FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Friday, June 5, 2015

የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ “ሰላይ” ነው – ዲና ሙፍቲ

“ከአገር የሚሰደዱት ገጠሬ ወጣቶች ናቸው”
spyvsspy
* “አቶ መለስ በጣም ይናፍቁናል”

አሸባሪነት በኢትዮጵያ ሊስፋፋ ያልቻለው ሕዝቡ በሙሉ ሰላይ መሆኑን ዲና ሙፍቲ አስታወቁ፡፡ ከአገር ተሰድደው የሚውጡት አብዛኛዎቹ ገጠሬ ወጣቶች እንደሆኑና ሟቹ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ህዳሴ አባት በጣም እንደሚናፍቋቸው ተናገሩ፡፡

ቀድሞ በቃል አቀባይነት ሲሰሩ የነበሩት በአሁኑ ወቅት ደግሞ በኬኒያ ተወካይ የሆኑት አቶ ዲና ሙፍቲ ስታንዳርድ ዲጂታል ከተባለ የኬኒያ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎች ድርጅታቸውን በመወከል  ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የአልሸባብና መሰል ታጣቂዎች የአሸባሪነት ተግባር በኢትዮጵያ ለማድረስ ያልቻሉበት ምክንያት ምንድርነው ተብለው ለተጠየቁት ሲመልሱ ሕዝቡ ሰላይ እንዲሆን የሰለጠነ መሆኑን በመጥቀስ ማንኛውንም ተጠርጣሪ ድርጊት ህዝቡ ሲያይ ሪፖርት እንደሚያደር ተናግረዋል፡፡ ሠራዊቱም እስኪበቃው ድረስ በዚህ ትምህርት አእምሮው የተሞላና የተጠመቀ በመሆኑ ጥቃቱ ሊኖር እንዳልቻለ አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የእስልምና ትምህርት ወደ አክራሪነት እንዳይሄድ ኢህአዴግ በየመድረሳው ከሚገኙ የሃይማኖት አስተማሪዎች በየጊዜው የሥራ ራፖር የሚያገኝ መሆኑን እንደተጨማሪ ማስረጃ አቅርበዋል፡፡

ኢትዮጵያውያን ከአገራቸው እየወጡ በኬኒያ አድርገው ወደ ሊቢያና ሌሎች አገራት ይሰደዳሉ፤ በርካታዎቹ ይሞታሉ፤ በአይሲስ ይታረዳሉ፤ … በማለት ጋዜጠኛው ጥያቄውን ሳይጨርስ አቶ ዲና ፈጠን ብለው እንዲህ አሉ፤ “ወደ ሌሎች አገራት ሲሄዱ የተያዙት አብዛኛዎቹ በሰው አዘዋዋሪዎች እየተባበሉና እየተታለሉ ከአገር የወጡ ናቸው፤ በርካታዎቹ ገጠሬ ወጣቶች ናቸው፤ ከዚህ ሌላ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ባለው ዕድል ተደስተው እየኖሩ ነው፤ ኢትዮጵያ በየአምስት አመቱ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የምታካሂድ ዴሞክራሲያዊት አገር ናት እንጂ በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ያለች አይደለም” ብለዋል፡፡

ወደ ኬኒያ ስለሚኮበልሉት ጋዜጠኞች ጉዳይ እንዲሁም በአሁኑ ወቅት ስድስት ታዋቂ ጦማሪያን እና ሶስት ጋዜጠኞች በእስር ላይ ስለመሆናቸው ለተጠየቁት ዲና ሙፍቲ አሁንም ፈጣን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያለው የሚዲያ ነጻነት ገና በዕድገት ላይ ያለ መሆኑ ያስረዱት አቶ ዲና በጋዜጠኝነት ሽፋን ህዝብን ከህዝብ ጋር ማጋጨትና ለግጭት ማነሳሳት ኢህአዴግ የማይቀበለው መሆኑን በመግለጽ አሁን በኬኒያ በስደት ያሉት እውነተኛ ጋዜጠኞች እንዳልሆኑ ተናግረዋል፡፡ በእስር ስላሉት ደግሞ የህጉ ጉዳይ ሳያልቅ አስተያየት ከመስጠት እንደሚቆጠቡ ገልጸዋል፡፡

“መለስ ይናፍቃችኋል?” ተብለው ሲጠየቁ ዲና ሙፍቲ ለሁሉም የኢህአዴግ ሰዎች መለስ በጣም እንደሚናፈቃቸውና የመለስ ራዕይ እስካሁንም እያበበ እንደሆነ አስረድተዋል፤ ሲቀጥሉም “ከአፍሪካ መሪዎች የራሱ መኪናም ሆነ ቤት ሳይኖረው የሞተ ብቸኛ መሪ መለስ ነበር፤ መለስ የመዋቅር ሰው ነበር እንጂ የራሱን ስብዕና ወይም አምልኮተ መለስ (ፐርሰናሊቲ ከልት) የገነባ አለልነበረም” ሲሉ ለቀድሞው አለቃቸው ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም በአዲስ አበባ የተዘረጋው የከተማ ባቡር መንገድ ሥራ ከዛሬ ሶስት ወር በፊት የሙከራ አገልግሎቱን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በአዲስ አበባ የትራፊክ መጨናነቅ በሚያስገርም ሁኔታ መቀነሱ ራሳቸውን ምስክር አድርገው አቶ ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም ከዚህ የባቡር ዝርጋታ ልምድ ኬኒያ ብዙ ልትማር እንደምትችልና የናይሮቢን ከተማ ከተመሳሳይ ችግር ማላቀቅ እንደማያስቸግር አስረድተዋል፡፡

http://www.goolgule.com/every-ethiopian-citizen-is-a-spy/

Thursday, May 14, 2015

በየመን የሚታየው ምስቅልቅል እየሰፋ ስለመጣው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውጥረት ምን ያስተምረናል?

(አክሊሉ ወንድአፈረው)
yemen crisis
በተለያዩ ሀገሮች የሚካሄዱ እንቅስቃሴዎች ያለፉባቸውን ጥምዝምዞች፣ የገጠማቸውን ደጋፊና አደናቃፊ ሂደቶች መመርመር በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚካሄደው ትግል ታላቅ ጠቀሜታ አለው። በዚህ አንጻር በ2011 የአረብ ስፕሪንግ ከአምባገነናዊ ስርአት ወደ ዴሞክራሲ ልትሸጋገር ነው ተብላ ተስፋ የተጣለባት የመን፣ እነሆ ዛሬ በእርስ በርስ ጦርነት ተናውጣ እንኳንስ ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ልትሸጋገር ከራሷም አልፋ አካባቢውን ለማመስ የቻለ ሁኔታ ውስጥ ገብታለች። ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ ብሎ መመርመር ለሀገራችን ዴሞክራሲያዊ ትግልም ሆነ በአካባቢው መረጋጋት ላይ ሊኖረው ለሚችለው እንደምታ ታላቅ ትምህርት ይሰጣል።

በዚህ አኳያ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ የየመንን ተመክሮ በመመርመር ለኢትዮጵያ ሁኔታ የሚኖረውን ትምህርት አመለክታለሁ። በርግጥ ይህ ጽሁፍ ሰፊ የሆነውን የሁለቱን ሀገሮች ውስብስብ የታሪክ፣ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ ኑሮ፣ ወዘተ እውነታ ሙሉ ለሙሉ በዝርዝር መሽፈን እንደማይችል ግልጽ ቢሆንም፣ ለቀጣይ ገንቢ ውይይት አስተዋጽኦ ያበረክታል ብዮ ተስፋ አደርጋለሁ።

የየመን ምስቅልቅል መሰረቶች

ለ150 አመታት ያክል ለሁለት ተከፍላ የቆየችው የመን በ1990 እንደገና ተዋሀደች ። ምንም እንኳ የተዋሀደችው የመን ህገመንግስት የብዙሀን ፖርቲዎች ስርአትን እንደሚቀበል የደነገገ ቢሆንም፣ የመን ከውህደት ቀኗ ጀምሮ አብደላሂ ሳሊህ ከስልጣን እስከተወገዱበት ጊዜ በእርሳቸው ፕሬዚደንትነት እና በፓርቲያቸው በየመን አጠቃላይ ህዝባዊ ኮንግረስ ፓርቲ (The General People’s Congress) የበላይነት ነው ስትገዛ የኖረችው።

አብዲላህ ሳሊህ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደስልጣን የወጡት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በጁላይ 17፣1978 በዚያን ጊዜዋ ሰሜን የመን ሲሆን የመሪነት ምሳሌነታቸውን ሀ ብለው የጀመሩትም ስልጣን ከያዙ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 30 የሰራዊቱ ባለስልጣኖችን እንዲገደሉ ትእዛዝ በመስጠት ነበር። የሟቾቹም ጥፋት “ስልጣኔን ለመጋፋት አሲረዋል” የሚል ነበር። ይህ ሁኔታ ያመላከተውና በቀጣይም የተረጋገጠው የአብዲላሂ ሳሊህ ራእይ ተቃዉሞን ጨፍልቆ ስልጣንን ለብቻ ጠቅልሎ መኖር እንደሆነ ነበር። መልእክቱ ገና ከጠዋቱ ግልጽ ነበር፡፡

ውህዷ የመን በመጀመሪያው ጥቂት አመታት ከየመን ሲሻሊስት ፓርቲ እስከ እስላማዊው ኢስላህ (Islaah) ፓርቲ ድረስ ያሉት ሁሉ የተሳተፉበት የተለያዩ የፖለቲካ አመለካከቶች የተሰተናገዱበት ህገመንግስት በሜይ 1991 አጸደቀች፡፡ በ1993 በተካሄደ ምርጫም ሕዝባዊ ኮንግረስ 143 ፣ የየመን ሶሻሊስት ፓርቲ 69 ኢስላህ የተሰኝው የእስልምና ፓርቲ 63 የባአዝ አመለካከት ተከታይ ፓርቲ 6፣ የናስር ርእዮትን የሚከተለው ፓርቲ 2፣ አል ሀቅ 2 እና ከምንም ፓርቲ ያልወገኑ ግለሰቦች 15 ወንበር ይዘው ነበር፡፡
በዚህ ምርጫ ምንም እንኳ መሰረቱ በዋናነት የቀድሞዋ ደቡብ የመን የሆነው ሶሻሊስት ፓርቲው ሁለተኛውን ብዛት ያለውን የፓርላማ መቀመጫ ያሸነፈ ቢሆንም ባዲሱ የትብብር መንግስት ውስጥ ግን፣ ህዝብ በብዛት ከሌለበት አካባቢን የሚወክል ነው በማለት፣ የሚገባውን ቦታ ሳያገኝ በምትኩ የእስላማዊው ፓርቲ (ኢስላህ) መሪ አብዲላሂ ቢን ሁኔይን ከአሊ አብዲላህ ሳሊህ እና በፓርቲያቸው በየመን አጠቃላይ ህዝባዊ ኮንግረስ ፓርቲ ጋር የጋራ መንግስቱን እንዲመሰርቱ ተደርጎ አብዲላሂ ቢን ሁኔይን የፓርላማው አፈ ጉባኤ ሆነው ተመረጡ። ይህ ጉዳይ የደቡብ የመንን ህዝብ እና የሶሻሊስቱን ፓርቲ ቅሬታ እንዲገባቸው ማድረግ ጀመረ።

በመቀጠልም ሀድረመውት (Hadhramaut) እየተባለ በሚጠራው ደቡብ የመን ክፍል ሰፊ የነዳጅ ዘይት ማምረት ሲጀመር፤ መሬታችንንና ሀብታችንን ያላግባብ በሰሜናውያኑ ተዘረፈ የሚል ከፍተኛ የቅሬታ ስሜት በደቡቡ ነዋሪዎች መሀል ተቀሰቀሰ።
በመቀጠልም በትብብሩ መንግስት ውስጥ የበለጠ ቅሬታና መፍረክረክ የተከተለው ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ የመናውያን፣ መንግስታችሁ የገልፉን ጦርነት እልደገፈም በማለት ከሳውዲ አረቢያ ተባረው ድንገት ወደየመን ሲመለሱ ነበር። እነዚህ እጅግ ብዙ ገንዘብ ወደሀገራቸው በመላክ የሀገሪቱን እኮኖሚ ያግዙ የነበሩ ሰዎች ድንገት ከሳውዲ ሲባረሩ ወደሀገሪቱ የሚገባው የውጭ ምንዛሬ ባንድ ጊዜ ደረቀ። ለተመላሾቹም ቤት፣ ስራ ወዘተ ማመቻቸት ለመንግስቱ እጅግ ከባድ ሆነ።

ይህ ሁኔታ የፈጠረው ጫና በትብብሩ መንግስቱ ውስጥ አለመግባባትና ቅራኔውን አፋፋመው። ቀጥሎም፣ የሀገሪቱ ምከትል ፕሬዚደንት አሊ ሳሊም አል በይደር ስልጣናቸውን ለቀው ወደ ደቡቧ ከተማ ወደ ኤደን ተሰደዱ። የቀድሞው የደቡብ የመን ፕሬዚደንት የውህዷ የመን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሁነው ቢቀጥሉም በአጠቃላይ በተለያዩ ፓርቲዎች ውስጥ በተፈጠረው አለመተማመን እና ንትርክ ምክንያት ፕሬዚደንቱ ስልጣናቸው ዋጋ ቢስ ሆነ።

በዚህ ሁሉ መሀል ጎሳ ነክ የሆኑ አመለካከትን የሚያራምዱ ድርጅቶች በሰሜንም በደቡብም የሀገሪቱ ክፍል ራሳቸውን ማጠናከሩን ቀጠሉበት እያደርም በተለያየ የፖለቲካ ክፍሎች መሀል የሚታየው አለመግባባትና ግጭት እየሰፋ ሄደ። ሁኔታው ተባብሶም በሜይ 21፣ 1994 ደቡብ የመን ተገንጥላ የየመን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ብላ ራሷን እንደ ነጻ ሀገርና መንግስት አወጀች።

ይህች አዲስ ሀገር በአለም አቀፉ ማህበረሰብ እውቅናን ያላገኘች ሲሆን፣ ባብዛኛው በሰሜን የመን ባለስልጣኖችን ያካተተው መንግስትም የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ አካሂዶ በጁን 7፣1994 ኤደንን ተቆጣጠረ። ደቡቡና ሰሜኑ ሲዋሀዱ ቀደም ሲል በሁለቱም በኩል የነበረው ሰራዊት ሙሉ ለሙሉ ስላልተዋሀደ በድርጅቶች መሀል አለመግባባት ሲፈጠር በሁለቱም በኩል ያለው ሰራዊት በገለልተኛነት ቆሞ ሀገራዊ የማረጋጋት ሀላፊነት ከመወጣት ይልቅ፣ ከየክልሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ወግኖ ግጭቱን እጅግ ወደመረረ ደም መፋሰስ አናረው። ሁለቱም የውህዷ የመን አካሎች (ሰሜኑም ደቡቡም) ቀደም ሲል እንደመንግስት የተደራጀ ሰራዊት ስለነበራቸው የደቡብ አማጽያንና በዋናነት ከሰሜን የመን በመጣው የመንግስት ሰራዊት መሀል የተካሄደው ውጊያው በታንክ እና ባይሮፕላን ጭምር ነበር።
የሰሜኑ ጦር ኤደንን መቆጣጠሩን ተከትሎም በሽዎች የሚቆጠሩ የደቡብ የመን የፖለቲካ ሰዎችና ወታደሮች ሀገር ለቀው ተሰደዱ። የደቡብ የመን ህዝብ እምርሮ በሰሜኑ ነዋሪዎች ተረግጠናል፣ የሚለው ሰሜት እጅግ እየሰፋ ሄደ። ከሰሜኑ የመን ተገንጥሎ ነጻ የደቡብ የመን መንግስትን ለመመስረት የሚደረገው ትግልም ከፖለቲካ ተቃውሞ እስከ ትጥቅ ትግል ደረሰ። ይህ ሁኔታ በዚሁ በደቡብ የመን ውስጥ ተጠናክሮ ለቀጠለው አልቃይዳም አመች ሁኔታን ፈጥሮለታል።

ከላይ ከተጠቀሱት ሌላ አብድላሄ ሳላህ የስልጣን ተቀናቃኝ የበዛባቸው የያዙትን ስልጣን መደላድል የሚያጠናክር ህገመንግስታዊ ማሻሻያ በተከታታይ በመውሰድ ስልጣናቸውን ለማንም ሳያካፍሉ እርሳቸው ቤተሰቦቻቸው እና ድርጅታቸው በዘላቂነት ለመግዛት የሚያስችላቸው እርምጃወችን ይወስዱ ስለነበረ ነው፡፡ ለምሳሌ በ2000 አመተ ምህረት ልጃቸውን የስልጣናቸው ወራሽ ለማድረግ የወሰዱት እርምጃ የቅርብ አጋሮቻቸው ሳይቀሩ እንዲርቋቸው አድርጓል። በዚህም ምክንያት የቅርብ አጋሮቻቸው ሳይቀሩ ከ2009 ጀምሮ አብድላሄ ሳላህ ስልጣን መልቀቅ እንዳለባቸው በግልጥ ይናገሩ ነበር።

አብደላሂ ሳላህ የውህዷ የመን ፕሬዚደንት ከሆኑ በኋላ በደቡብ የመን የነበረውን የመገንጠል ስሜት ሊያስወግዱ ባለማቻላቸው ብዙዎችን የመሪነት ብቃታቸውን እንዲጠራጠሩ አድርጓቸዋል፡፡ እንዲሁም በሰሜን በኩል እያደር የመጣውን የሁቴዎችን እንቅስቃሴ ሊገቱ ባለመቻላቸው የሺዓዎችን መጠናከር እና የኢራንን ጣልቃ ገብነት የሚፈሩ ሁሉ አብድላሄ ሳላህ ላይ ታላቅ ቅሬታ እንዲያድርባቸው ሆኗል።

