the rising talk of the Bank venturing into riskier investments, coming from as high positions as the President! Hundreds of organizations of indigenous peoples and forest dwellers are terribly concerned with the proposed ‘opt out’ clause, and the dilution of protection hitherto given to biodiversity rich and protected areas.  You also propose to venture into uncharted territory of biodiversity offsets!  These are gambles more suited to a venture capital fund, not fit for a “Development Bank”, and the people of the world cannot allow this to happen.
We, the hundreds of people’s movements and organizations present here from around the world, and the many thousands we represent back in our countries, are rejecting this current draft of safeguards.  The protections you now seek to dismantle, the safeguards that we fought for over decades – do not belong to you, they are not yours to throw away, they belong to the world and its vulnerable people.
In our engagements here, we have also heard a handful of saner voices from within the bank, and urge them to fight inside the system, for protecting the very rights they themselves enjoy – also for the people and communities around the world facing potential threats from this proposed dilution of protections.  We strongly believe this protest action that we were compelled to take, will strengthen those voices and create a better environment for creating a really progressive safeguards policy.  This will be in the interest of the bank itself, as well as for the entire world.
That is why we are forced to take this action now and join our partners in the protest outside.  Today we are going out of this consultation, to defend the safeguards and to stand with the World and against the Bank that is trying to destroy it!  We sincerely hope that this will help a better tomorrow, within & outside.
http://www.goolgule.com/a-world-bank-coup-and-obang/

Saturday, October 11, 2014

የ‹‹ሚዲያ ካውንስሉ›› ምስረታ አጨቃጫቂ ጉዳዮች ተነሱበት

ነገረ ኢትዮጵያ
‹‹የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት የምክክር ጉባዔ›› በሚል የሚዲያ ካውንስ ለመመስረት እየተደረገ የሚገኘው ስብሰባ አጨቃጫቂ ጉዳዮች ተነሱበት፡፡ ለሁለት ቀን የሚቆየው ስብሰባ ዛሬ መስከረም 29/2007 ዓ.ም በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ የተጀመረ ሲሆን ‹‹የምክክር ጉባዔው››ን በሰብሳቢነት ወይዘሮ ሚሚ ስብሃቱ እንዲሁም በምክትል ሰብሳቢነት አቶ አማረ አረጋዊ መርተውታል፡፡ በጉባዔው በአብዛኛው ገዥውን ፓርቲ የሚደግፉ ሚዲያዎች፣ ማህበራትና ግለሰቦች ተገኝተዋል፡፡
mimi sibehatu
የመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ባተኮረው የዛሬው ውይይት ካውንስሉ ‹‹የትኞቹን ሚዲያዎች ይቀፍ?›› የሚለው ጥያቄ አጨቃጫቂ ከመሆኑም በተጨማሪ የ‹‹ሚዲያ ካውንስሉ›› በበጎ አድራጎት ድርጅትነት ወይንስ በንግድ ድርጅትነት ይቋቋም የሚለውም አጨቃጫቂና ውሳኔ ያልተሰጠበት ጉዳይ ሆኖ አልፏል፡፡
በስብሰባው ላይ መንግስት ለመረጃ ዝግ መሆኑንና ይህም በጋዜጠኞች ላይ ለሚደርሰው በደል እንደምክንያት የተነሳ ሲሆን የኮምኒኬሽን ሚኒስትር ድኤታው አቶ እውነቱ ገለታ ችግሩ እንዳለ አምነዋል፡፡
‹‹የምክክር መድረኩ›› አዘጋጆች ለቅድመ ጥናትና ለጉባዔው ከእንግሊዝ ኤምባሲ የገንዘብ እርዳታ እንዳገኙ ገልጸዋል፡፡
ሆኖም አሁንም ድረስ እውቅና የተነፈገው ‹‹የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ›› በምስረታው ወቅት ከእንግሊዝ ኤምባሲ ጋር ግንኙነት ባደረገበት ወቅት በመንግስት ድጋፍ የሚንቀሳቀሱት የጋዜጠኛ ማህበራት፣ በአሁኑ ወቅት የሚዲያ ካውንስሉን ለማቋቋም በግንባር ቀደምነት የሚንቀሳቀሱት ግለሰቦችና መንግስት ‹‹ከውጭ አካላት ጋር ግንኙነት እያደረገ ነው፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ይጎዳል›› በሚል መግለጫ ከማውጣትም በተጨማሪ በመንግስትና በመንግስት ደጋፊ ሚዲያዎች ወቀሳ እንዳቀረቡበት ይታወሳል፡፡
በነገው ዕለት ስለጋዜጠኝነት ስነ ምግባር፣ ስለ ሚዲያዎች አሰራርና መሰል ጉዳዮች ውይይት ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ነገረ ኢትዮጵያ መረጃዎችን እየተከታተለች ለማቅረብ ትጥራለች፡፡
Ze-Habesha