በመቀጠልም በማርች 18፣ 2011 51 ሰላማዊ ሰልፈኞች በጸጥታ ሀይሎች ከተገደሉ በኋላ እጅግ የቅርብ ወዳጆቻቸው ሳይቀሩ ፕሬዚደንት ሳላህ ከስልጣን መውረድ እንዳለባቸው ይናገሩ ነበር፡ (Charles Schmitz, Yemen’s National Dialogue ፣ a policy paper serious, PP 8 , Middle east Institute, February 2015.)
ይህ ሁሉ ሲሆንም ቀስ በቀስ ባንድ ወቅት በመካከለኛው ምሰራቅ በዴሞክራሲያዊ ጅምሯ ውዳሴን ያገኝችው የመን፤ ህዝቧ ከማዕከላዊም መንግስት ጋር ሆድና ጀርባ እየሆነ መጣ። በዚህ ውስብስብ የቅራኔ ሂደት ውስጥ የአልቃይዳ ተዛማጅ የሆነው እንቅስቃሴም ስር እየሰደዱ የቅራኔው አደገኛነቱም እየጨመረ ነበር የመጣው።
ለማጠቃለል የየመን የፖለቲካ ምስቅልቅል መስረቶች
  • እያደር እየጠበበ በመጣው የፖለቲካ ምህዳር ምክንያት በስርአቱ ውስጥ ሀሳብን በነጻ ማራመድ አይቻልም የሚለው አመለካከት በተቃዋሚውም በህዝቡም አመለካክት ውስጥ በመስረጹ
  • ስርአቱ በተለያየ ማጭበርበሪያ በመጥቀም ለውጥን ለማገትና ራሱን ዘላለማዊ ገዥ ለማድረግ በመሞክሩ የተለየ ራዕይ ያላችው በህጋዊነት በመታገሉ ላይ ተስፉ መቁረጣቸው
  • ስርአቱ በሀገሪቱ ውስጥ ለሚነሱ ጥያቈዎች አና ግጭቶች መፍትሄ ሊሰጥ ስላልቻለ በአንድ በኩል ችግሩን ለመፍታት ቅንነት የለውም በሌላ በኩል ችሎታ/ብቃት የለውም የሚለው አስተሳሰብ መስፈኑ
  • የስራ አጥነት መጠን አጅግ ክፍ ብሎ በወጣቱ ላይ ያሳደረው ተስፋ መቁረጥ
  • በጎሳ ላይ ያተኮረ ማህበራዊ ግንኝነትን ትልቅ ቦታ የሚስጥው የህብረተሰብ አደረጃጀት የገዥውን ቡድን አግላይነት በቀላሉ የጎሳ ትርጕም በመስጥት እኛ እና እነሱ ለሚለው አደገኛ አመለካለት ስፊ አድል በመክፈቱ
  • ደቡብ አና ስሜን የመን ሲዋሀዱ ሰራዊቱ በጊዜ ከአንድ አካባቢ ወይም ድርጅት ታማኝነት አንዲወጣና በሀገራዊ ራዕይ አንዲዋሀድ ባለመደረጉ።(ሌሎችም የታጠቁ ሀይሎች እንዲሁ ወደሀገራዊ ሰራዊትነት እንዲቀላቀሉ ሳይደረግ የፖለቲካ ድርጅቶች መሀል ግጭት ሲከሰትም ከሀገሪቱ ይልቅ ለየጎሳው ወግኖ እንዲነሳ ተመቻችቶ መገኘቱ)
  • ከሁሉም በላይ ደግሞ አብደላሂ ሳሊህ እና ድርጅታቸው በተለያየ ደረጃ መቻቻልን እንዲያሰፍኑ፤ ስልጣንን እንዲያጋሩ፣ ንቅዘትን እንዲያሰወግዱ መብት እንዲያከብሩ፣ እርቅ አንዲያወርዱ ቢለመኑም ነገሩን ሁሉ በማሳነስ በውጭ ድጋፍ ላይ እጅግ በመመካት በትምክህት የተፈጠረውን እድል ሁሉ ሊጠቀሙበት አለመቻሉ
ጥቂቶቹ ነበሩ።
የጸደይ አብዩት በየመን (አረብ ሰፕሪንግ)ና የዲሞክራሲ ሀይሎች ንቅናቄ
የአብድላሂ ሳሊህ እና ፓርቲያቸው ህዝባዊ ኮንግረስ ፓርቲ (The General People’s Congress) በሚያካሂደው ያላቋረጠ የመብት ረገጣ የተነሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከህዝብ እየተነጠሉ፣ አዳዲስ ተቃዋሚወችንም በሰፊው እያፈራ በውስጡም እየተፍረከረከ ነው የተጓዘው፡፡ ባንድ ወቅት ተከፋፍላ ለነበረችው ሰሜንና ደቡብ የመን መዋሀድ ባለውለታ በመሆኑ የተወሰነም ቢሆን አክብሮት የነበራቸው አሊ አብዲላህ ሳሊህ እና ፓርቲያቸው አጠቃላይ ህዝባዊ ኮንግረስ ፓርቲ (The General People’s Congress) ቀስ በቀስ በሕዝብ አክ እንትፍ ተባሉ።

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2011 ሰሜን አፍሪካንና መካከለኘው ምስራቅን ያናወጠው ሕዝባዊ አመጽ ወደ የመን የደረሰው ብዙም ሳይዘገይ ነበር። እንደ ቱኒዝያና ግብጽ፣ በየመንም ህዝብ በየከተማው በነቂስ በመውጣት አሊ አብዲላህ ሳሊህና ፓርቲያቸው የያዙትን መንግስት ከስልጣን እንዲለቁ ጠየቁ።

የአጠቃላይ የህዝባዊ እንቅስቃሴ ሞተር በመሆን ይህን ሕዝባዊ አመጽ የመሩት ወጣቶች ስርአቱን አስወግዶ በምትኩ መቻቻል የሰፈነባት፣ ዴሞክራሲያዊት የመንን እውን ለማድረግ ቆርጠው ተነሱ፡፡ የየመን ወጣቶች እንቅስቃሴ “civil state,” በማለት የሰየሙት ስርአት እንዲመሰረት ነበር ትኩረት አድርገው የሚጠይቁት። ይህ ሲቪክ መንግስት (civil state) በወጣቶቹ አገላለጥ በህግ የሚገዛ፣ ባስተዳደር ችሎታ ቴክኒካዊ ብቃት ያላቸውን ያቀፈ እና ከሙስና የጸዳ ስርአት ነው። ባጭሩ፣ የለውጥ ፈላጊወቹ ወጣቶቹ ፍላጎት ገዥውን ቡድን ማስወገድ ብቻ ሳይሆን በምትኩ የዴሞክራቲክ ስርአትን መመስረትም ነበር

ትግሉ እየጠነከረ የተቃዋሚው ጎራም እየሰፋ ቢመጣም አሊ አብዲላህ ሳሊህ እና ፓርቲያቸው ግን ቀደም ባሉት አመታት እንዳደረጉት ሁሉ ይህንንም ተቃውሞ ጨፍልቆ ማለፍ ይቻላል በሚል ግምት ስልጣንን የሙጥኝ ብለው ተቀመጡ።
ይህም በመሆኑ በአሊ አብዲላህ ሳሊህ እና ፓርቲያቸው ላይ ተጽእኖ ለማድረግ እና ትግሉን ለማፋፋም፤ ከተለያየ ህብረተሰብ ክፍሎች እና የፖለቲካ ድርጅቶች ህብረት በኦገስት 2011 ተመሰረተ። ይህ ብሄራዊ የምክክር ካውንስል (the National Council) ተብሎ የተሰየመው አካል 143 አባላት ያሉት ነበር። ይህ ትብብር የተለያየ የፖለቲካ አቋም እና ፍላጎት የነበራቸውን ድርጅቶች ወደአንድ መግባቢያ እንዲደርሱ በማድረግ በተፍረከረከችው ሀገራቸው ህዝብ ላይ እንደገና የተስፋ ብርሀን ብልጭ እንዲል አደረገ።
በፎቶው ላይ የሚታዩት ከመሀል መሀመድ ባሲንደዋህ (Mohammed Basindwah) አዲስ የተመሰረተው የተቃዋሚወች ትብብር ፕሬዚደንት፡ በግራ በኩል አብደል ዋሂብ አል አነሲ (Abdul Wahab Al-Anesi) የ እስላማዊው ኢስላህ ፓርቲ (Islah Party) ዋና ጸሀፊ በቀኝ በኩል ደግሞ የየመን ሶሻሊስት ፓርቲ ዋና ጸሀፊ ያሲን ሰኢድ ኑማን (Yasin Said Numan) ናቸው።
በፎቶው ላይ የሚታዩት ከመሀል መሀመድ ባሲንደዋህ (Mohammed Basindwah) አዲስ የተመሰረተው የተቃዋሚወች ትብብር ፕሬዚደንት፡ በግራ በኩል አብደል ዋሂብ አል አነሲ (Abdul Wahab Al-Anesi) የ እስላማዊው ኢስላህ ፓርቲ (Islah Party) ዋና ጸሀፊ በቀኝ በኩል ደግሞ የየመን ሶሻሊስት ፓርቲ ዋና ጸሀፊ ያሲን ሰኢድ ኑማን (Yasin Said Numan) ናቸው።

ተቃዋሚው ራሱን አሰባስቦ ተከታታይ ሰላማዊ ግፊትን በማድረግ አሊ አብዲላህ ሳሊህ ከስልጣናቸው እንዲለቁ ጥሪውን ቀጠለ። ከፖለቲካ ድርጅቶች እና የወጣቱ መሪዎች በተጨማሪም ብዙ ታዋቂ ግለሰቦችም በህዝባዊው እንቅስቃሴው አሊ አብዲላህ ሳሊህን ከስልጣን በማስወገድ በምትካቸውም ሁሉን አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለመመሰረት ለሚደረገው ትግል ድጋፋቸውን ሰጥተው ነበር። ከነዚህም ውስጥ ከዚህ በታች ምስላቸው የሚታየው በ2012 የኖቤል ሽልማት አሸናፊ የሆኑት ተዋኩል ካርማን (Tawakul Karman) አንዷ ናቸው።

የየመን ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከሞላ ጎደል እጅግ በሚያሰገርም መረጋጋት ትግሉን ሁሉ በሰላማዊ መንገድ ቢያካሂድም ፣ ጽንፈኛ የሆነው የአልቃይዳ እና ከእሱም ጋር የተባበሩ ታጣቂዎች በሰላማዊ ትግሉ ውስጥ አየተቀላቀሉ አልፎ አልፎ ንቅናቄውን የመሳሪያ ሀይል የተጨመረበት ሲያደርጉት ታይቷል።
የኖቤል ሽልማት አሸናፊ የሆኑት ተዋኩል ካርማን
የኖቤል ሽልማት አሸናፊ የሆኑት ተዋኩል ካርማን
በወቅቱ አሜሪካኖች “ተቃዋሚውን ከሳላህ መንግስት ጋር በመሆን በኃይል ያጠቃሉ” እየተባለ ይነገር ለነበረው ተቃውሞ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካን ባለስልጣን ሁኔታውን እንዲህ ሲሉ ገልጸውታል “የአልቃይዳ ስርጎገቦች ከሌሎች ጸረ መንግስት ሀይሎች ጋር ተቀላቀቅለው ስለሚንቀሳቀሱ አሜሪካን በየመን የሚገኙ ያልቃይዳ አማጽያን ላይ የሚወሰደው የሀይል እርምጃ ለመንግስቱ የወገነች ሳትመስል መንቀሳቀስ እጅግ ከባድ ነው።”

የሳላህ መንግስትና የሀያላኑ ግንኙነት

የመን ከምእራቡ ሀገር በተለይም ከአሜሪካን እና ከሳውዲ አረብያ ጋር የቅርብ ግንኑነት ያላት ሀገር ናት። ያሜሪካን ዋና ትኩረት በየመን ውስጥ መሽጎ የሚገኘውን የአልቃይዳ ድርጅት መደምሰስ ነው፡፡ በሌላ በኩል የሳውዲ አረብያ (እንዲሁም የሌሎቹ የገልፍ ሀገሮች) ዋና ፍላጎት ደግሞ በየመን ሺዓ ሙስሊሞች በኩል ሊደርስብኝ ይችላል ብላ የምትሰጋበትን የኢራን መንግስት ግፊት መቋቋም ነው። የኢራን የኃይማኖት መሪዎች ለሳውዲ ንጉሳዊ ቤተሰብ ፍቅር እንደሌላቸው ብቻ ሳይሆን ስራቸው ሁሉ ከእስልምና ህግጋት ጋር የተጻረረ ስለሆነ መወገድ አለባቸው ብለው በይፋ በተደጋጋሚ ተናግረዋል።

ኢራኖች በተለይም የሺዓ እምነት ተከታይ የሆኑትን የሁቱ ነገድ ሙስሊሞችን ተከታታይ የመነሳሳት እንቅስቃሴ ስለሚደግፉ ይህ እንቅስቃሴ እንዳያድግ እና እናዳይጠናከር ሳውዲዎችም ሆኑ ሌሎች የገልፍ መንግስታት አጥብቀው ይጥራሉ። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ በየመን ውስጥ እነሱ የሚቆጣጠሩት ወይም ለነሱ ታማኝ ያልሆነ መንግስት እንዳይመሰረት እጅግ ይሰጋሉ። የመን ከሳውዲ ጋር ባላት የድንበር አዋሳኝነት የተነሳ በየመን ውስጥ የሚደረግ ነገር ሁሉ ሳውዲን ይነካል ብለው ስለሚሰጉ፣ የሳውዲ ባለስልጣኖች የመንን ባይነቁራኛ መመልከት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ አካሄዷን ለመቆጣጠር ሁልጊዜም ይጥራሉ።

የሳላህ መንግስት ለአሜሪካንም ይሁን ለሳውዲ የነበረው ታማኝነት 100% በላይ ነበር ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህም በመሆኑ ህዝበዊ ትግሉ እጅግ በተፋፋመበት እና በለውጥ ፈላጊው የዴሞክራሲያዊ ሀይሎች ላይ ስርአቱ ታላቅ ጭፍጨፋ ያካሂድ በነበረበት በ2011 መጨረሻ ሳይቀር አሜሪካ ለሳላህ መንግስት የ120 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ባብዛኛው ወታደራዊ ሰጥቶ ነበር።
በማርች 2012 ዘ ኔሽን በተሰኝው ጋዜጣ ላይ የቀረበ አንድ ሪፖርት እንዳለውም በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ1980ቹ ከተጀመረው ሶቭየት ህብርትና ከአፍጋኒስታን የማስወጣት ጦርነት ጀምሮ ከዚያም የ9/11 ን ሽብር ተከትሎ የሳላህ መንግስት አልቃይዳንና ጸረ ሽብርተኛነትን እንደማሰፈራሪያ በመጠቀም ካሜሪካኖች እና ከሳውዲ አረብያ ስልጣኑን ለማጠናከር እና ተቃዋሚወቹንም ለማዳከም የሚያስችለው ከፍተኛ ድጋፍን አካብተውበታል

በውጭ ግንኙነት ጉዳይ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚንቀሳቀሰ አንድ ድርጅት (ካዉንስል ፎር ፎሬን ሪሌሽን) በቅርቡ እንደዘገበው አሜሪካ ለፕሬዚዳንት አሊ ሳሊህ መንግስት ያደረገችው እርዳታ ከአመት ወደ አመት እጅግ ፈጣን በሆነ መልክ ሲያድግ ነበር የቆየው።

የምእራቡ አለም እና ያካባቢው መንግስታት ነጠላ ጥቅም ላይ ያተኮረ አካሄድ በዴሞካራሲ እንቅስቃሴው ላይ ያሳደረው እንደምታ

የየመን ህዝባዊ እንቅስቃሴ እያደገ ቢመጣም አሜሪካኖች ከሳላህ በኋላስ ምን ይሆናል ለሚለው በቂ ዝግጅት አላደረጉም ነበር። ሳውዲዎችና የገልፍ መንግስታትም ያለው ሁኔታ ተመሳሳይ ነበር። ከሳላህ በኋላ የሚመጣው መንግስት ከቁጥጥራቸው ውጭ ቢሆንስ የሚለው እጅግ አሰጨቋቸው ነበር።

በተቃዋሚው እና በምእራቡ መንግስታት መካከል የተወሰነ ግንኙነት ቢደረግም፣ የአብዳላሂ ሳላህ ቢወገዱ ባልቃይዳ ላይ ለሚያካሂዱት ጥቃት ተቃዋሚው ሙሉ በሙሉ ድጋፍ ይስጥ ይሆናል ወይ ለሚለው ጥያቂ ባሜሪካኖች በኩል በተወሰነ ደረጃ እርግጠኞች አልነበሩም። ተቃዋሚው የብዙሀን ፓርቲ ስርአትን፣ የምእራቡን የሚመስል ዴሞክራሲ፣ አሰፍናለሁ ቢልም ላሜሪካኞች ይህ ቅድሚያ የሚሰጡት አልሆነም፡፡ ስለዚህ ሙሉ በሙሉ የስርአት ለውጥን ከመደገፍ ይልቅ ሳላህን አስወግዶ ስርአቱን ግን ማስቀጠሉን ስራዬ ብለው ተያያዙት።

የሳውዲ አረብያና ሌሎችም የጎልፍ መንግስታትም በተመሳሳይ መንገድ ያቀረቡት የውሳኔ ሀሳብ አብደላሂ ሳላህን አስወግዶ በቦታው ምክትል ፕሬዚደንቱን አብዱ ረቡ ማንሱር ሃዲ (Abdu Rabbu Mansour HadI) ወደ ስልጣን ማምጣት ነበር።
በዚህም መሰረት ያሜሪካውኑ ፕሬዚደንት የተከበሩት ባራክ ኦባማ የጸረ ሽብር አማካሪና በኋላም የሲአይኤ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ጆን ብረናን (John Brennan), ፕሬዚደንት ሳላህን በሳውዲ አረብያ ከሚገኙበት ሆስፒታል ከጎበኙዋቸው በኋላ ስልጣናቸውን እንዲለቁና ለምክትል ፕሬዝደንቱ እንዲያስተላልፉ ነገሯቸው፡፡

የተቃዋሚዎች ህብረትም ሆነ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ይህንን የሳውዲና ያሜሪካ እቅድ ፈጽሞ አልተቀበሉትም የህዝቡን እንቅስቃሴ ለማምከን የሚደረግ ሴራ ሲሉ ነበር ያወገዙት።
ተቃዋሚው በስርአቱ ውስጥ ሙሉ ተሳታፊ መሆን እንዳለበት አበክሮ ቢያሳሰብም የገልፍ መንግስታትም ሆኑ አሜሪካ አልደገፉትም። የሽግግር እቅድ ተብሎ ባሜሪካና በገልፍ መንግስታት (ሳውዲ፣ ኳታር፣ ባህሬን) የቀረበውም ሁሉን አቀፍ መንግስት መመስተረትንም ሆነ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ወዲያውኑ ማካሄድን ያካተተ አልነበረም። የተፈለገው የሳሊህን ምክትል ወደ ፕሬዚደንትንት አምጥቶ መቀጠል ነበር።

ይህ ከህዝቡና ከአክቲቭስቶች ፍላጎት ጋር የተቃረነና ዴሞክራሲያዊ አካሄድን የሳተ ቢሆንም በወቅቱ ያሜሪካን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምሰራቅ ሀላፊ የነበሩት ሚስተር ጀፍሪ ፌልትማን (Jeffrey Feltman, the Assistant Secretary of State for Near Eastern Affairs) ይህንኑ እቅድ እንደሚደግፉ አስታወቁ።
ያሜሪካን መንግስት የወሰደውን አቋም እንዲያስተካክል የኖቤል ሽልማት አሽናፊዋ የመናዊት ተዋኩል ካርማን (Tawakul Karman) እንዲህ ሲሉ ተማጸኑ “ዩናትድ ስቴትስ አሜሪካንን በሽብርትኛነት ላይ ያላትን ጭንቅ እንገነዘባለን። ያሜሪካን ደህንነት ለመጠበቅ ከየመን ጋር አሜሪካ ያላትን ስምምነት ማክበርን በተመለከተ ምንም ችግር የለንም። እኛ የምንጠይቀው አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት መለኪያወችን እንድትከተሉና የየመንንም ህዝብ ለነጻነት፣ ለስብአዊ መብቱና፣ ለፍትህ መስፈን ያለውን ፍላጉቱን እንድታከብሩለት ብቻ ነው። በሸዎች በሚቆጠሩ የየመን ወጣቶች ስም ከእናንተ ጋር በሙሉ ሽሪክነት አብረናችሁ ለመቆም ዝግጁነታችንን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ፡፡ ከእናንተ ጋር በጋራ፣ ሆነን ጽንፈኛነት እንዳይቀፈቀፍ አመች ሁኔታ የሚፈጥረውን መደላድሎች፣ ልማትን ተጋባራዊ በማድረግ እና ነጻ የሲቪክ ማህበራትን በመመስረት እናስወግዳለን፣፡ መረጋጋትንም እውን እናደረጋለን። ለዚህም ለውጥ ፈላጊወችን እንድትደግፉና ከሽብርተኞች ይልቅ ንጹሀን የመናውያንን የሚገድለውን ስርአት መደገፍ እንድታቆሙ እማጸናለሁ”፡፡

ያም ሆኖ ግን ሰሚ አላገኙም። በወቅቱ የለውጥ ፈላጊዎቹ ወጣቶች መሪ ከነበሩት ውስጥ አንዱ ኻሊድ አለ አኒስ (Khaled al-Anesi) ትግላችን እና አብዮቱ ከጀርባ ነው በጩቤ የተወጋው ነበር ያለው “This revolution has been stabbed in the back.”
ባሜሪካን ነዋሪ የሆኑ ትውልደ የመኖችም ተመሳሳይ የለውጥ ፍላጎታቸውን ለአሜሪካ ባለስልጣናት አሰምተው ነበር።
አብዱላሂ ሳላሀ አርፈውበት በነበረው በኒውዮርክ ሪትዝ ካርልተን (Ritz-Carlton ) ሆቴል ፌት ለፌት የተቃውሞ ስልፍ ካካሄዱት ውስጥ ጥቂቶቹ (ፎቶ ከኒው ዮርክ ታይምስ 2012)
አብዱላሂ ሳላሀ አርፈውበት በነበረው በኒውዮርክ ሪትዝ ካርልተን (Ritz-Carlton ) ሆቴል ፌት ለፌት የተቃውሞ ስልፍ ካካሄዱት ውስጥ ጥቂቶቹ (ፎቶ ከኒው ዮርክ ታይምስ 2012)
ይህ ሁሉ የህዝብ ተቃውሞ እያለ በተጻራሪው መንገድ እንዲጓዝ በመደረጉ ህዝባዊ ንቅናቄው በተጀመረው መልክ ቢቀጥል የሚፈለገው ነጻነት፣ የመብት መከበር፣ ዴሞክራሲ ወዘተ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል የሚለው አመለካከት በጥርጣሬ መታየት ጀመረ። ሌሎች አማራጮችንም የመመርመር ጉዳይ ትልቅ ቦታ ያዘ።

አቡበከር አልሸማሂ የተባለ አንድ በትውልደ የመናዊ የሆነ እንግሊዛዊ ጋዜጠኛ የምእራቡ አለም የስርአት ለውጥ እና የዴሞክራሲ እንቅስቃሴውን በመደገፍ በዋናነት የሚፈሩትን አላቃይዳን ለማዳከም እንደሚቻል ይህ ሳይሀን ቢቀር ግን ቀጣዩ ሁኔታ ለየመንም ላካባቢውም መልካም ነገርን እንደማያመጣ ልብ ያለው ልብ ይበል ሲል የማስጠንቀቂያ ደወል አስምቶ ነበር
የዚህ ወጣት ጥሪ፣ የኖቤል ሽልማት ተሸላሚዋ፣ የተቃዋሚ ፖለቲከኞች ህብረትም ሆነ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ድምጽ ግን አድማጭ አላገኘም። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ነው አልቃይዳና ሌሎችም ኃይሎች “ብለናችሁ ነበር፣ የምንፈልገውን ለማገኝት የራሳችንን ጉዞ መጀመር ነው የሚያዋጣን” በማለት ወጣቱን ከሰላማዊ የትግል ጎዳናው ወጥቶ ለሚፈልጉት ግብ እንዲሰለፍ ሰፊ የመመልመያ መሳሪያ ያገኙት።

የየመን ህዝባዊ ትግል መደናቀፍና ለየት ያለ ተቃውሞው መበራከት

የዴሞክራቲክ ሂደቱ መደናቀፍ የሳላሀ መንግስት ደጋፊወች፣ ምእራባውያንና የገልፍ መንግስታት እንደተመኝት ሳይሆን ለገዢው ፓርቲ መንኮታኮት ለፕሬዚደንቱ ስደት፣ በየመን ውስጥ ላክራሪዎችና ለቀጣይ ምስቅልቅል የተመቻቸ ሁኔታን ነው የፈጠረው።
በቅርቡ የቀረበ ጥናት እንዳሳየውም፣ ሀገሪቱ ምስቅልቅል ውስጥ መግባት አልቃይዳን ተጠቃሚ አድርጎታል።
ባሜሪካን ጸረሽብር ሀይሎች እና በሰው አልባ አይሮፕላን ጥቃት በተከታታይ በደረሰበት ጥቃት እጅግ ተዳክሞ የነበረው አልቃይዳ በ ኤፕሪል 2015 ሙላካ (Mukallah) በተሰኘችው ከተማ የሚገኝ እስር ቤት ሰብሮ በመግባት በመቶዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቹን አስለቅቋል። በመቀጠልም በከተማዋ ዙሪያ የሚገኙ አምስት ኬላዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል
የሀሽድ (Hashid) ጎሳ ተዋጊወች በሰንአ (Sanaa) ከተማ ውስጥ ጎዳናወችን ሲቆጣጠሩ (ፎቶ በ ካሊድ አብደላሂ፣ ሮይተር፣ ዲሰምበር 2011)
የሀሽድ (Hashid) ጎሳ ተዋጊወች በሰንአ (Sanaa) ከተማ ውስጥ ጎዳናወችን ሲቆጣጠሩ (ፎቶ በ ካሊድ አብደላሂ፣ ሮይተር፣ ዲሰምበር 2011)
በኤፕሪል 17፣ 2015 እንደተዘገበውም፣ በሀገሪቱ ምስራቃዊ ግዛት የሚገኝ የመንግስት ኃይል አሸንፎ፣ እጅግ ሰፊ የሆነ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ተቆጣጥሯል።

መሰረቱን ጎሳ ያደረገው የየመን ፖለቲካ አሁንም ተጠናክሮ ሀገሪቱን ወደተወሳሰበ አሳዛኝ ክፍፍል ይዟት በመጓዝ ላይ ይገኛል።አሊ ሳላህን፣ የተኳቸው ፕሬዚደንት ሃዲና ፓርቲያቸው ከስልጣን ተባረው እነሆ ዛሬ የስደት ፕሬዚደንት ሆነዋል።
አፍቃሪ ኢራን የሆኑት የሁቴ አማጽያን ሰንአ (Sanaa) ከተማን ከተቆጣጠሩ በሐላ በሳውዲ አረቢያ የሚመራውና ባሜሪካ የሚደረፈው የአየር ጥቃት  እንደማይበግራቸው በሰልፍ ሲገልጽ ( ፎቶ በሀና ሞመመድ፣ ዐሶሽየትድ ፐረስ 2015)
አፍቃሪ ኢራን የሆኑት የሁቴ አማጽያን ሰንአ (Sanaa) ከተማን ከተቆጣጠሩ በሐላ በሳውዲ አረቢያ የሚመራውና ባሜሪካ የሚደረፈው የአየር ጥቃት እንደማይበግራቸው በሰልፍ ሲገልጽ (ፎቶ በሀና ሞመመድ፣ ዐሶሽየትድ ፐረስ 2015)
ባጠቃላይ የፕሬዚደንት አሊ ሳላህ መንግስት የዲሞክራሲ እንቅስቃሴውን ለማጨናገፍ ቀና ደፋ ሲል እና ባለው ኃይል ሁሉ ሲሯሯጥ አልቃይዳ፣ የሁቲ አካራሪዎችና ሌሎችም ጎሳ ነክ ኃይሎች እጅግ ተጠናከሩ። የፕሬዚደንቱ የስልጣን ጥም፣ ግትርነትና እኔ ያልኩት ብቻ ካልሆነ ብሎ ድርቅ ማለት መጨረሻው የዴሞክራሲያዊ ኃይሎች መዳከም፣ የስርአቱ ሀገሪቱን ሊገዛ አለመቻል፣ የሀገሪቱ አንድነት መናጋት፤ የአልቃይዳ መጠናከር፣ የተገንጣዮች እንቅስቃሴ መጠናከር፣ ሀገሪቱ የሰፊ ጦርነት አውድማ መሆን እና ከራሷም አልፋ ላካባቢው ሁሉ አደጋን መጋረጧ ጥቂቶቹ ናቸው።

እኛስ?

የየመን ሁኔታ የህዝብን መብት ረግጦ፣ ሌሎችን አግልሎ፣ ተለጣፊ ድርጅቶችን ሰብስቦ መግዛት ይዋል ይደር አንጂ በዘላቂነት ሊቀጥል እንደማይችል በርግጠኛነት ያሳያል። የውጭ መንግስታት ድጋፍ፤ ጊዚያዊ ጥንካሬን አንጂ ዘለቄታ ያለው በህዝብ ዘንድ ከበሬታን እና ፍቅርን ሊያሰገኝ እንደማይችልም ያመለክታል፡ በጎሳ ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ መዘዙ እጅግ ሰፊ እንደሆነም ያሳያል።
በሀገራችን ፖለቲካ መድረኩን ለብቻ ሙጭጭ ብሎ መያዙ፤ የመብት ረገጣው፣ ህዝብን ተስፋ የሚሰጥ ሁኔታ እየተሟጠጠ መምጣቱን ከገዥው ወያኔ/ኢህአዴግ በስተቀር የሚክድ የለም። በሀገሪቱ ውስጥ የሚታየው ውጥረትም የተለያየ መልክ እየያዘ፣ እጅግ እየተካረረ እንጂ እየረገበ መፍትሄም እያገኘ አይደለም የመጣው።

በገዥው ቡድን በህጋዊነት የሚንቀሳቀሱትን ፖለቲካ ድረጅቶችንም ሆነ የሲቪክ ድርጅቶች ሰበብ እየፈለገ በፍጹም እነዳይንቀሳቀሱ እያደረገ ስለመጣ፤ በዚች ሀገር ውስጥ በዚህ ስርአት ውስጥ መብትን በህግ ስር ሆኖ ለማስከበር መሞከር ከንቱ ሙከራ ነው የሚለው ስሜት እጅግ ፈጣን በሆነ መልክ እየተስፋፋ ይገኛል።

የምእራብ መንግስታትን በተመለከተም በኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት ታላቅ ድጋፍ ሊያበረክቱ እንደሚችሉ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በተግባር እንደታየው ግን ዴሞክራሲን፣ እኩልነትን፣ ፍትህን ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ ለእነርሱ በዋነኛነት ቅድሚያ የሚሰጡት እንዳልሆነ ነው።

ሀገራችን ሁሉን አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ከሚፈልጉ ጀምሮ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር መቀጠል የለባትም እስከሚሉ ድርጅቶች የተለያየ አይነት ትግል በውስጥም በውጭም የሚያካሂዱባት ሀገር ነች። የጎሳ መርዝ እጅግ ስር ሰዷል፡ በሰራዊቱም በፖሊሱም ውስጥ የጎሳ ቅኝት ሰፊ ነው። ከዚህ ሁሉ በተጨማሪ እንደሻቢያ ያሉ እና ሌሎችም ጠላቶች ኢትዮጵያን ከበዋት ይገኛሉ። በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አልቃይዳ፣ አሁን ደግሞ ኢሰላሚክ ስቴት በአይነ ቁራኛ ከሚያዩዋቸው ሀገሮች አንዷ ለመሆኗ በየጊዜው በአልሸባብ የተነገረውን እና በኤፕሪል ወር ደግሞ በሊቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመውን አንገት መቅላት እና በጥይት ደብድቦ መግደል ማገናዘቡ ይበቃል።
የየመን ምስቅልቅል ሰለባ፤ በደም የተነከረ የወገኑን ልብስ ሲያሳይ (ፎቶ በ ቢቢሲ አፕሪል 2015)
የየመን ምስቅልቅል ሰለባ፤ በደም የተነከረ የወገኑን ልብስ ሲያሳይ (ፎቶ በ ቢቢሲ አፕሪል 2015)

ይህ ሁሉ የሀገራችንን አደጋ እጅግ ሰፊና ውስብስብ እንደሆነ ያሳያል። በሀገሪቱ የሚታየው ውጥረት ገንፍሎ እንደሚፈነዳ በርግጠኛነት መናገር ይቻላል፤ ጥያቄው መቼ እና በምን መልክ የሚለው ብቻ ይሆናል።
በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሊፈጠሩ የሚችሉትን አደጋዎች ለማስወገድ ካልተቻለም ለመቀነስ ምን መደረግ አለበት የሚለው እጅግ አስቸኳይ መፍትሄን የሚሻ ሁሉንም ሊያስጨንቅ ሊያስጠብብ የሚገባ ጉዳይ ነው።

ማጠቃለያ

ኢትዮጵያ የሁሉም ዜጎቿ ሀገር ነች። ለኢትዮጵያ አንድነት አንድ ድርጅት ብቻ ሳይሆን እጅግ ብዙ ዜጎች ያሰባሉ፡ ለብሄር ብሄረሰቦችም እኩልነት እንዲሁ። በዚህ አኳያ የሁሉም አመለካከከት በክብር ሊስተናደግ የሚችልበት በጠንካራ እሴቶቻችን ላይ በማተኮር በኢትዮጵያዊነት በጋራ የመኩራት ሂደት ተጠናክሮ የሚወጣበትን መደላድል መፍጠር ግድ ይላል።
የተለያዩ ቅሬታዎችና አዳዲስ አመለካከቶች በሰላማዊ መንገድ በሙሉ ቅንነት ሊስተናገዱ የሚችሉበት መድረክ ሊፈጠር ይገባል። ወጣቶች፣ አዛውንቶች፣ የተማረ፣ ያልተማረ፣ ሁሉም ዜጎች ሀገራቸውን ጥለው በባሌም በቦሌም እንዲሰደዱ የሚያደርጓቸው የፍትህ መጥፋት፣ የህግ የበላይነት መጥፋት፣ የተስፋ ማጣት ወዘተ ሁኔታዎች ሊስተካከሉ የሚችሉበት ስርአት እውን መሆን አለበት። ለዚህም ችግሩን በጋራ በቅንነት ለመፍታት በቁርጠኛነት መነሳት ያሰፈልጋል።

የፖለቲካ ድርጅቶች የማምንበትን ራእይ ተግባራዊ ለማድረግ ከውጭ ጠላትም ጋር ቢሆን እሰለፋለሁ የሚያሰኛቸው የፖለቲካ ድባብ እንዲወገድ የሚያስችል መተማመን፣ መፈጠር ይኖርበታል። በስልጣን ላይ ያሉ ፖለቲካ መሪዎች መጨረሻቸው፣ እስርቤት፣ ስደት ወይም ክብር የሌለው ሞት የሆነበትን ስርአት እንዲያከትም ማድረግ የግድ ነው። በምትኩም በፖለቲካ ራእይ ልዩነት የተነሳ እንደጠላት መተያየት የሚወገድበትን መሰረት መጣል፣ ያመጽ አዙሪትን መሰረት ማፍረስ ያሰፈልጋል። ለዚህም አሳታፊ፣ እውነተኛ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ስርአት መስረት መጣል የግድ ይላል።