48 + 1 ደቂቃ ቢያልፍ ምን እንደሚከተል ግንዛቤ ነበር

“ወያኔዎቹ የተሰራላቸው ውለታ አልገባቸውም”
time is up


ከስያሜው ጀምሮ እያነጋገረ ያለው የኢህአዴግ የአሜሪካ ጽ/ቤት የጥበቃ ሰራተኛ፣ በኢህአዴግ አባባል “ዲፕሎማት” አገር ለቆ እንዲወጣ ከተሰጠው የጊዜ ገደብ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ ምን ሊከተል እንደሚችል አስቀድሞ ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ተጠቆመ። በስምምነቱ መሰረት ወዲ ወይኒ መባረሩ ከህወሃት ደጋፊዎችና አመራሮች ቅሬታ ማስነሳቱን አስመልክቶ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ዲፕሎማት “ወያኔዎቹ የተሰራላቸው ውለታ አልገባቸውም ማለት ነው” ሲሉ መደመጣቸውን የጎልጉል ታማኝ ምንጭ ተናገሩ።
ለተቃውሞ ወደ ኢህአዴግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ባመሩ ኢትዮጵያኖች ላይ ጥይት የተኮሰው የቀድሞው “ዲፕሎማት” ተመልሶ አሜሪካን መርገጥ እንዳይችል ተደርጎ የተባረረው በሁለቱም ወገኖች በተደረገ የውስጥ ስምምነት ነው። ለጉዳዩ እጅግ ቅርብ የሆኑ እንደገለጹት በአሜሪካው የምስጢር አገልግሎት (Secret Service) እና የዋሽንግተን ከተማ ፖሊስ ወዲ ወይኒን ለማሰር ወስነው ነበር። ውሳኔው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት እነ አቶ ግርማ ብሩ “ጓዳቸውን” ፈቅደው ለማሰናበት ቅድሚያውን በመውሰዳቸው ተጠርጣሪው ወንጀለኛ ሳይያዝ ቀርቷል። ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት (State Department) የተሰጠው መግለጫም ቃል በቃልም ባይሆን ይህንኑ ያረጋገጠ ሆኗል።
የምስጢር አገልግሎቱም ሆነ የከተማው ፖሊስ ከ“ፖለቲካው ግንኙነት” ጋር በተያያዘ ስለሚፈጠረው የፖለቲካ ውዝግብ ቁብ እንደሌለው ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ይሁን እንጂ አቶ ግርማ ብሩ “በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ ተነጋግረናል” ሲሉ ለአገዛዙ ተላላኪ ድረገጽ ባለቤት እንዳረጋገጡት የስቴት ዲፓርትመንት ሰዎች የጊዜ ገደብ በማስቀመጥ ያልተፈረደበትን ወንጀለኛ፣ ወዲ ወይኒን፣ ካገር የሚወጣበትን መንገድ እንዳመቻቹ ዲፕሎማቱ አልሸሸጉም።
“አሜሪካ በቂ ጥበቃ አላደረገችልንም” በማለት ተቃውሞ የሚሰነዝሩት አፍቃሪ ህወሃቶች የሚሰነዝሩትን ተቃውሞ አስመልክቶ “የተደረገላቸውን ውለታ ካለመረዳት ነው፤ አፋቸውን ቢዘጉ (ዝም ቢሉ) የተሻለ ነው” ሲሉ የተደመጡት ከፍተኛ ሃላፊ፣ ይህንን ሲናገሩ ክፉኛ ተበሳጭተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። የአሜሪካ መንግስት ተወንጃዩ ፍርድ ቤት ቀርቦ የሚዲያ ቁርስና ምሳ ሲሆን፣ ከዚሁ ጋር ከኢህአዴግ ጋር የሚነሳው ውዝግብና በምስራቅ አፍሪቃ በኩል ስለሚከወነው የፖለቲካ ጨዋታ ሲባል ጉዳዩ አሁን በተከናወነበት መልኩ እንዲጠናቀቅ መወሰኗን ከጉዳዩ ብዙ ርቀት የሌላቸው ክፍሎች አመልክተዋል። አቶ ግርማም ቢሆኑ “በዲፕሎማሲያዊ” ሲሉ ቋንቋውን ቢያስውቡትም ስምምነቱ ስለመኖሩ ከማሳበቅ ወደኋላ አላሉም።
በገደብ፣ በስምምነት የተቆረጠው 48 ሰዓት ቢተላለፍ ምን ሊከተል እንደሚችል ግንዛቤ በመኖሩ እነ አቶ ግርማ ወዲ ወይኒን አፋፍሰው ኢህአዴግ አለገደብ ወደሚገዛት አገር ልከውታል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ “ወዲ ወይኒ ወህኒ ወርደው ወዲ ወህኒ የሚል ስም ይሰጣቸው ነበር” ሲሉ ከዲሲ አካባቢ አንዳንዶች ተሳልቀዋል፡፡
ከኢህአዴግ ወገን አሁንም ዋሽንግተን ዲሲ ለተከራዩት ለጽህፈት ቤታቸው አሜሪካ ልዩ እንክብካቤ እንዲደረግ እየወተወቱ ነው። አሜሪካ ለዚህ ምንም ዓይነት የተለየ ጥበቃ የማታደርግ መሆኑ በተለያዩ መግለጫዎች የተነገረ ቢሆንም በህወሃት/የኢህአዴግ በኩል ጥያቄው እንዲነሳ ያደረገው መነሻ በድጋሚ ተመሳሳይ ውርደት እንዳይከሰትና ወደ ሌሎች አገራትም እንዳይዛመት ስጋት በመኖሩ ነው።
በተመሳሳይ ዜና ከአሜሪካ በሰዓታት ገደብ እንዲሰናበት የተደረገውና ተበደልን ባሉ ወገኖች ላይ ጥይት ሲተኩስ የነበረው ይኸው የትግራይ ተወላጅ ለሞራሉ በሚል ወደ ሌላ አገር ኤምባሲ ተዛውሮ እንዲሰራ አዲስ ምደባ እንደሚሰጠው የጎልጉል የውጪ ጉዳይ ምንጮች አመልክተዋል። ከህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን ወጣ የተባለው ይኸው የአዲሱ ምደባ ጉዳይ ለወዲ ወይኒ “ተጋዳላይነት”፤ ለሌሎች ደግሞ “አለኝታነትን ለማሳየት” በሚል ታስቦ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
http://www.goolgule.com/what-would-have-happened-to-wedi-weyni-after-48-hours/