ባለንብረቶች አንዱ ፖለቲካ ፓርቲ ከስልጣን ሲወርድ ንብረታቸው የሚነጠቅበት፣ የጦር መኮንኖች እና ሌሎች ባለስልጣኖች የውርደት ኑሮ እንዲኖሩ የሚገደዱበት ስርአት ማብቃት አለበት።
ይህንን ለማድረግ ደግሞ መመካከር የግድ ነው፡፡ የተቃዋሚው ባስቸኳይ ማበር አስፈላጊ ነው። የብሄራዊ መግባባትና እርቅ መሰረትን መጣል የግድ ነው። የዚህ ጉዳይ ተግባራዊ መሆን የረፈደ ቢመስልም እጅግ ሳይዘገይ አሁኑኑ ሊሆን ይገባዋል።
የኢትዮጵያ ወዳጅ የሆኑ መንግስታትም ሆኑ በዚች ሀገር ደህንነት ተጠቃሚ ነን የሚሉ ሁሉ ለዚህ ተግባር መደናቀፍ ሳይሆን መሳካት ነው ድጋፍ ሊሰጡ የሚገባው። የነርሱም ጥቅም በዘላቂነት የሚጠበቀው በተረጋጋ፣ ህግ በሰፈነበት፣ መብት በተረጋገጠበት መቻቻልና ነጻነት በሰፈነበት ስርአት ውስጥ ብቻ እንደሆነ የመን ምስክር ነች።

ቀደም ብየ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ የጠቀስኩት አቡበከር አልሸማሂ የተባለው የየመን ትውልድ ያለው እንግሊዛዊ ወጣት በ 2011 ሀገሩን በተመለከተ ካሰማውን የአደጋ ደውል እና ካቀረበው ጥሪ ጋር የሚመሳሰል መልእክት እኔም ለማሰማት እፈልጋለሁ።
የኢትዮጵያ ሁኔታ እጅግ አሳሰቢያ እጅግ ፈታኛና አጣዳፊ መፍትሄን የሚሻ ነው። በሀገሪቱ ላይ ጥቁር ደመና አንዣቧል። ጭንቀት ሰፍኗል። ውጥረት በዝቷል። ተስፋ ማጣት ተስፋፍቷል። አሁንም ቢሆን ይህን ጭንቅ ለማስወገድ አደጋውን ለማስወገድ የተወሰነ እድል አለ፡፡ ይህ ደግሞ ደፈር ያለ አዲስ እርምጃን ይጠይቃል። ይህን እውነታ በመካድ ወይም በማድበስበስ ለማለፍ መሞከር ለኢትዮጵያም ለአካባቢውም መልካም ነገርን እንደማያመጣ ልብ ያለው ልብ ይበል።

ሜይ 5፣ 2015
ላስተያየት ethioandenet@bell.net

http://www.goolgule.com/lessons-from-yemen-to-mitigate-conflict-in-ethiopia/

Wednesday, April 8, 2015

በስዊድን የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር ራሱን አስተዋወቀ

semayawi sweden
የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር በስዊድን ተመስርቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በመግለጽ፤ የድጋፍ ማኅበሩ ቅዳሜ አፕሪል 4 ቀን 2015 ዓ.ም. (ግንቦት 26 ቀን 2007 ዓ.ም.) ራሱን አስተዋውቋል። በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ዓላማና ተግባርን ጥሪ ለተደረገላቸው ተሰብሳቢዎች ያስረዱት አቶ ሰለሞን ጌታነህ የድጋፍ ማኅበሩ ሰብሳቢ ናቸው።
አቶ ሰለሞን በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በተደረገው የማስተዋወቁ ሥነሥርዓት ላይ ስለሰማያዊ ፓርቲ ሲያስረዱ፤ ሰማያዊ ፓርቲ በወጣት አባላት የተመሰረተና የሚመራ መሆኑን ገልጸው፤ ወጣቱ ደግሞ ከኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት ብልጫ ያለው እንደሆነና የወጣቱም ድጋፍ ሰማያዊ ፓርቲን እንዳልተለየው አሳውቀዋል። አያይዘውም ሰማያዊ ፓርቲ የዓላማ ጽናቱ የበረታ በመሆኑና በሀገር ውስጥ የሚያደርገውም እንቅስቃሴ እጅግ የጎላ ስለሆነ ፓርቲውን ሁላችንም መደገፍ ይገባናል ብለዋል።
የፓርቲው አመራሮች
የፓርቲው አመራሮች
በስብሰባው ላይ የተገኙት ኢትዮጵያውያን መግለጫውን ከሰሙ በኋላ ልዩ ልዩ ገንቢ ሃሳቦችን ሰጥተዋል። ተሰብሳቢዎቹ ለፓርቲው ከሰጡት ሃሳቦች ውስጥ፣ “ሰማያዊ ፓርቲ በሀገር ቤት እንደሚያደርገው ሁሉ በዚህም የድጋፍ ማኅበሩ ከሌሎች የሰላማዊ ትግል ከሚያራምዱ ፓርቲዎች ጋር በመገናኘት ራሱን ማዳበር ይገባዋል” የሚለው ይገኝበታል።
ተሰብሳቢዎቹ የመጀመሪያ ጥሪ መሆኑን አስታውሰው በዕለቱ የተገኘው የህዝበ ቁጥር አነስተኛ ነው ተብሎ እንደማይገመት በመግለጽ፣ “ፓርቲው የበለጠ በሰራ ቁጥር ብዙ አባላትና ደጋፊ ማፍራት እንደምትችሉ ካለው ሁኔታ መረዳት ይችላል” በማለት አስተያየት ሰጥተዋል። ስብሰባውን ለመዘገብ በስፍራው የነበረው የኢትዮጵያ ዛሬ ዘጋቢ አብዛኞቹ ተሰብሳቢዎች የነቃ ተሳትፎ ሲያደርጉ እንደነበር ገልጽዋል።
ቀጥሎም ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ዓላማና ሥራ የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ለተሰብሳቢው ቀርቧል። በመጨረሻም የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በስልክ ቀርበው ሰብሳቢዎቹንና ተሰብሳቢውን በማመስገን በሀገር ቤት ያለውን ችግር አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አመላክተው፤ በአሁኑ ጊዜ በፓርቲያቸው አባላትና በሳቸውም ላይ እየተፈጸመ ያለው በደል የበረታ መሆኑን ገልጸዋል። ነገር ግን ከዚህ የከፋ ችግር ሊገጥመን ቢችልም ፓርቲዬም ሆነ እኔ በጽናት ቆመን ትግሉን እንገፋለን በማለት ያላቸውን ቁርጠኝነት አስረድተዋል። ከኢንጂነር ይልቃል አጭር የስልክ መልክት በኋላ ስብሰባው ተጠናቋል። 

(ዘጋቢ: ወለላዬ ከስዊድን)

http://www.goolgule.com/semayawi-party-support-group-introduced-in-sweden/

የት ሂዱ ነው?

"ኑሮዬም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም እዚሁ ነው፤ ከኢትዮጵያ አፈር የሚለየኝ የለም"
Prof_Mesfin1
ዓለም ሁሉ ጠላን፤ በየትም አገር እየሄድን “የሙጢኝ!” ከራሳችን መሬት በጉልበት እየተነቀልን፣ ከራሳችን ቤት እየተባረርን፤ ከተወለድንበትና ከአደግንበት አካባቢ እየተፈናቀልን፣ ጭራውን ቆልምሞ እንደሚሮጥ ባለቤቱ እንዳባረረው ውሻ በአገኘነው አቅጣጫ እየሮጥን፣ እጃችንን እያርገበገብን “የሙጢኝ!” እንላለን፤ የፈራነውን ሞት በየመንገዱ እናገኘዋለን፤ ሞትን ሸሽተን ሞት ያጋጥመናል፤ የሞቱ ልዩነት አይታየንም፤ በየመንገዱ የሚያጋጥመው ሞት የውርደት ሞት ነው፤ የብቸኛነት ሞት ነው፤ ዘመድ-ወዳጅ ለቀብር የማይገኝበት ሞት ነው፤ ሠለስት፣ አርባ፣ ሙታመት የማይወጣበት ሞት ነው፤ ባዕድ ምስጥ ያላሳደገውን አካል የሚበላበት ነው፤ የሞት ሞት ነው፡፡
ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ከአገር አስወጥቶ ባዶ መሬት ብቻ ይፈልግ ይመስል የወያኔ ሎሌዎች በማስፈራራት ሁሉም አገሩን እየተወላቸው እንዲሄድ ያቀዱ ይመስላል፤ ጥንት ኢሰመጉ በምሠራበት ጊዜ በየጊዜው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሰዎችን በማስፈራራት ሰላማቸውን ለመረበሽ ወደስደት ወይም ወደወንጀል ተግባር የሚመሩ የወያኔ አባሎች ነበሩ፤ አሁን እንደገና ብቅ ማለት ጀምረዋል፤ ሕጋዊ ሥርዓት እየላላ ጉልበተኞች በግላቸው ለዘረፋና ለቅሚያ እየተሰማሩ ይመስላል፡፡
ስለራሴ ላውራ፤ ከእኔ የሚፈልጉት ምን እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም፤ የሚፈልጉት የምኖርበትን አፓርትመንት እንደሆነም አላውቅም፤ በእኔ ቤት ያለ ሀብት የሚባል ለወያኔ አገልጋዮች የሚጠቅም ሁለት የገብረ ክርስቶስ ስዕሎች ብቻ ናቸው፤ (በዚህ አጋጣሚ እነዚህን ስዕሎች ለመግዛት የሚፈልግ ያነጋግረኝ)፤ ከዚህ ሌላ ለወያኔ ዋጋ የሌላቸው መጻሕፍት ናቸው፤ ስለዚህም አሁን በእኔ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት እኔን ወደስደት ለመግፋት የሚደረግ ሙከራ ይሆናል፤ በ1992 ግድም ተሞክሮ ነበር፤ አልሠራም፤ ዛሬ ይበልጥ አይሠራም፤ ለማናቸውም ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ባልችልም በእኔ ላይ ዘመቻ መጀመሩን አንድ በቅርብ ከማውቀው ወያኔ በትክክል ተረድቻለሁ፤ ይህንን ዘመቻ በመምራት ላይ ያለውንም ሰው ማንነት ተነግሮኛል፡፡
ይህ አገር የአንድ ጉልበተኛ ቡድን ነው ብዬ አልቀበልም፤ የአባቶቼና የእናቶቼ፣ የአያቶቼና የቅድማያቶቼ አጥንትና ደም የገነባው አገር ነው፤ ማንም ለስደት አይዳርገኝም፤ ማንም አስፈራርቶ ኢትዮጵያዊነት መብቴን መግፈፍ አይችልም፤ አልፈቅድለትም፤ በግልጽ በማያጠራጥር ቋንቋ ኑሮዬም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም እዚሁ ነው፤ ከኢትዮጵያ አፈር የሚለየኝ የለም፡፡
እኔን ለማጥቃት ላሰፈሰፉት ወያኔዎችና ሎሌዎቻቸው አንድ እውነት ልንገራቸው፤– በፈለጉትና በተመቻቸው መንገድ በእኔ ላይ በጉልበታቸው ግፍ ቢፈጽሙ ነገ በነሱ ላይ የባሰ ግፍ እንደሚደርስባቸው ይወቁት፤ ሁልጊዜም ከሕግ የወጣ ጉልበተኛነት ጉልበተኛነትን ያነግሣል፤ በመግደል ድል ይገኛል ብለው የሚያምኑ ወያኔዎች ትንሽ ቆም ብለው ያስቡ፤ በመሞትም ድል ይገኛል፤ በመሞትም ማሸነፍ ይቻላል፡፡
በእኔ ላይ የዘመተው ወያኔ ወይም ሎሌ ማናቸውም ሥራ ውጤት እንዳለው ማወቅ አለበት፤ አንድ ነገር አድርጎ ምንም ዓይነት ውጤት አያስከትልም ብሎ ማሰብ ድንቁርና ነው፤ ይህ የሳይንስ ሕግ ነው፤ For every action there is a reaction ይላል!
ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

http://www.goolgule.com/i-live-and-die-here-in-my-own-home-land/

Wednesday, March 11, 2015

የወያኔ ጥላቻ ፍሬ (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም
ወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ ሲሰይመው፣ በአዲስ አበባ የተሠራውን መንደር መቀሌ ብሎ ሲሰይመው እየመሰከረ ነው፤‹‹የለሁበትም!›› እያለ ነው።Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
የትግራይ ሕዝብ መደህየቱ አልበቃ ብሎት ሲለምንም እየተሳቀቀ ነው፤ የሚለምነው ትግሬ ለብዙ ሰዎች ትግሬና ወያኔ አንድ መስሎ እንደሚታየው ያውቃል፤ አብዛኛው ሰው በወያኔ ላይ ያለውን ስሜት ያውቃል፤ ስለዚህም ሲለምን ሰዎች በወያኔ ላይ ያላቸውን ስሜት ስለሚያራግፉበት እየተሸማቀቀ ነው፤ አንድ የትግራይ ቄስ ከአርሲ ነኝ አሉኝና ለምን እውነቱን አይናገሩም ስላቸው እውነቱን ስናገር የማገኘው ስድብ ብቻ ነው አሉኝ፤ እኒህ ሰው ምን በወጣቸው የወያኔን ኃጢአት ተሸካሚ ይሆናሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በትግሬነቱ የተጠቀመ አለ፤ እኔ የማውቀው የደርግ ወታደር የነበረ ትግሬ ቆስሎ ከውትድርና ወጣና በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የጥበቃ ሥራ ላይ ነበር፤ በጣም ይቸግረው ነበር፤ ሚስቱ ሕመምተኛ ነበረች፤ የቤት ኪራይ መክፈል ይቸገር ነበር፤ ዛሬ ግን የሚለብሰው ልብስ ሌላ ነው፤ ከኑሮውም ተርፎ ለሲጃራና ለጫት እያወጣ ነው፤ ወይም ሌሎች እያወጡለት ነው፤ ትግሬነታቸው ብቻ እንዲህ የደላቸው በጣም፣ በጣም ጥቂቶች ናቸው፤ ስለዚህም በወያኔ አገዛዝ ትግሬ ሁሉ ተጠቅሞአል ማለት ከጉልሁ እውነት ጋር የሚጋጭ ስሕተት ነው፤ አብርሃ ሰዎች ትግሬ ሁሉ ተጠቃሚ ሆኗል ሲሉ ‹‹ያመኛል›› ማለቱ ይገባኛል።
ወያኔ ትግሬ በመሆኑ ብቻ ትግሬ ሁሉ ዕዳ አለበት ማለት እንደወያኔ ማሰብ ነው፤ ወንጀል በዘር አይተላለፍም፤ እያንዳንዱ ሰው ለሠራው ሥራ ሁሉ ኃላፊነትን ይወስዳል፤ ጊዜው ሲደርስ ውጤቱንም ለመቀበል ይገደዳል፤ ይህ የሚሆነው ሰው ሁሉ በመንፈሳዊ ኃይል በጎ መንፈስ አድሮበት፣ አእምሮው በትምህርት ተገርቶ በትክክል ማሰብ ሲችል ነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን በአለበት ሁኔታ በጎ መንፈስ የራቀው ይመስላል፤ አእምሮም ጭራሹኑ በእኩይ መንፈስና በጥላቻ እየዛገ ነው፤ ስለዚህ ያስፈራል፤ በደቡብ ሱዳን ሁለት መቶ ሰዎች በዘር ተለይተው ታረዱ ሲባል ያስፈራል፤ በናይጂርያ፣ በኮንጎ የሚካሄደውን የዘርና የሃይማኖት እልቂት ስንሰማ ያስፈራል፤ በ1997 ዓ.ም. መለስ ዜናዊና አዲሱ ለገሰ እንዳስታወሱን የሩዋንዳ የጎሣ እልቂት በብዙ ሰዎች አእምሮ ውስጥ አለ፤ የቅርብ ተኳሽ የሆነው የአግዓዚ ጦርም አድፍጦ መጠበቅ ያስፈራል፤ ሌላውም ይህንን አውቆ አድፍጦ መጠበቁ ያስፈራል፤ ሰማይ ጠቀስ የሠሩት፣ የሥልጣን ኃላፊነትን ችላ ብለው በሥልጣን የሚነግዱና የሚከብሩት፣ የማይኖሩበትን ሕንጻ የሚክቡት፣ ከሕዝብ ጋር ያላቸው የአይጥና የድመት ኑሮ ያስፈራል፤ አቶ አስገደ ወያኔ መደንገጡን ይነግረናል፤ መደንገጥ የማይቆጣጠሩት ፍርሃት ነውና አደጋ ያመጣል፤ አደጋው አደጋን ይጠራል፤ ይህም ያስፈራል።
በትግራይ ዙሪያ ያለው ምንድን ነው? የትግራይ ሕዝብ በየትኛው አቅጣጫ ነው አንደልቡ እየተዘዋወረ ለመሥራትና ለመኖር የሚችለው? ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከሰሜን ከወገኑ ከኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም አቃብቶታል፤ በደቡብ-ምሥራቅ ከወሎ መሬት ቆርሶ የወሎን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ በደቡብ-ምዕራብ ከጎንደር መሬት ቆርሶ የጎንደርን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ የራስን ወገኖች አስቀይሞ ሱዳንን በመሬት ለመደለል የሚደረገው ጥረት ሁሉ ፋይዳ የለውም፤ ሱዳን ለራሱም ያልበጀ አገር መሆኑ እየታየ ነው፤ ወደፊት ደግሞ ይበልጥ ይታያል፤ በትግራይ ውስጥ ደግሞ ወያኔ የፈጠረው አፓርቴይድ የወያኔን የኑሮ ደረጃ ወደሰማይ ሲያስጠጋው፣ የቀረውን ወደአንጦርጦስ የደሀነት ገደል ውስጥ ከቶታል፤ በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ ከተማ ከነልጆቻቸው እየተዘዋወሩ የሚለምኑ ሞልተዋል፤ ይህ ልመናም ለወያኔ ለመገበር ነው፤ ብዙዎቹ እንደሚናገሩት የሚለምኑት የማዳበሪያ ዕዳቸውን ለወያኔ ለመክፈል ነው።
ወያኔ ከሀያ ዓመታት በላይ አፍንጫ እየያዘ ያስከፈለውን የሚመልስበት ጊዜ እየተቃረበ ነው፤ ጥያቄው ወያኔ እንዲመልስ የሚገደደው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ጥላቻ ወደንዴት፣ ንዴት ወደቁጣ ተለውጦ ሲገነፍል ምጽዓት ደረሰ ማለት ነው፤ ሁሉም ሰው ራቁቱን ይሆናል፤ አንደአውሬ ከጥፍሩና ከጥርሱ በቀር ሌላ መሣሪያ አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ በክፋት ወደአውሬነት ይለወጣል፤ ጠመንጃና ቦምብ አያገለግሉም፤ ሕንጻው ምሽግ አይሆንም፤ መኪናው፣ ባቡሩ፣ ታንኩ ከቆመበት አይነቃነቅም፤ የትም አያደርስም፤ ጭፍራ ሁሉ በየራሱ ፍዳ ታንቆ እንኳን ለሌላ ሊተርፍ ለራሱም የማይበቃ ይሆናል፤ ለነገሩ ጌታና ሎሌም የለም፤ ሁሉም በአውሬ እኩልነት የተፋጠጠ ነው፤ ርኅራኄ ተሟጦ፣ መግል ያዘለ ልብ ፈርጦ፣ ውይይትና ክርክር አብቅቶ፣ ጥርሱን ያገጠጠና ጥፍሩን የሳለ መንጋ በደም የሚራጭበት ሁኔታ ነው።
ሌላ አገር እንዲህ አልሆነም፤ እዚያ አገር እንዲህ አልሆነም፤ የሚባል ነገር የለም፤ እኛ ዘንድ ሌላ ነው፤ የኢትዮጵያ ደሀዎች እንባ የእግዚአብሔርን ሰማይ አጨቀየው!
ክፋት እንደ እሳት ይቃጠላል፤ ኵርንችቱንና እሾሁን ይበላል፤ ጭፍቅ የሆነውንም ዱር ያቃጥላል፤ ጢሱም ተትጐልጕሎ እንደ ዓምድ ይወጣል፤በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ቁጣም ድር ተቃጥላለች፤ ሕዝቡም እሳትእንደሚበላው እንጨት ሆኖአል፤ ሰውም ለወንድሙ አይራራም፤ ሰው በቀኙ በኩልይነቅላል፤ ይራብማል፤ በግራም በኩል ይበላል፤ አይጠግብምም፤ እያንዳንዱምየ ክንዱን ሥጋ ይበላል፤ ምናሴ ኤፍሬምን፣ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላል፤ …ኢሳይያስ 9/18-21
ትንቢተ ኢሳይያስ ለሩዋንዳውያን ብቻ አይደለም፤ ጥላቻና ክፋት በተዘራበት ቦታ ሁሉ ውጤቱ ጥፋት ነው፤ ምናሴ ኤፍሬምን በልቶ አይቀርም፤ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላዋል።
http://ecadforum.com/Amharic/archives/14596/