Friday, October 10, 2014

ኦባንግ ስለ ሁለተኛው የአፍሪካ መሬት ነጠቃ

“ድርጊቱ የሚፈጸመው በእንግሊዝ ዕርዳታ ነው” አሉ
o meth o


ከጥቂት ሳምንታት በፊት ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ በሥራ ጉዳይ እንግሊዝ አገር ተገኝተው የነበሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ሎንዶን የሚገኘው Minority Rights Group International ጽ/ቤት ባደረገላቸው ግብዣ ቃለምልልስ አድርገው ነበር፡፡
በቃለ ምልልሱ ወቅት ሁለተኛው የአፍሪካ የመሬት ነጠቃ እየተካሄደ እንደሆነ እና እንዲህ ዓይነቱ አስከፊ ተግባር እየተፈጸመ ያለው በእንግሊዝና ሌሎች ምዕራባውያን አገራት ዕርዳታና ድጋፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይ በኢትዮጵያ የአናሳ ቡድኖች መብት አይከበርም የሚባልበት ሁኔታ ብቻ ሳይሆን ያለው እነዚህ ወገኖች መብት የሚባል ነገር እንደሌላቸው አቶ ኦባንግ ተናግረዋል፡፡ እንደ ማስረጃም በጋምቤላ አካባቢ መሬታቸውን በግፍ እየተነጠቁ ለስደት፣ ለግዳጅ ሰፈራ፣ ይህንንም የተቃወሙ ለስደት፣ እስራትና ግድያ የተጋለጡትን በመጥቀስ አስረድተዋል፡፡
በጋምቤላ ያለውን ሁኔታ ሲያስረዱም “በጋምቤላ ያለው ድህነት ለዘመናት ድርቅ ሲያጠቃው እንደኖረው የሰሜኑ ክፍል የሞቱ ላሞች፣ የኮሰሱ ህጻናት፣ የሚበሉት ያጡ ሰዎች የሚታዩበት አይደለም፡፡ እንዲያውም ጋምቤላ ከኢትዮጵያ ክፍሎች እጅግ ለም የሆነው ነው” በማለት አስረድተዋል፡፡ ነገርግን በክልሉ ያለው የዜጎች ንብረት ለሰፋፊ እርሻዎች እንዲሆኑ ለባለሃብቶች በመሰጠቱ እነዚህም ባለሃብቶች ያለገደብ በመሬት ነጠቃ ላይ በመሳተፋቸው የክልሉ ሕዝብ ለከፍተኛ ችግር መጋለጡን በቃለምልልሱ ማስረጃዎችን እየጠቀሱ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡
“146ሺህ ሔክታር የኢትዮጵያን ለም መሬት ለ99ዓመት በ99ሳንቲም ሊዝ ለመስጠት መስማማት ያውም ይህንን ዓይነቱን ውሳኔ ነዋሪውን ሕዝብ ሳያማክሩ ማድረግ እኤአ በ1884 የበርሊኑ ኮንፍራንስ አፍሪካን ከተቀራመቱት አውሮጳውያን ድርጊት ምንም ተለይቶ አይታይም” በማለት ያስረዱት የጋራ ንቅናቄው ዋና ዳይሬክተር የዚያን ጊዜ አውሮጳውያኑ ውሳኔውን ሲያስተላልፉ አፍሪካውያን በጠረጴዛው ላይ ባለመኖራቸው አፍሪካውያኑ እስካሁን የዚያ ዕዳ ከፋዮች ሆነው መቅረታቸውን “ጥቁር ሰው” ኦባንግ ሜቶ ተናግረዋል፡፡ “አሁንም” ይላሉ ሲቀጥሉ “አሁንም በሕዝብ ያልተመረጡ የአፍሪካ አምባገነኖችን (ነዋሪውን ሕዝብ ሳያማክሩ) መሬት እየነጠቁ፣ የተፈጥሮ ሃብት እየዘረፉ” እንደሆነ በግልጽ አስረድተዋል፡፡
ከምዕራባውያን መንግሥታት 3.1ቢሊዮን ዶላር የሚያገኘው የኢህአዴግ አገዛዝ የፈለገውን እንዲያደርግ ከአለቆቹ የተፈቀደለት እንደሚመስል በመናገር ምዕራባውያን በገሃድ ለሚታየው የሰብዓዊ መብት ረገጣ ዓይናቸውን መጨፈናቸው በኢትዮጵያ ቀኑን ጠብቆ የሚፈነዳ ቦምብ እንዲኖር የፈቀዱ ያህል መሆኑን አቶ ኦባንግ ተናግረዋል፡፡ ሲቀጥሉም “መፍትሔው ሰላማዊ ትግል ነው፤ ምክንያቱም በኢትዮጵያ በሥልጣን ላይ ያሉትና ሁሉንም ነገር የሚቆጣጠሩት የትግሬ አናሳዎች በመሆናቸው የዘር እሣተጎመራ ከፈነዳ የሚሆነውን ለመገመት እንኳን አይቻልም” በማለት አሁንም ለችግሩ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ከዓመጽ ነጻ የሆነ ትግል ማድረግ ብቻ እንደሆነ በአጽዕኖት አስረድተዋል፡፡
አቶ ኦባንግ ሜቶ ባደረጉት ቃለምልልስ ላይ የተጠናቀረው ዘገባ ሙሉ ቃል የሚከተለው ነው፡-

Ethiopia: Obang Metho condemns ‘Life Grabs’ and the Second Scramble for Africa

Speaking at MRG’s London office as part of a nationwide tour, Executive Director of the Solidarity Movement for a New EthiopiaObang Metho, sheds light on the systematic violation of indigenous land rights by Ethiopia’s autocratic regime, resulting in the alleged torture and imprisonment of those who resist. And although this is happening in a land far, far away, says Obang, these atrocities are funded by UK aid.
‘We live in a country where the minorities are not only denied their rights, but where their rights do not exist,’ deplored Mr Metho, painting a picture of Ethiopia as a land without rule of law, accountability, or even respect for the basic liberal principle that all people are equal. As a member of a minority tribe called Anuak, which comprises less than 0.1% of Ethiopia’s population, based primarily in the south-west region of Gambella, Obang claims to have had first-hand experience of being treated as a second-class citizen.
The problem in Gambella, however, is not one of poverty. ‘People usually know Ethiopia for the starvation, dead cows, skinny children, people not having enough food to eat,’ explains Obang, ‘but Gambella is one of the most fertile areas in Ethiopia.’
According to Mr Metho, the indigenous inhabitants of Gambella live off their land and the rivers; they breed their own cattle and grow their own crops. But the activist explains that while Gambella’s indigenous communities are self-sufficient, they receive no support from the government in terms of education, healthcare and the provision of clean water. On the contrary, he says, they are deprived of their only means of survival by a state policy of land grabbing.
gambell aObang describes the process of land grabbing as a brutal one. He claims that the government uses armed force to turn entire communities out of their homes, transporting them miles away from the land their families have owned for centuries before leasing the land to foreign firms, which turn it into commercial farms or sugar plantations in order to attract investment.  Obang claims that millions of acres of Ethiopian land have been seized in this way since the global food shortage in 2008.
‘In China, their population is skyrocketing,’ explains Obang, ‘their population needs food. But where do they find it? From somewhere where people have no voice, like Ethiopia.’
Obang explains that those who refuse to vacate their land and burn down their huts are generally arrested by Ethiopian authorities, tortured or forced into exile – allegations which have been echoed in NGO reports. Mr Metho claims that those who comply with the demands generally do so because they are promised the alternative of ‘villagization.’ While this term summons images of comfort, community and urban development, the reality is reportedly quite different:
‘The government’s action plan was to give these people access to services… But since the people have been displaced, which is up to three years ago for some of them, there’s nothing. There’s no school built, there’s no health centre… the local people had to build the school with wood, and the kids sit on the rocks. So some of these villages are abandoned, no one’s living there anymore.’
‘These are people who are used to feeding themselves, but now the government gives them food aid with ‘USA’ written all over it, while they sit there and do nothing all day. Making the people inactive… there are no words to describe that kind of injustice,’ he adds. ‘They’re taking them somewhere where the food will be given to them! The irony is just ridiculous. And no one is saying anything about it.’
According to Obang, Western aid perpetuates Ethiopia’s land grabbing policy; he claims that the donations, which constitute 40% of the country’s GDP, ultimately pay the wages of the Ethiopian soldiers commanded to seize indigenous property, while UK and US-supplied food packages are channelled to communities which have been ‘villagized’ against their will.
‘[Donor countries] don’t want to hear the words “accountability, transparency, corruption, good governing, human rights” because they carry responsibility,’ says Obang. ‘So they have turned a blind eye. Ethiopia is getting almost 3.1 billion dollars from the West. But rule of law..? The simple rights that the donor countries are founded on are being violated right in front of them, and they’re not doing anything about it.’world bank protest