Wednesday, February 25, 2015

ሳይገባቸው ቻይና በነገራቸው የሚያውቁትን የሚረሱ ማን ያስተምራቸው!

ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም

haile china



የጎረቤት ኬንያ ዳኛ ለኬንያ መንግሥት አስፈጻሚው ክፍል ልኩን ነገረው፤ ሕገ መንግሥቱን በመርፌ አስተኝተህ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር ሕግ ለማውጣት አትችልም፤ ስለዚህም የሰነዘርኸውን የጉልበት ሕግ አንሣ፤ አለው፤ ዳኛ አይጥፋ! ሌላ ቢቀር ከጎረቤት ዳኝነትን እንስማ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር ስንት ጋዜጠኛ፣ ስንት የሃይማኖትና ስንት የፖሊቲካ መሪዎች ከየወህኒ ቤቱ ይወጡ ነበር! ሁላችንም እንደልባችን ሳንፈራ፣ ሳንፈራራ በሙሉ ነጻነት ችግሮቻችንን የወያኔን ጭቆና ጨምሮ ለመወያየትና መፍትሔዎችን ለመለዋወጥ የምንችልበት መድረክ፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ራድዮና ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ ውስጥ ይኖረን ነበር፤ ስንት ሰው ሥራ ያገኝ ነበር፡፡
ከሁሉም በላይ በየመንገዱ ጠመንጃ የያዘ ሊያስፈራራን የሚሞክር ሆድአደር እያየን፣ እንደዚሁም በየጫካው ያሉትን እያሰብን ሰላማችንን ከምናጣ አበባውን ትተን፣ ሩዙን ትተን፣ የተወደደልንን ጤፋችንን እያመረትን አዲስ ኑሮ ብንጀምር የተሻለ ነበር፡፡
ግን አንድ እንቅፋት አለብን፤ እነዚህ ከየኪዮስኩ እውቀት ገዝተን አዋቂዎች ሆነናል የሚሉት እንትኖች መጀመሪያ ችግሩ እንዲገባቸው፣ ሁለተኛ መፍትሔው እንዲገባቸው፣ ሦስተኛ ጉልበትና እውቀት አንድ አለመሆናቸውን ብቻ ሳይሆን በጉልበት እውቀት የማይገኝ መሆኑን ማሳመን በረዶ እየወረደ የስሜን ተራራን መውጣት ነው፤ በረዶ ሳይኖር ወጥቼዋለሁ!
እነዚህን የጉልበት አዋቂዎች — ስለሽማግሌዎችና አሮጊቶች ሳያስቡ፣ ስለመብራት ኃይል ሳያስቡ፣ ስለውሀ ሳያስቡ ሁሉም በጉልበት ፎቅ ይውጣ የሚሉ! ይባስ ብለው ለእስረኛውም ፎቅ እየሠሩለት ውጣ! ሊሉት ነው!
እነዚህ የጉልበት አዋቂዎች የአበሻ ኑሮ፣ ቡናው፣ ሙቀጫው፣ ምጣዱ፣ በርበሬው፣ ቁሌቱ፣ ቄጤማው፣ ዶሮና በግ ማረዱ፣ ኧረ ስንቱ! ሳይገባቸው ቻይና በነገራቸው የሚያውቁትን የሚረሱ ማን ያስተምራቸው! እናውቃለን ስለሚሉ እንዴትስ ይማራሉ? በእውነት ለመማር ቢፈልጉስ ስንት ዓመት ሊያስፈልጋቸው ነው!
እግዚአብሔር እነሱንም እኛንም በምሕረቱ ይጎብኘን! የሚያስተምር ጎረቤት አያሳጣን! (ምንጭ: ከፕ/ር መስፍን ፌስቡክ ገጽ)
http://www.goolgule.com/forgetting-what-they-have-learned-and-taught-by-the-chinese/

“መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ”

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በጨለማ ቤት መታሰራቸውን አስታወቁ

dark



በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ የሚገኙት የሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀጠና/ዞን አመራሮች ለ16 ተከታታይ ቀናት በጨለማ ክፍል መታሰራቸውን ለፍርድ ቤት አስታወቁ፡፡
የካቲት 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ (የፓርቲው የጎንደር አደራጅ አቶ አግባው ሰጠኝ)፣ የአንድነት እና መኢአድ የዞን አመራሮች “መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ” እያሉ እንደሚደበድቧቸውና በጨለማ ክፍል እንዳሰሯቸው ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ አሁንም መረጃየን ሰብስቤ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ 8 ቀናት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡
ተጠርጣዎቹ በማዕከላዊ እየደረሰባቸው የሚገኘውን ሰቆቃ አስመልክተው ለፍርድ ቤት አቤት ማለታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የቀረበበትን አቤቱታ እንዲያስተካክል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በጎንደርና ጎጃም አካባቢዎች የዛሬ አራት ወር ገደማ በፖሊስ ታስረው ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ እንዲዛወሩ የተደረጉ ሲሆን፣ ጠበቃቸው በተደረገባቸው ክልከላ ምክንያት ተጠርጣሪዎቹን ካገኟቸው 2 ወር እንደሞላቸው ተናግረዋል፡፡ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አቶ አግባው ሰጠኝ እየተፈጸመበት ያለውን የመብት ጥሰት በመቃወም የርሃብ አድማ ላይ መሆኑ የታወቀ ሲሆን አድማውን ከጀመረ ሁለተኛ ቀኑ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፍርድ ቤቱ በሰጠው የጊዜ ቀጠሮ መሰረት አመራሮቹ የካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ (ነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ ገጽ)
http://www.goolgule.com/opposition-party-leaders-under-severe-interrogation-and-torture/

Monday, February 9, 2015

ዋ ለረዣዢም በቆሎዎች! (ታሪኩ አባዳማ)


ታሪኩ አባዳማ
ከ1990ዎቹ የቀዝቃዛ ጦርነት ፍፃሜ ወዲህ የአምባገነኖች ባህሪ እንኳ ተለውጦ እንደ አዲሱ ዘመን ሁሉ እነሱም ስልጣን ላይ የተቀመጡት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያውም በህዝብ ፈቃድ መሆኑን ለማሳየት ተግተው እየሰሩ ነው። በቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን ይታይ እንደነበረው አይነት ሁሉን ነገር በይፋ ጨፈላልቆ በማን አለብኝነት በብቸኛ ፓርቲ ስልጣን ላይ መቀመጥ የሌጅትመሲ ጥያቄ ከማስነሳቱም በላይ አስተማማኝ እንዳልሆነ ጠንቅቀው ተገንዝበዋል። በመሆኑም ጨካኝ አምባገነኖች ሳይቀሩ ምርጫ ሲጠሩ ፣ መድብለ ፓርቲ የፖለቲካ ስርዓት መፈጠሩንም ሲሰብኩ ማየት እና መስማት እየተለመደ ነው። ለምርጫው ሂደት ፣ ለውድድሩ ድራማ ብሎም ለማይቀረው የመጨረሻ ውጤት አዋጅ የተቀነባበረ አሰራር ቀይሰዋል።Tigray People Liberation Front Split
የምዕራቡ እና ምስራቁ ዓለም ፍጥጫ በረድ ብሎ የፖለቲካው አየር የሚነፍስበት አቀጣጫ ሲቀየር ከወጀቡ ጋር ተቀላቅሎ ከማዝገም ሌላ አማራጭ አልተገኘም። ስለሆነም ከዲሞክራሲያዊ ባህሪያት አንዱ የሆነውን ምርጫ የተቀበሉ ስልጡኖች መሆናቸውን ለለጋሽ የምዕራቡ ዓለም ለማሳየት ደፋ ቀና ብለዋል። ህዝባቸው እንደሚወዳቸው ፣ እንደሚመካባቸው እንደሚመርጣቸውም ደጋግመው ያስተጋባሉ።
አሸነፍን ያሉቱ ዘጠና ዘጠኝ በመቶ ወንበር በተቆጣጠሩበት ፓርላማ ባንድ ጀምበር ህግ አርቅቀው ያውጃሉ ፣ ህጉን ራሳቸው ይፈፅሙታል ወይንም ይጥሱታል… ተሸነፉ የተባሉት ፀባይ አሳምረው ፣ አንገት ደፍተው ካልተቀመጡ ህገ ረቂቅ ይፃፍባቸዋል… አሸባሪ ተብለው ወህኒ ይጋዛሉ… ስለዚህ አምባገነኖች ምርጫ ለመጥራት አይፈሩም ፣ አያፍሩም… እንደሚያሸንፉም አይጠራጠሩም። ምክንያቱም ድል የሚታወጀው በብቸኛው መገናኛ በራሳቸው ራዲዮና ቲቪ ነውና!!
የኢንዶኔዢያው ሱሀርቶ ፣ የዛምቢያው ካውንዳ ፣ የኬንያው ሞይ ዓለም አቀፍ ፖለቲካው ባሳደረው ግፊት ምርጫ ጠርተው ተሸንፈው ስልጣናቸውን ለተመረጡ ዜጎች አስረክበዋል ፤ የግብፁ ሙባረክ እና የቡርኪና ፋሶው ካምፓዎሬ ምርጫ መጥራት ማለት ማሸነፍ ሆኖ ስላገኙት ያለገደብ ስልጣን ላይ ለመቀመጥ የሚያስችል ህግ ከልሶ ለማርቀቅ ሲሰናዱ ህዝብ በቃ ብሎ በቁጣ አስወግዷቸዋል ፣ የዙምባቤው ሙጋቤ የዩጋንዳው ሙሰቬኒ እና ሩዋንዳው ካጋሜ ዛሬም ምርጫ እየጠሩ ተፎካካሪያቸውን በብረት እያደቀቁ በስልጣን ላይ ናቸው – ምርጫ ሳይተጓጎል በየዓምስት አመቱ ሲጠሩ ውነትም ዲሞክረሲ የሰፈነ ይመስላል።የአይቮሪኮስቱ ሎሬት ባግቦ እና የኛዎቹ ወያኔዎች ምርጫ መጥራት ባይታክቱም ተወዳዳሪን በምርጫ ሳጥን ብቻ ሳይሆን በሬሳ ሳጥን መሸኘት ላይ የተካኑ ሆነው ተገኝተዋል።
እነኝህ ሁሉ የድህረ ቀዝቃዛ ጦርነት ዘመን ወጀብ የሚቀዝፉበትን አቅጣጫ እንዲሞርዱ ካስገደዳቸው መካከል ናቸው። ሁሉም በገዛ ህዝባቸው ላይ ሰቆቃ የፈፀሙ ፤ የዘረጉት መንግስታዊ መዋቅር በዘር እና አድልዎ ላይ የተገነባ ፤ ሙስና እስከ አንገታቸው የዋጣቸው ፣ ስልጣንን አላንዳች ተጠያቂነት በመዳፋቸው ጨምድደው ለመዝለቅ ቅንጣት የማያመነቱ ገዢዎች መሆናቸውን ህዝባቸው ፣ አለምም ይመሰክራል።
ኢንዶኔዢያ ከ200 ሚሊየን በላይ ህዝብ ያላት ፣ ከ250 በላይ ቋንቋዎች የሚነገርባት እና ከ300 በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት አገር ናት። ሱሀርቶ ወደ ስልጣን የመጣው በወታደራዊ ሀይል ሲሆን ለ31 ዓመታት ሰልጣን ላይ ቆይቷል – አገዛዙ በየ አምስቱ ዓመት ምርጫ የሚጠራ ሲሆን ሱሀርቶ ለሰባተኛ ጊዜ ለመመረጥ እየተሰናዳ ባለበት ሁኔታ ከቀዝቃዛው ጦርነት ማግስት በግንቦት 1998 በህዝባዊ እምቢተኝነት ከስልጣን ተወግዷል። የሱሀርቶ አገዛዝ ቃላት ሊገልፁት በማይቻል መጠን የነቀዘ ፣ አፈና አና ግድያ የተንሰራፋበት ሲሆን ከምዕራቡ ጋር በነበረው ቁርኝት በተገኘ ብድር የተገነቡ ፎቆች እና መንገዶች ምክንያት አገሪቱ በርሱ አገዛዝ ዘመን አድጋ ነበር የሚሉ አሉ። የመሬት ልማት በፖለቲካ ጥፋት!!
ሁዋላ ላይ ይፋ እንደ ሆነው የሱዋርቶ አገዛዝ ብልሹነት ተጋልጦ ስልጣኑን እንዲለቅ ሲገደድ በመጨረሻው ሰዓት “I am sorry for my mistakes” ሲል ተመፃድቋል። ስህተቱ በቢሊየን የሚቆጠር ሀብት ለራሱ እና ለቤተሰቦቹ ማግበስበሱ ፣ ከግማሽ ሚሊየን በላይ ተቃዋሚ ዜጎች ለሞት እና ስደት መዳረጉ ፣ እጅግ አድርጎ በሙስና የነቀዘ አስተዳደር መሆኑ ነበር።
ዛምቢያ ከቅኝ አገዛዝ እንድትላቀቅ መሪ ሚና የተጫወቱት ካውንዳ ለስልጣናቸው እጅግ አድርገው የሚሳሱ እሳቸው ከሌሉ አገሪቱ ያበቃላት የሚል ዝንባሌ ነበራቸው። የፖለቲካው አየር ሲለወጥ እና ተቀዋሚ ድርጅቶች የለውጥ ጥያቄያቸውን አንግበው ሲነሱ ምርጫ ለመጥራት ተገደዋል። እሳቸው ምርጫ ውድድር ውስጥ ሲገቡ ለነፃነት ያበቃሁት ‘ህዝብ ካለኔ ማንን ሊመርጥ ይችላል?’ የሚል እምነት አድሮባቸው ቆይቷል። ውነትም ሀያ በመቶ ድምፅ ማግኘታቸው ሲታይ አሁንም የሚወዳቸው አለ ያሰኛል። ይሔ ሀያ በመቶ ድምፅ ግን ዘር ግንድ ቆጥሮ የለገሳቸው የራሳቸው ብሔረሰብ ህዝብ ብቻ ነበር። የምርጫው ውጤት በዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምስክርነት ይፋ ሲሆን እና መሸነፋቸውን ሲገነዘቡ ጓዛቸውን ጠቅልለው ከቤተመንግስት ለመውጣት አላንገራገሩም። ከነጭ ቅኝ ግዛት ነፃ ያወጡት ህዝብ ድምፁን ሲነፍጋቸው ህዝቡ ውለታ ቢስ መሆኑን በምሬት ሳይጠቁሙ ግን አላለፉም። በኔ የደረሰ እንዳይደርስባችሁ ፣ ህዝብን አምናችሁ ምርጫ የሚባል ጣጣ ውስጥ አትግቡ ብለው ቀሪ አምባገነን የአፍሪካ መሪዎችን ምክር ከመለገስም አልቦዘኑም። ጉዳዩ ምርጫ ከሆነ ሌላ መላ ፈልጉለት የሚል መልዕክታቸውንም አስተላልፈዋል።
እነሆ ምርጫዎች እየተካሄዱ ነው። በዩጋንዳ ፣ በኬንያ ፣ በደቡብ ሱዳን ፣ በሩዋንዳ፣ በኢትዮጵያ … ምርጫ ይጠራል… ደም ይፈሳል… አምባገነኖቹ ተቃዋሚ ነው ብለው በጠላትነት የፈረጁትን እጃቸው ላይ ባገኙት በማናቸውም የማጥቂያ ዘዴ ተጠቅመው ያምቃሉ። እናም ስልጣን ላይ ይቆያሉ… በምርጫ!!
ዘመኑ የዲሞክራሲ ነዋ! ዲሞክራሲ ደግሞ ‘ሂደት’ ነው ይላሉ። ዛሬ ተዘርቶ ነገ አይበቅልም ይሉናል። ሀያሶስት ዓመትም መብቀል አይችልም… ሀምሌ ላይ ዘርቶ ታህሳስ ላይ እንደሚታጨድ ሰብል ጊዜ ይወስዳል ይሉናል…እንደ ማሳው እንደ አፈሩ ነው። ዲሞክሲ ጎምርቶ የሚታጨደው በስንት ዘመን እንደሆነ ግን የሚነግረን የዲሞክሲ አዝመራ ጠቢብ ሊጠሩልን አልቻሉም… ብቻ ሂደት ነው… ምርጫ ደግሞ በያምስት ዓመቱ ይጠራል… ማን ይፈራል?
በዘረኝነት ቀንበር ጠምደው የከፋፈሉትን ህዝብ በማይጎመራው የዲሞክረሲ ማሳ ላይ እየነዱት ነው። ቀንበሩን ተሸክመው ከሚወላከፉት ዜጎች መካከል የምናውቃቸው የሚያውቁን ብዙ ናቸው።
ከአስር ዓመት በፊት በ1997 ወያኔ ምርጫ ውድድር ይደረግ ብሎ የፖለቲካ ምህዳሩን በመጠኑ ሰፋ ሲያደርግ ፉክክሩን ባሸናፊነት እንደሚወጣ አልተጠራጠረም ነበር። ወያኔ በወቅቱ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ መለስ ዜናዊ እንዳረጋገጠው ‘… ሳናጭበረብር ግልፅ በሆነ ምርጫ የምናሸንፍ መሆኑን ይህ ሰልፍ ያራጋግጣል’ ብሎ እንደነበር ያስታውሷል። ባለ ‘ራዕዩ መሪ’ ህዝቡንም ልቡንም ማንበብ አልቻለም። ውድድሩ ተጠናቆ ወያኔ መሸነፉ ሲረጋገጥ ታንክ እና መትረየስ ይዞ መጣ – አዲስ አበባን የጦር ቀጠና አደረጋት። የፈሰሰው ደም ፣ የጎደለው አካል እና የፈረሰው ቤት ጩኸቱ ዛሬ ድረስ ያስተጋባል።
ታዛቢ አይፈሩም ምክንያቱም ማን እንደሚታዘባቸው አስቀድመው የሚወስኑትም እነሱ ናቸው። ከወያኔ የዘርኝነት ቀንበር ነፃ የሆነው ብዙሀኑ ህዝብ ግን ሳይመርጡት በነፃ ይታዘባል ፤ ሸፍጡንም ፣ ኮረጆ ግልበጣውንም ፣ ዱላውንም ፣ ጥይቱንም ፣ ወህኒውንም አይቶ ቀምሶ በዝምታ ይመሰክራል። ማን ተወዳድሮ ማን እንዳሸነፈ ያውቃል ፣ ድምፁን ሲሰርቁበት ግን ሌቦችን ለመታደግ አቅም የለውምና በዝምታ ታዝቦ ፣ አድፍጦ ሌላ ቀን ይጠብቃል።
አምባገነን ገዢዎች በስልጣን መቆየት የሚችሉበትን ሰበብ እያሰላሰልኩ ሳለሁ ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት ሔሮዶቱስ በማስታወሻው ያሰፈረው ገጠመኝ ትዝ አለኝ።
ጉዳዩ እንዲህ ነበር። ፐርቲንደር የተባለው ንጉስ ኮሪንዝ በተሰኘች ምድር በለጋ ዕድሜው ወደ ዙፋን ይወጣል። ታዲያ ሰልጣኑን ጠብቆ ለማቆየት የሚችልበትን ልምድ ለመቅሰም እንዲረዳው መልዕክተኛውን በስልጣን ለረዢም ዘመናት የቆየ ዝራቡለስ ወደ ተባለ የሚልተስ አምባገነን ገዢ ዘንድ ይልከዋል።
አንጋፋው አምባገነን ዝራቡለስ መልዕክተኛውን በጠዋት ተቀብሎ የመጣበትን ጉዳይ ካጣራ በሁዋላ ፈረሱን አስጭኖ ወደ በቆሎ እርሻ ይዞት ይሄዳል። እዚያም ከማሳው መካከል እየተንጎራደደ ለመልዕክተኛው የሆነ ያልሆነውን እያወራ በያዘው ገጀራ ከሌሎቹ ተክሎች ቀድመው ረዘም ረዘም ያሉትን አንገት እየቀላ ይጥላል። ረዣዢም በቆሎ ካናቱ እየተጎመደ ሲወድቅ ማየቱ ግራ የገባው መልዕክተኛ ወደ መጣበት ተመልሶ የሆነውን ለወጣቱ ንጉስ ፐርቲንደር በዝርዝር ይነግረዋል። ወጣቱ ንጉስ የተላለፈለት መልዕክት ምን እንደሆነ ለመረዳት ጊዜ አልፈጀበትም – ስልጣንህን ለማቆየት ከፈለክ ከሌሎች ሁሉ ቀድመው የነቁ ረዘም ያሉትን እየመረጥክ ሳይቀድሙህ በመቀንደብ ማስወገድ ነው። ይኸው ነው መልዕክቱ –
ጥንትም ዛሬም ረዣዢም ተቀናቃኞችን ሳይቀድሙህ ቅደማቸው… ‘ለምሳ ሲያስቡን ለቁርስ አደረግናቸው…’ የመንግስቱ ፖሊሲ እንደነበር ሁሉ የመለስ ዜናዊ ‘ጃኬታቸውን አስወልቀን አባረርናቸው…’ የተግባር መመሪያ ነበር – ወያኔ ዛሬ የሚጠቀመው በዚሁ ነው። በተቀዋሚ ሰፈር ረዘም ብሎ የወጣውን እሸት አናቱን ቀንጥሰው ለመጣል ቆርጠው ሲሰሩ ቆይተዋል። ትናንት በቅንጅት ፣ በነ ፕሮፌሰር አስራት እንዲሁም ዛሬ – በአንድነት እና በመኢአድ ላይ የተፈፀመው ይኸው ነው። በወያኔ ዘመን ድንክዬ በቆሎዎች ሲሻቸው መኖር ይፈቀድላቸዋል – የአምባገነኖች ዲሞክረሲ በነሱ አንገት ላይ አይመትርም።
ዋ ለረዣዢም በቆሎዎች!!
http://ecadforum.com/Amharic/archives/14360/