British press coverage of one particular lawsuit against the UK Department of International Development by an Ethiopian victim of land grabs reflects this neglect. The plaintiff, “Mr O,” claims that UK aid, intended to supply starving Ethiopians with food and clean water, was misused by the State to pay the military who forcibly seized his land and tortured him. One particular leading British newspaper saw no reason for the UK to exercise due diligence on its aid exports, opting instead for a particularly inflammatory headline.
Obang believes that the Western media’s silence on the plight of Africa’s indigenous populations is tactical: ‘The donor countries of the West are turning a blind eye because Ethiopia claims to protect its national interests through the war on terror, fighting al-Shabab,’ says Obang, who agrees that while national interests are important, greater attention needs to be paid to the needs of individual citizens. ‘We need to have a society where we see the humanity before anything else, before religion, language, dialect,’ insists Obang.
‘For me it’s not a land grab. It’s life grabs. It’s grabbing the life and the future of these people,’ explains the activist. ‘These are not people who have grown up on food that’s been bought by income from the office. These are people who survive on the land… They are agriculturalists. So for them the land is who they are. So the land is their identity. They are the land, the land is them. And so when the government is coming to give this land to the foreigners without consultation, without compensation, it’s really scary.’
However, Obang reminds us that this is not the first time that foreigners have exploited poor governance in Africa in order to reap the continent’s resources. ‘This is what I call “the second scramble for Africa,”’ says Obang. But this time, he claims, Africans are taking a leading role.
‘An Ethiopian making the decision to lease 360,000 acres of land for 99 years for 99 cents without consulting the people is almost equivalent to the Berlin Conference in 1884. The Europeans made the decision to divide up Africa. Africans were not at the table. The decision was made, and even today, Africans are paying the price for that because they were not consulted,’ explains Obang. ‘And the same thing [is happening] now, these African dictators, autocratic leaders which are not elected by the people are doing exactly the same thing in terms of land grabs, in terms of natural resources .’
For Obang, the solution is unlikely to be a peaceful one. ‘Ethiopia is a ticking bomb’, he warns, ‘if it is not handled properly, it could be worse than Rwanda, because you have a tiny minority controlling everything: the Tigrayan people… The ethnic volcano will erupt in Ethiopia and when it does, everyone will say, “Oh, we didn’t know about this”.’
For Obang, therefore, the answer is to raise global awareness to the neglect of indigenous rights in Ethiopia and the unethical nature of trade relations between African countries and wealthier countries. His organisation, Solidarity Movement for a New Ethiopia, aims to sensitise indigenous communities in Ethiopia to their rights – a difficult task given that many NGOs and political opponents are either imprisoned in Ethiopia or banned.
‘We try to mobilise more people in the Diaspora and get the message back to the people,’ he says. ‘We have to be more tactical… we have what we call a “tree-mail.” If we want to send an idea, we write an article, send it to a person, and then that person prints it out, goes out late at night and nails them on the trees. So there is a way,’ insists Obang, ‘you cannot deny human freedom completely.’
But Mr. Metho insists that his cause requires long-term, international pressure to be placed on African despots. This, according to Obang, can only be achieved by encouraging world leaders to set aside trade concerns and Ethiopia’s elusive “national interests” and focus instead on the sufferings of individuals. Instead of seeking further Western aid, therefore, Obang merely asks that existing aid – which comprises 40% of Ethiopia’s GDP – be attached with the same transparency and accountability that is so valued in the Western world. ‘We are not asking the Western countries to free Africa,’ he explains, ‘but we’re asking them not to be the road-block for Africa.’
Isabelle Younane, MRG Communications Intern
Photos: (Top) Obang Metho, Executive Director of the Solidarity Movement for a New Ethiopia. Credit: Deutsche Welle/CC (Middle) Agriculturalists tend to their livestock in Gambella, Ethiopia. Credit: Julio Garcia/CC (Bottom) Protests in front of IMF/World Bank headquarters. Credit: Joe Athialy/CC
http://www.goolgule.com/ethiopia-obang-metho-condemns-life-grabs-and-the-second-scramble-for-africa/