Saturday, February 7, 2015

የትግራይ ሕዝብንና የኢትዮጵያ ፓሊስን በኢትዮጵያዊያን ለማስጠላት የሚደረገው ጥረት ከሽፏል!


Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy
ህወሓት ንፁሀንን ለመደብደብ የሚያበቃ በቂ ክፋት ያለው ልዩ ጦር ሲያሰለጥን ቆይቷል። ይህን ልዩ ጦር የፓሊስን መለያ እያለበሰ ነውረኛ ሥራዎችን እንዲሠራ በማድረግ በአንድ በኩል ንፁሀንን የመጉዳት በሌላ በኩል ደግሞ ፓሊስን በሕዝብ የማስጠላት መንታ ግቦችን ለማሳካት ተጠቅሞበታል። ይህ ልዩ ጦር በአለፉት ጥቂት ሳምንታት ባዶ እጃቸው ለተቃውሞ በወጡ ነብሰ ጡር ሴቶች ላይ ሳይቀር ባሳየው ጭካኔ፣ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ባደረሰው ድብደባ መጠን እና ባካሄደው የግለሰብ ንብረቶች ዝርፊያ የሥርዓቱ ባህርይ ፈጽሞ ከሰውኛ ተፈጥሮ እየወጣ እንደሆነ አመላካች ነው። በእነዚህ ድብደባዎች ወቅት በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስባቸው ተደርጓል። በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት የተደረገው በደብዳቢዎቹ የግል ውሳኔ ሳይሆን ከበላዮቻቸው በተሰጠ ትዕዛዝ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
በአርበኞች ግንቦት 7: እምነት መሠረት የፓሊስ ከፍተኛ አዛዦች ህወሓቶች ቢሆኑም አብዛኛው የሠራዊቱ አባል በህወሓት ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ የተማረረ፤ የሥርዓቱ መለወጥ የሚፈልግና ሥርዓቱን ለመለወጥ የሚደረገውን ትግል የሚደግፍ ኃይል ነው። ስለሆነም ህወሓት የተለየ ጦር አሰልጥኖ የፓሊስ ልብስ በማልበስ ነውረኛ ወንጀል በማሠራት ፓሊስን ለማስጠላት የሚያደርገው ሴራ ሊጋለጥ ይገባል ብሎ ያምናል። የፓሊስ ሠራዊት አባላትም በስማቸውና በደንብ ልብሳቸው የሚደረገውን ደባ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እንዲያጋልጡ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ህወሓት እንደሚያስበው እና የኢትዮጵያም ሕዝብ እውነት አድርጎ እንዲቀበለው እንደሚፈልገው የትግራይ ሕዝብ በጅምላ የህወሓት አፍቃሪና ደጋፊ አይደለም። እንዲያውም በተፃፃሪው ህወሓት ከትግራይ ተወላጆች ልብ እየተነቀለ ነው። የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትሕዴን/ደምህት) ከትግራይ የበቀለ፤ ህወሓትን በአመጽ ለመፋለም የቆረጠ ኃይል ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በትግራይ ውስጥ ብዙ ደጋፊዎች ያሉት መሆኑ የምናውቀው ሀቅ ነው። አረና ትግራይ ህወሓትን በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተነሳ ተሰሚነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ የመጣ እና አቶ አብርሀ ደስታን የመሰለ ወጣት ኢትዮጵያዊ የፓለቲካ መሪ ያወጣ ድርጅት ነው። ህወሓት አንድነት ፓርቲ ላይ የመረረ አቋም ከወሰደባቸው ምክንያቶች አንዱ በትግራይ ውስጥ ያለው ተቀባይነት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ነው። ህወሓት የትግራይን ሕዝብ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ በጅምላ ለማጣላት የሚያደርገው ጥረት ማክሸፍ ይኖርብናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል፤ ለዚህም ተግቶ ይሠራል። አርበኞች ግንቦት 7 ከትግራይ የዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር በመተባበር ፀረ ህወሓት ትግል በትግራይ ውስጥ መቀጣጠል ይኖርበታል ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ትግራይ የህወሓት መቀበሪያ የመሆኗ ጊዜ ሩቅ አይደለም።
በዘንድሮው የ2007 የሴራ ምርጫ አማካይነት ተድበስብሰው የመጡ እነዚህ ሁለት ክፋቶች ማለትም ፓሊስን በሕዝብ ማስጠላት እና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የዲሞክራሲ ወገንተኞችን ለይቶ ማጥቃት ከበስተጀርባቸው ያዘሉት እኩይ ዓላማ መጋለጡ መንገዳችን ያጠራልናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። በአንድነትና በመኢአድ የተፈፀው የድርጅትና የንብረት ዘረፋም የዚሁ ፕሮጀክት አካል መሆኝ ግልጽ ነው፤ ነገ ተመሳሳይ ነገር በሰማያዊ ፓርቲም ላይ ይፈጽም ይሆናል።
በመሆኑ ከ2007 የሴራ ምርጫ ትሩፋቶች በትግራይ ሕዝብና በፓሊስ ሠራዊት ጀርባ የሚደረገው ደባ መጋለጡ ነው። ይህ ድል ጽኑ መሠረት እንዲይዝ ህወሓትንና የትግራይን ሕዝብ የመነጠል እና ፓሊስ የሕዝብ አጋር መሆኑን የማረጋገጥ ሥራዎችን አጠናክረን መሥራት እንዳለብን አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !
http://ecadforum.com/Amharic/archives/14351/

Wednesday, February 4, 2015

አንድነትን “እናኝከዋለን፤ እንገድለዋለን” – ምርጫ ቦርድ

ትዕግስቱ አወሉ እንደ አየለ ጫሚሶ

tplfs election board


የዛሬ አስር ዓመት “የሕዝብ ሱናሚ” እያለ ሲምል ሲገዘት የነበረው ህወሃት ሱናሚው ወደ እርሱ እየጎረፈ ሲመጣ በረገገ፡፡ መፍትሔ በጠብመንጃ አፈሙዝና በብረት ብቻ እንደሆነ የሚያምነው ህወሃት በረሃ የለመደውን በትሩን አነሳ፤ ንጹሃንን ጨፈጨፈ፤ ደም አፈሰሰ፤ ኢትዮጵያን ወደ እስርቤትነት ቀየራት፡፡ ትዕዛዙን በቀጥታ የሰጡት “ባለራዕዩ” ለፍርድ ሳይቀርቡ “እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” ያሉትን ሰፊውን ሕዝብ ሳይጨርሱት እንደ ክዳን ቆርኪ ተስፈነጠሩት፤ ላይመለሱ ሄዱ፡፡
የዛሬ አስር ዓመት የቅንጅት አካሄድ ያስፈራው ህወሃት ጉዳዩን ለራሱ ለፓርቲውና ለሕዝብ ከመስጠት ይልቅ ደም መቃባት ውስጥ ገባ፡፡ ፓርቲው የነበረበት የውስጥ ችግር እንዳለ ሆኖ የፈሪ በትር የዘረጋው ህወሃት የገደለውን ገድሎ ከጨረሰ እና የኢትዮጵያን መሬት በደምና በእናቶች እምባ እንደገና ካጨቀየ በኋላ ቅንጅትን የማፍረስ ተግባሩን በዕቅድ ይዞ በይፋ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ግምባር ቀደም ተሰላፊው የተቋም ባንዳ “ምርጫ ቦርድን”፤ በግለሰብ ደረጃ ደግሞ በተለይ ሁለት ግለሰቦችን አሰለፈ፡፡ ዘመቻ “ቅንጅትን መግደል” ተጀመረ፡፡
በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ምንም በማያሻማ ሁኔታ በኢትዮጵያ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ዶናልድ ያማሞቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር (ስቴት ዲፓርትመንት) ለሚገኙት አለቆቻቸው THE ETHIOPIAN GOVERNMENT CHEWS THE CUD” (የኢትዮጵያ መንግሥት ቅንጅትን አኘከው) በሚል ርዕስ የጻፉት እንዲህ ይነበባል፤
Over the course of the week of January 7, the National Electoral Board of Ethiopia (NEB) hammered what appear to be the final nails in the coffin of the opposition Coalition for Unity and Democracy (CUD) party. Since their surprise showing in the 2005 elections, gaining enough seats to become the second largest political party in Ethiopia, the CUD has virtually disintegrated as a result of internal power struggles and interference from the Ethiopian Government (GoE). In the latest setback, the NEB awarded the famous victory sign — the CUD symbol widely recognized by voters — to former ally turned foe, Lidetu Ayalew of the United Ethiopian Democratic Party-Medhin (UEDP-Medhin).  The NEB followed this later in the week by finally awarding registration of the reformed Coalition for Unity and Democracy Party (CUDP) party name to yet another former CUD ally turned foe Addis Ababa city council member-elect Ayele Chamisso.  Though Ayele, who is broadly viewed as having been co-opt by the GoE, has invited all faction of the former CUD to join his party, few will likely take his offer.
In a meeting with Ambassador on January 11, NEB board chairman Dr. Merga Bekana and vice-chairman Dr. Addisu Gebre-Egziabhier said that the Board still had not decided on the CUDP’s registration and would continue to consider the matter in coming weeks. Almost immediately following the meeting, however, the NEB publicly announced that it had decided that morning to award the party license to Ayele. This followed their controversial decision earlier in the week to give the CUD’s famous victory symbol to the CUD’s despised adversary Lidetu Ayalew (another person believed to have been co-opted by the GoE during the CUD’s post-2005 election struggles), and his UEDP-Medhin party.
The opposition fiercely accused the NEB of being under the influence of the GoE and of delivering votes to the ruling Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Forces (EPRDF) party after the opposition’s surprisingly strong showing. Since then, a new Board has been put in place, but the opposition have not altered their criticism. The NEB’s recent decisions to award the CUD party symbol and name to politicians, who are at best undeserved and at worst proxies of the GoE, has done much to reignite lingering suspicions regarding the NEB’s independence. As if to prove these suspicions, NEB vice-chairman Dr. Addisu (a Tigrayan political scientist widely believed to be the “enforcer” at the NEB) recently commented to USAID’s Senior Democracy Advisor — a former Stanford University Political Science Professor ) (strictly protect) that the NEB had decided to “kill the CUD.” The NEB decisions of the last week have effectively done exactly that.
በጃኑዋሪ 7 ሳምንት ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ (ቅንጅት) ፓርቲ የሬሣ ሳጥን ላይ የመጨረሻ የሚባለውን ሚስማር መትቷል፡፡ በ2005 (1997) ምርጫ በአገሪቱ ሁለተኛው ትልቁ የተቃዋሚ ፓርቲ ለመሆን የሚያስችለውን አስደናቂ ድልና በቂ መቀመጫ ካገኘ በኋላ ቅንጅት በውስጡ በነበረው የኃይል (የሥልጣን) ሽኩቻና ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ይደርስበት በነበረው ጣልቃ ገብነት ምክንያት አለሁ ቢልም እየተፈረካከሰ ነበር፡፡ በቅርቡ በተደቀነበት ሌላ ደንቃራ ደግሞ ምርጫ ቦርድ ዝነኛውንና በብዙሃን መራጭ ዘንድ ዕውቅና የነበረውን የቅንጅትን (V) ምልክት ቀድሞ (የቅንጅት) ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ፓርቲ – ኢዴፓ-መድህን ልደቱ አያሌው ሸልሞታል፡፡ በመቀጠልም ምርጫ ቦርድ ይህንን ተከትሎ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የስም ምዝገባ ቀድሞ የቅንጅት ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የአዲስ አበባ ምክርቤት እጩ ተመራጭ አየለ ጫሚሶ ሸልሞታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ቅጥረኛ እንደሆነ በሰፊው የሚታመነው አየለ ጫሚሶ ከቀድሞው ቅንጅት ተሸራርፈው ለወጡት ሁሉ የእርሱን ፓርቲ እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቢደርግም ጥቂቶች ብቻ ጥሪውን ይቀበላሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ . . .
addisu  g of neb
አዲሱ ገብረእግዚአብሔር
የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ዶ/ር መርጋ በቃና እና ምክትል ሊቀመንበሩ ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔርከአምባሳደሩ (ያማሞቶ) ጋር ጃኑዋሪ 11 ቀን ባደረጉት ስብሰባ የቅንጅትን ምዝገባ በተመለከተ ገና ውሳኔ ላይ እንዳልደረሱ እና በመጪዎቹ ሳምንታት ጉዳዩን እንደሚመለከቱት ነበር የተናገሩት፡፡ ነገር ግን ወዲያውኑ ስብሰባው እንዳበቃ ማለት ይቻላል የዚያኑ ቀን ጠዋት የቅንጅትን የስም ምዝገባ ለአየለ ለመስጠት መወሰኑን ምርጫ ቦርድ ለሕዝብ ይፋ አደረገ፡፡ ይህ የቦርዱ ውሳኔ በሳምንቱ መጀመሪያ አካባቢ የቅንጅትን ዝነኛ (V) ምልክት በቅንጅቶች ለተናቀውና የፓርቲው ጠላት ለሆነው ልደቱ አያሌውና ለኢዴፓ-መድህን ፓርቲው ለመሸለም የተደረገውን አከራካሪ ውሳኔ ተከትሎ ነው፡፡ (ልደቱ አያሌው ከምርጫ 1997 በኋላ ቅንጅት ውስጥ በነበረው ትግል ውስጥ በኢትዮጵያ መንግሥት የተመደበ ሌላው ቅጥረኛ እንደሆነ ይታመናል)፡፡ . . .
ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ መንግሥት ሥር እንደሆነ እና ተቃዋሚዎች አስገራሚ ውጤት በምርጫው ላይ ካሳዩ በኋላ (የመራጮችን) ድምጽ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢህአዴግ) እንዳስረከበ ተቃዋሚ (ፓርቲዎች) አጥብቀው ይከስሳሉ፡፡ ከዚያ ወዲህ አዲስ ቦርድ የተሰየመ ቢሆንም ተቃዋሚዎች ግን አሁንም ትችታቸውን አላቆሙም፡፡ የቅንጅትን ስም እና ምልክት ፍጹም ለማይገባቸውና ለኢትዮጵያ መንግሥት የቅርብ ወዳጆች ለሆኑት ፖለቲከኞች ማስረከቡ ምርጫ ቦርድ ከአድልዎ የነጻ አለመሆኑ ላይ ያሉትን ጥርጣሬዎች እንደገና እንዲቀጣጠል አድርጓል፡፡ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር አዲሱ በቅርቡ ለዩኤስኤይድ ከፍተኛ የዴሞክራሲ አማካሪና የቀድሞ የስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር (ስሙ እንዳይወጣ በጥብቅ የተከለከለ) ምርጫ ቦርድ “ቅንጅትን ለመግደል” ወስኖ እንደነበር መናገሩ እነዚህን ጥርጣሬዎች እርግጠኛ ያደርጋቸዋል፡፡ (የአዲግራት ተወላጅ የሆነው) (ዶ/ር አዲሱ የትግሬ የፖለቲካ ሳይቲስት ሲሆን የምርጫ ቦርድ “ፈጣሪና አድራጊ” እንደሆነ በሰፊው ይታመናል)፡፡ ባለፈው ሳምንት ምርጫ ቦርድ የወሰደው ውሳኔ (የቅንጅትን ስምና ምልክት ለቅጥረኞቹ መስጠቱ) ይህንኑ (ቅንጅትን የመግደሉን ዕቅድ) የሚያረጋግጥ ነው፡፡ . . . (ሹልክዓምድ (ዊኪሊክስ) ላይ የወጣውን ሙሉ መረጃ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
አሁንስ ማነው ባለሳምንት? በዚህኛው የምርጫ ድራማ አየለ ጫሚሶን የሚጫወተው ትዕግስቱ አወል እንደሆነ ይፋ ሆኗል፤ ልደቱንስ ማን ይተውነዋል?
ከዚህ በፊት በሰማያዊና በሌሎች ፓርቲዎች ላይ የደረሰውና አሁንም እየደረሰ ያለው እንዲሁም ሰሞኑን በአንድነት ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ላይ የደረሰው ሰቆቃ የዘንድሮውን ሁኔታ የተለየ እያደረገው እንደሆነ ጎልጉል ከተለያዩ ምንጮች የሚደርሱት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ስለዚህም ነው “ምርጫ ቦርድ” ቅንጅትን በዕቅድ እንደገደለው አሁንም አንድነትንና ሌሎቹን ተቀናቃኞች “አኝኮ ለመግደል” ውሳኔው የሆነው፡፡
ከሕዝብ በኩል የሚሰማው የሰላማዊ ትግል ቁርጠኝነት ግን የህወሃትን የልመና ኮሮጆ በሚሞሉት ምዕራባውያንም ዘንድ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው እንደሆነ ጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ሰልፍ በተካሄደበት ወቅት በተለያዩ የማኅበራዊ ገጾች ላይ ተሰራጭቶ ያገኘነውን መረጃ መጥቀሱ የቁርጠኝነቱን መጠን በተወሰነ መልኩ የሚያመለክት ነው፡፡ “በዕለቱ የደረሰበትን ጉዳት አስመልክቶ ለቢቢኤን ሬዲዮ የተናገረው የአዲስ አበባ ወጣቶች ጉዳይ አንድነት ፓርቲ ኃላፊ ስንታየሁ ቁስሉ ሳይደርቅ በወኔ እንዲህ ነበር ያለው “ወያኔ ላጠፋው ጥፋት የሚያወራርደው ሒሳብ እንዳለ ማወቅ አለበት፡፡ ለትግላችን እንሰዋለን፤ በዋዛ አንላቀቅም”፡፡
http://www.goolgule.com/election-board-to-chew-and-kill-udj/

ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድ የፓርቲዎች ሚዲያ አጠቃቀም ድልድል ፍትሃዊ አለመሆኑን አስታወቀ


ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድ ያወጣው ረቂቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ውድድር የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሰዓት አጠቃቀም ድልድል ፍትሃዊና በእኩልነት ላይ የተመሰረተ አለመሆኑን አስታወቀ፡፡Ethiopia's Semayawi (Blue) party logo
ዛሬ ጥር 25 ቀን 2007 ዓ.ም የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሀገር አቀፍ ፓርቲዎችን በረቂቅ የሰዓት ድልድሉ ላይ ጊዮን ሆቴል ጋብዞ ውይይት አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) ኃላፊዎች ረቂቁን ለውይይት ያቀረቡ ሲሆን፣ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ እና ሌሎች ኃላፊዎችም በውይይቱ ተገኝተዋል፡፡
የኢብኮ ኃላፊዎች ባቀረቡት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚዲያ አጠቃቀም ረቂቅ ድልድል መሰረት 55 ፐርሰንት በፓርላማ መቀመጫ ወንበር ላላቸው ፓርቲዎች፣ 20 ፐርሰንት ፓርቲዎቹ በሚያቀርቧቸው ዕጩዎች ብዛት እንዲሁም ቀሪ 25 ፐርሰንቱ ለሁሉም ፓርቲዎች በዕኩል የሚከፋፈል እንደሆነ ተገልጹዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲን በመወከል በውይይቱ ላይ የተገኙት የፓርቲው የህግ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደ ለነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጹት፣ ረቂቅ የሚዲያ አጠቃቀሙ ድልድል ሲወጣ እንደ መስፈርት የተጠቀሙባቸው ነጥቦች ችግር ያሉባቸው ናቸው፡፡
‹‹በእኛ እምነት መስፈርቱም ልክ አይደለም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የሚዲያ ሰዓት አጠቃቀም ድልድል ሲወጣ ሁለት መስፈርቶች በቂና ትክክለኛ ናቸው ብሎ ያምናል፡፡ እነዚህ ነጥቦች በሚቀርቡ እጩዎች ብዛት እና በእኩልነት የሚከፋፈል የድልድል መስፈርት መሆን አለባቸው›› ብለዋል አቶ ይድነቃቸው፡፡
በእርግጥ ረቂቁን ያቀረበው ኢብኮ እንደ መመዘኛ መስፈርት የተጠቀመው ‹‹እኩልነትና ፍትሃዊነት›› የሚሉ መርሆዎችን ነው፡፡ ‹‹ኢብኮ በቃላት ደረጃ የገለጻቸው ‹ፍትሃዊነትና እኩልነት› በተግባር ረቂቅ ድልድሉ ላይ አልታዩም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በእኩልነትና ፍትሃዊነት መርሆዎች ላይ ችግር የለበትም፡፡ መርሁን መሰረት አድርጎ ወጣ የተባለው የሚዲያ ድልድል መጠን ግን በትክክል መርሁን የተከተለ አይደለም፡፡ ስለሆነም ለውጥ ሊደረግበት ይገባል›› ብለዋል አቶ ይድነቃቸው፡፡
አቶ ይድነቃቸው የሰዓት አጠቃቀም ድልድሉ ላይ ስንወያይ ነጻ ሚዲያ በሌለበት፣ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በተገደበበት፣ ጋዜጠኞች በታሰሩበትና በተሰደዱበት፣ አማራጭ የሚዲያ ተቋማት በሌሉበት በዚህ አጣብቂኝ ወቅት ላይ በህዝብ ሀብት በሚተዳደሩ ሚዲያዎች ላይ የፍትሃዊነት ችግር ይዘን መወያያታችን አሳዛኝ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ሳንሱር በህገ-መንግስቱ ተነስቷል፤ ይሁን እንጂ ኢብኮ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ጊዜያት ለህዝብ የሚያስተላልፏቸው አማራጭ ሀሳቦችና ፖሊሲዎቻቸውን በቆርጦ ቀጥል ሲያዛባ እናስተውላለን፤ ይህ ሁኔታ መወገድ ያለበት ነው፡፡››
በውይይቱ ላይ ኢህአዴግ የድልድሉ መስፈርት ላይ እንደሚስማማ በመግለጽ፣ በፐርሰንቱ የተቀመጠው መጠን ላይ ግን መሻሻል እንዲደረግ እንደሚፈልግ መግለጹ ታውቋል፡፡
http://ecadforum.com/Amharic/archives/14326/

Saturday, January 3, 2015

“እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም” አብርሃ ደስታ

"በሐሰት ፕሮፖጋንዳ ሰው ማሳበድ ይፈልጋሉ" ኦኬሎ አኳይ

abraha and okello


ከቂሊንጦ እስር ቤት ከሚገኙት መካከል የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ያነጋገራቸው አብርሃ ደስታና የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ኦኬሎ አኳይ፣ ስለ እስራቸው ሁኔታ እንዲህ ይላሉ:: በቅድሚያ አብርሃ ደስታ:-
“እዚህ እስር ቤት ውስጥ በሽብር ስም የገባ ሰው በፈጠራ ወንጀል እንደገባ ነው የሚታመነው፡፡ ስለዚህ የሽበር ክስ ተመስርቶባቸው የታሰሩትን ሰዎች ማንም ወንጀለኛ አድርጎ አይመለከታቸውም፡፡ በእርግጥም አሸባሪ የለም፤ የፈጠራ ክስ ነው ያሳሰራቸው፡፡ አሸባሪ አለ ከተባለም እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም፡፡
“ነጻ መውጣት ያለበት ቡድን አለ፣ እሱም ኢህአዴግ ራሱ ነው፡፡ እኔ አልታሰርኩም፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እስር የአዕምሮ ነው፡፡ እኔ አዕምሮየ አልታሰረም፡፡ ነጻ ሰው ነኝ፤ ውስጤ በጣም ነጻነት አለው፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡
“እኔ እስር ቤት እንድገኝ ያደረገኝ ወንጀል አይደለም፡፡ መቃወሜና ይህን ተቃውሞየን በጽሑፍም በፊት ለፊትም መግለጼ ነው፡፡ ይህን ደግሞ ብዙ ኢትዮጵያውያን ያውቁልኛል፡፡ ሌላው ቢቀር ጥቂት የህወሓት ሰዎችም ያለ መረጃ እንደታሰርኩኝ በማመን እስሩን እየተቃወሙ ይመስለኛል፡፡ አንድ ቀን ወደ ህሊናቸው ከተመለሱ ስህተታቸው በህዝብ ፊት ያዋርዳቸዋል፡፡”
“በሐሰት ፕሮፖጋንዳ ሰው ማሳበድ ይፈልጋሉ” ኦኬሎ አኳይ፣ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት
“የሆነ ያልሆነውን የሚያወራው በዙሪያዬ ቢሰበሰብም እኔ በጣም ሰላም ይሰማኛል፡፡ ካድሬዎች አብረውን እስር ቤት አሉ፡፡ ወሬ ነው የሚለቃቅሙት፡፡ ይህን ወሬ ሲለቃቅሙ ይቆዩና የሆነ ያልሆነውን እያወሩ፣ የሐሰት ፕሮፖጋንዳ እየነዙ ሊያሳብዱህ ይሞክራሉ፡፡ እስር ቤትም ችግር ፈጣሪዎች ራሳቸው ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እኔማ ሰላማዊ ሰው ነኝ፡፡ ጉዳዩንም ፍርድ ቤት ይጨርሰው፡፡ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ ባላስብም ፍርድ ቤት የሚወስነውን እጠብቃለሁ፡፡
“እየመጡ የሚጠይቁኝ ዘመዶች አሉኝ፡፡ ቤተሰቦቼ ደህና መሆናቸውን መረጃ አገኛለሁ፡፡ ስለዚህ ምንም የምረበሽበት ነገር የለም፡፡ በህግ የምከራከርባቸው ብዙ ነጥቦች አሉ፡፡ ቢሆንም ከውሳኔ በፊት ምንም ባልናገር ጥሩ ነው፡፡ እዚህ ድረስ እየመጡ ለሚጠይቁኝ ሁሉ ክብር አለኝ፡፡” (በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር)
http://www.goolgule.com/eprdf-is-the-most-notorious-terrorist/

ወ/ሮ ገነት ዘውዴ እውን ነገሩ እንዲያ ነውን?

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

genet zewdie


ወ/ሮ ገነት ዘውዴ (ዮዲት ጉዲት) ይቅርታ መሳደቤ አይደለም ሰው የሚያውቃቸው በዚህ ስም በመሆኑና የሚኮሩበትም በመሆኑ እንጅ፡፡ እናም ወ/ሮ ገነት በቅርቡ በሸገር የኤፍ ኤም ሬዲዮ (ነጋሪተ- ወግ) “የሸገር እንግዳ” በተባለው ዝግጅት እንግዳ ሆነው አዘጋጇ ጋዜጠኛ ወ/ሮ መዓዛ ሦስት ቅዳሜ አዋይተዋቸው ነበር፡፡ በዚያ ጨዋታቸው ወ/ሮ ገነት ከተናገሩት ብዙው ነገር ከንክኖኝ ከጊዜ አንጻር ባይሆን በጥቂቶቹ ላይ ጥቂት ነገር ለማለት አስቤ እየጫጫርኩ እያለሁ እንዲያውም በወ/ሮዋ በሐሰት ስማቸው ከጠፋ ወገኖችና ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አንደኛው በጥሩ ምሁራዊ ተዋስኦ የተዋዛ ምላሽ ሰጥተው አሻሩልኝ፡፡ ይሁንና ወ/ሮዋ የተናገሩት አጉል ነገር በርካታ በመሆኑ ሁሉንም ለመዳሰስ ከጊዜና ከቦታ አንጻር የማይቻል በመሆኑ ዶክተሩ ለሁሉም አጉል ነገር መልስ ሳይሰጡ ቀሩ፡፡ እኔም እንማማርባቸው ዘንድ ይጠቅማሉ ብየ ባሰብኳቸው በዚያ በወይዘሮዋ ወግ በተነሡ ሁለት ዐበይት አጉል ጉዳዮች ላይ አተኩሬ የተቻለኝን ያህል ለማለት ፈለኩ፡፡ እነኝህ ወ/ሮዋ የተናገሩት ሁለት ዐበይት አጉል ነገሮችም አንደኛው ወይዘሮዋ “የግራ ዘመም የፖለቲካ (የእምነተ-አሥተዳደር) አስተሳሰብ አራማጅ በመሆኔ” እያሉ የተናገሯቸው ነገሮች ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ ሀገራችንን የሴቶች ሲዖል አድርገው ያቀረቡት ነገር ነው፡፡
ወ/ሮ ገነት ግራ ዘመም የፖለቲካ (የእምነተ አሥተዳደር) እምነትን ወይም አሥተዳደርን (left political belief) የተረዱት በተሳሳተ አረዳድ ነው፡፡ ለወ/ሮ ገነት ግራ ዘመም ፖለቲከኛነት (እምነተ-አሥተዳደሬነት) ማለት ነባሩን አስተሳሰብ ሙሉ ለሙሉ መቃረን መቃወም ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ግራ ዘመም እምነተ አስተዳደር ማለት የራስን መጣል መተው መቃረን ማለት ሳይሆን የሶሻሊዝምን (የኅብረተሰባዊነትን) የፖለቲካ (የእምነተ-አሥተዳደር) ርዕዮተዓለም (Ideology) መከተል ወይም መቀበል ማለት ነው፡፡ ይህ ችግር የወ/ሮ ገነት ችግር ብቻ አይደለም በዚያ ዘመን የነበረው ትውልድ ሁሉ ሊባል በሚችል ደረጃ የነበረውን የፖለቲካ ማዕበል ይንጠው የነበረውም እንጅ፡፡
በስለው ከማይበስሉት ከጥቂቶቹ በስተቀር ብዙዎቹ ዛሬ ላይ ሰክነው ሲያስቡት በዚያ ጊዜ የነበራቸው አስተሳሰብ የተሳሳተ እንደነበረ ከመረዳታቸው የተነሣ ያ ዘመን የእብደት ዘመን እንደነበር ሐፍረት እየተሰማቸው ይናገራሉ፡፡ ይህ የጸጸት ስሜት ከግለሰቦችም አልፎ በዚያ የስሕተት ማዕበል ይናጡ የነበሩ ሀገራትም ተጋርተውታል፡፡ የግራ ዘመም ፖለቲከኞች (እምነተ-አስተዳደራዊያን) በነበራቸው የተሳሳተ ግንዛቤ የተነሣ ያራምዱት የነበረው የግራ ዘመም አስተሳሰብ የዜሮ (የባዶ) ብዜት ማለት ነበር፡፡ የነበረውን ነገር አጥፍቶ ከዜሮ የመጀመር የድንቁርና ሥራ ማለት ነው፡፡ በተለይም እንደኛ ጥንታዊና ለሌሎችም የተረፈ ሥልጣኔ ባለቤት በነበረች ወይም በሆነች ሀገር ላይ የነበረውን ብዙ የተለፋበትን የተደከመበትን መሥዋዕትነት የተከፈለበትን ነገር ሁሉ በዜሮ አጣፍቶ ከዜሮ መጀመር ምን ያህል እብደትና ድንቁርና እንደሆነ ቢያንስ አሁን ላይ የማይረዳ ሰው ይኖራል ብየ አላስብም፡፡ አሀ! ለካ እነ ወ/ሮ ገነት አሉ እሽ ከእነሱ ውጭ በሚል ይስተካከልልኝ፡፡
አንድ ሀገርና ማኅበረሰብ ታሪካዊና ጥንታዊ ከሆነ በረጅም ጊዜ ቆይታውና ሒደት ማንነቱን ባሕሉን ሃይማኖቱን አየር ንብረቱን ሳይቀር መሠረት በማድረግ የሚያፈራው በርካታ የተለያዩ ዓይነት እሴቶች ይኖሩታል እነዚህ በሒደት በሞክሮ ማየት (trial and error) የሚጠቅመውን በመያዝ የማይጠቅመውን በመተው ሒደት የሚያዳብራቸው ብዙ ዓይነት አስተሳሰቦች መኖራቸው የማይቀር ነው፡፡ ታዲያ አንድ ትውልድ ድንገት ተነሥቶ ከባዕድ በተጫነው አስተሳሰብ ሳቢያ የነበረውን ሁሉ እንዳለ ጠቅልሎ ልጣል በሚልበት ሰዓት ሊደርስ የሚችለው ኪሳራ እጅግ ከግምት በላይ ነው፡፡ ከስልሳዎቹ እስከ ሰማኒያዎቹ አጋማሽ (1950-1975ዓ.ም.) የነበረው ተማሪውና ተራማጅ ነኝ ይል የነበረው ትውልድ (የደርግ የኢሐፓና ከእነሱ የወጡት የወያኔ ሌሎችም የዚያን ዘመን ፖለቲካ ተዋንያን) በምዕራቡ የሶሻሊዝምና ኮሚኒዝም ርዕዮተ ዓለም ራሳቸውን አጥምቀው የሀገራችንን እሴቶች ከባሕል እስከ ሃይማኖት ከታሪክ እስከ ትምህርት ከወግ እስከ ሥርዓት የነበረውን ሀብታችንን ዋጋ አሳጥተና ጥለው ለገዛ ማንነታቸው ታሪካቸው ቅርሶቻቸው ጠላቶች ሆነው እንደ አዲስ ሀገርና ኅብረተሰብ ከዜሮ ነበር እንድንጀምር ይሟሟቱ የነበሩት፡፡ የእነሱ ጥረትና ፍልስፍና ግን የት እንዳደረሰን ሁሉም በግልጽ የሚያየውና የሚረዳው መረጃ የማያስፈልገው ኪሳራ ነው፡፡
ያ ሁሉ አለፈና ምን አለፈና ይሄው ዛሬስ የሚያዳክረን እሱው አይደል? እሽ ከእኛ ውጭ ባለው ዓለም ግን ዛሬ ሌላው ቀርቶ የዚያ ርዕዮተ ዓለም (Ideology) ቃፊር የነበረችው ሩሲያ እንኳን ተለውጣ ተጸጽታ ያኔ የሰበረቻትን ያደቀቀቻትን አንቅራ ተፍታት የነበረችውን የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ከጣለችባት አንሥታ ክብር በመስጠት ከዚያ ሁሉ ቀውስ በኋላ ዛሬ ላይ የሩሲያ መንግሥት መሪዎች ያለ ፓትርያርኩ ቡራኬ የሚከውኑት መንግሥታዊ በዓላትና ታላላቅ ክንውኖች የሌለበት ሁኔታ ሊታይ ግድ ብሏል፡፡ መሪዎቿም ቤተክርስቲያን ሳሚዎች የሆኑበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡
እንግዲህ ወቅታዊ የዓለም አቀፍ ሁኔታ እንዲህ በሆነበት ሁኔታ ነው “ሞኝና ወረቀት ያሲያዙትን አይለቅም” እንዲሉ የኛዋ ግራ ዘመም ፖለቲከኛ ወ/ሮ ገነት ያኔ ያውም በተሳሳተ ግንዛቤ የጨበጡትን ሙጭጭ አድርገው ይዘው ከስንት ዐሥርት ዓመታት በኋላም በዕድሜ በልምድ በተሞክሮ ብዛት በትምህርትም ሳይለወጡ አሁንም “ግራ ዘመም ስለሆንኩ እንደዚህ ዘንደዚህ ዓይነቱን አልፈልገውም ደሞ የምን ምንትስ ነው እንደ ዛ የድሮው ደጅ አዝማች ቀኝ አዝማች!” እያሉ በዚያ ዘመን ቅኝት ማውራታቸው በጣም ነበር የደነቀኝ፡፡
አንዴ አንድ መድረክ ላይ ዶክተር ዳኛቸው (የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህርና ወያኔ በሀገራችን ላይ ያደረሰባትንና የጋረጠባትን ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ በተቻለው መጠን ባጋጠመው መድረክ ሁሉ እያጋለጠና እየሞገተ ያለ ምሁር) በኢሕአፓ ዘመን በነበረው ትውልድ ትግል ዙሪያ ላይ የተጻፈን መጽሐፍ በገመገመልን ወቅት ለዚያ ዘመን ትውልድ ያለኝ ግምት ወይም አቋም ከዶክተር ዳኛቸው ጋርም አጨቃጭቆጫል፡፡ ዶክተር ዳኛቸው እንደማንኛውም የዚያ ዘመን ሰው ሁሉ በተለይም እንደ የትግሉ አጋርነቱ ያን ትውልድ እያወደሰ እያሞካሸ መቸም ሊደገም የማይችል ትውልድ እያለ ነበር አቅርቦቱን (ፕረዘንቴሽኑን) ያቀረበው፡፡ በውይይቱ ላይ ሐሳብ አስተያየት እንዲሰጡ ዕድል ከተሰጣቸው ሰዎች አንዱ ነበርኩና ሐሳቤን ስሰጥ “እኔ የዚያ ዘመን ትውልድ ጀግና ምናምን በሚባለው ጉዳይ አልስማማም ስላልነበርኩበት ግን አይደለም ለኔ ጀግና ማለት ሞትን የሚጋፈጥ ሞትን የማይፈራ ማለት ሳይሆን የሚሞትለት ዓላማ ከሀገሩ ከማንነቱ አንጻር ሲታይ ባለው ጠቀሜታ የሚወሰን ነው ለኔ ያትውልድ ስሩን ከሀገሩ ከገዛ ከማንነቱ ነቅሎ አውሮፓ ላይ የተከለ ለገዛ ማንነቱ ሥልጣኔው ጠላት የሆነ ርዕዮተዓለሙም ኢትዮጵያዊ ያልነበረ ነውና በፍጹም ጀግና አልነበረም አባጭ የሚለው ስም ግን ይስማማዋል፡፡ ይሄው የጣለው የተከለብን ጠንቅም እስከዛሬ አልለቀቀንም ወደፊትም ገና ብዙ ያዳክረናል” አልኩ፡፡ አለዛ እኮ እነዮዲት ጉዲትን፣ እነ ግራኝ አሕመድን፣ በድፍረት መግደል ማጥፋት ማውደም የሚችሉበትን ዕድል ለራሳቸው የፈጠሩትን፣ ክፉ የጭካኔ እርኩስ መንፈስ ተጠናውቶት ያለምንም ምክንያት እየተነሣ በድፍረት የሚገለውን ሁሉ እኮ ጀግና ልንል ነው!
ይህ አስተያየቴ ለዶክተር ዳኛቸው በጣም አልተመቸውም ነበር “ያ ትውልድ ጀግና ካልተባለ ማን ሊባል ነው?” አለ “አንተን ደስ እንዲልህ ፈሪ ነው ልበል? ርዕዮተዓለሙ ኢትዮጵያዊ አይደለም ትላለህ መሬት ላራሹ ኢትዮጵያዊ አይደለም? የብሔር ጥያቄ ኢትዮጵያዊ አይደለም?” ሲል ጠየቀኝ መልስ ለመስጠት ዕድሉ እንዲሰጠኝ ጠየኩ አወያዩ አልፈቀደም እናንተ በግል ተወያዩ ያለንን ሰዓት በቀሪ ሐሳቦችና ጥያቄዎች ላይ እናተኩር በማለቱ ቀረ፡፡
በእርግጥ ወ/ሮ ገነት ዛሬ የዚያ ርዕዮተዓለም አፍላቂዎች በተውበት ዘመን የወደቀውን የነጭ ውራጅ አስተሳሰብ በተንጋደደ አረዳድ ጨብጠው ይዘው ዛሬም ማውራታቸው ወ/ሮዋ ለአሁኑ ትውልድ አርአያ የመሆን አቅም ኖሯቸው ይህ ትውልድም ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጥር በመፍራት አይደለም በዚህ ጉዳይ ላይ ትኩረት መስጠቴ፡፡ ነገር ግን የዚያን ዘመን እብደት እንዲገነዘብ እንዲታዘብ እንጅ፡፡ ወ/ሮ ገነት ግራ ዘመም ስለሆንኩ እያሉ በመንቀፍ ሊከተሉት እንደማይሹ ከገለጹት ነባር ባሕል ወግ ሥርዓት አንዱ ለጋብቻ ሽምግልና መላኩን ነው፡፡ ከዓመታት በፊት ይሄንን ጉዳይ አንድ እንደሳቸው ግራ ዘመም ወይም ተራማጅ ነኝ ባይ በሬዲዮ (በነጋሪተ ወግ) በሚተላለፍ ዝግጅት ላይ እየተቸ እንዲቀርም እየመከረ አሳች ሐሳቡን በጽሑፍ አስተላልፎ ስለነበርና ይህ ጉዳይ ዝም ተብሎ የሚታለፍ ስላልሆነብኝ በዚያው ዝግጅት ላይ ሰጥቸው የነበረው ምላሽ ይሄንን ይመስል ነበር፡፡
“ሌላው አቶ ተራማጅ ስለጋብቻ ሽማግሌ የመላክም ባሕል ኋላ ቀር ነው በማለት አጣጥለው ነቅፈዋል፡፡ ኋላቀሩ ባሕሉ ወይስ እርስዎ የሚለውን በአጭሩ እንይ አቶ ተራማጅ ምክንያት አድርገው ያቀረቡት በጣም አስቂኝ ነገር ነው የሆነብኝ፡፡ ምክንያትዎ ምን ነበር? 1ኛው ሽማግሌዎቹ ሄደው የሚያወሩት ነገር አብዛኛው ውሸት ስለሆነ የሚል ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ተጋቢዎቹ መጀመሪያ ተዋውቀው ተፈቃቅደው የጨረሱት ጉዳይ ነው፡፡ የሚለው ደግሞ ሌላኛ ውምክንያታቸው ነው፡፡
አቶ ተራማጅ ታዲያ በምን ሒሳብ ነው መፍትሔው ባሕሉን ማጥፋት ሊሆን የሚችለው? በትዳር ውስጥ የሚማግጡ ሰዎች አሉና ተብሎ ትዳር ይጥፋ ወይም ይቅር ይባላል እንዴ? ይሄስ ከበሰለ ጭንቅላት የፈለቀ በሳል የመፍትሔ ሐሳብ ነው? ነው ወይስ በትዳር ላይ የሚማግጡ ሰዎች እንዳይኖሩ የሚያስችሉ የማኅበራዊ ግንኙነትና አስተዳደር ሥራዎችን መሥራት? የትኛው ነው የበሰለ እና ማስተዋል የታከለበት የመፍት ሔሐሳብ? እንደዚሁም ሁሉ በሽምግልና የሚዋሹ ሰዎች አሉ ተብሎ ሽምግልና ይቅር አይባልም በሽምግልና ውሸት እንዲቀር መሥራት እንጂ፡፡ በዚህ ላይ አሁን ያለው ሽምግልና የሚላክበት ሁኔታ እና ሽምግልናን የፈጠረው የቀደመው ባሕላችን ሁኔታ ይለያያል፡፡ አንዱ ይሄ ነው ለሁለተኛው ምክንያትዎ ደግሞ እንደው እርስዎ ሲያስቡት አይደለም ልጅን ያህል ነገርና መርፌም እንኳ ቢሆን ሳይጠይቁ እና ሳያስፈቅዱ ከሰው ይወስዳሉ ይዋሳሉ እንዴ? ምን ነካዎት አቶ ተራማጅ? ምንም እንኳን ተጋቢዎቹ አስቀድመው የጨረሱት ጉዳይ ቢሆንም የወላጅ ፈቃድ ይሁንታና ቡራኬ እንዴት አያስፈልግም ጃል? ልጅን ያህል ነገር ማንነቱ ላልተነገረዎትና ለማያውቁት ሰው ባለቤት እንደሌለው እቃ ብድግ አድርጎ ሲወስድ ዝም ይሉታል እንዴ? ወይም ደግሞ ከሱቅ ገዝተው እንደሚተኩት እቃ ዝም ብለው ብድግ አድርገው ይሰጡታል እንዴ? ኧረ ከሱቅ የገዙት እቃም ቢሆን እንኳ ለማያውቁት ሰው ዝም ተብሎ ብድግ ተደርጐ አይሰጥም፡፡ አቶ ተራማጅ ለመሆኑ ሴት ልጅ አለዎት እንዴ? ይሄን ሲሉ እሷን አስበዋል? ምን ያህልስ ይሳሱላታል?
ለዚህ ዓይነት ስሕተት የዳረግዎትና ወደፊትም የሚዳርግዎት ምን እንደሆነ ልንገርዎት? እርስዎ ለማንነትዎ ለመለያዎ ያለዎት ግምትና የሚሰጡት ዋጋ ዝቅተኛ ወይም የተበላሸ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ የውስጥ የተበላሸ እምነትዎ የሆነ ነገራችንን ለመተቸት ሲያስቡ ትክክለኛ መመዘኛ እንዳይኖርዎ ከባድ ተጽእኖ ያሳድርብዎታል በመሆኑም ነገሩን በትክክል ለመረዳት ከስሩና ከተለያየ አቅጣጫ ማየት እንዳይችሉ ያደርግዎታል፡፡ እናም እናማ ከእንደዚህ ዓይነት ራስን ከባድ ትዝብት ላይ ከሚጥል ስሕተት ላይ ይጥልዎታል ማለት ነዋ፡፡ አቶ ተራማጅ ይህንን መልስ ለመስጠት የሚያስችል ጊዜ አልነበረኝም ተመሳሳይ ዓይነት የተሳሳተ አስተሳሰብ ያላቸው ዜጐች ብዙ በመሆናቸውና የተላለፈውም በፌዲዮ (በነጋሪተወግ) በመሆኑ ሊያሰናክሏቸው የሚችሏቸው ሰዎች ብዛት አሳስቦኝ በእርስዎ ምክንያትነት ማድረግ ያለብኝን አድርጌ በአጭሩ መልስ መስጠት እንዳለብኝ ስለተረዳሁእንጂ፡፡ ወደፊት እንደ ሁኔታው ለሚያቀርቧቸው ተመሳሳይ ጽሑፎች በተቻለኝ መጠን በሆደሰፊነት መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ፡፡ ነገር ግን እባክዎትን ለሚተቹት ነገር ጥልቅ የሆነ ምርመራ እና ግንዛቤ ደርዝ ያለው ምክንያታዊነት ይኑርዎት፡፡ በተቻለዎ መጠን ሚዛናዊ ይሁኑ እንደዚህኛው ዓይነት ጽሑፍዎት ግልብ አይሁን እንዲያም ሲል ደግሞ ለማንነትዎ ለመለያዎ ተቆርቋሪነትን ይጨምሩበት በትክክለኛ አተያይ ይሁን እንጂ የሚተች ወይም የሚነቀፍ ነገር ካለብንም ሳይሳቀቁ ይተቹ ይንቀፉ ነገር ግን የሚተቹብን ወይም የሚነቅፉብን ነገር የእኛ እንከን ብቻ ወይም ከሌሎች አንጻር ስንታይ የባስነው እኛ መሆናችንን እርግጠኛ ይሁኑ፡፡ በተረፈ እንደወረደ ስሜታዊነት በተንፀባረቀበት ሁኔታ ጽሑፉን ስለጻፍኩ ወይም መልስ ስለሰጠሁ ይቅርታዎ አይለየኝ” ብየ ነበር የመለስኩት ለወ/ሮ ገነትም ተስማሚ ሆኖ ስላገኘሁት ነው እዚህ ላይ ማንሣቴ፡፡
በጣም የገረመኝ ነገር ቢኖር ሌላው ቀርቶ ወ/ሮ ገነት ግራ አዝማች ቀኝ አዝማች ደጅ አዝማች የማሳሰሉት አገርኛ የጦር መሪዎች ሥያሜዎችን መጥላት ለወ/ሮ ገነት ግራ ዘመምነት ነው፡፡ ጋዜጠኛ ወ/ሮ መዓዛ ውይይታቸውን ሲጀምሩ ወ/ሮ ገነትን በቅርቡ ፒ.ኤች.ዲዎን ሠርተዋልና ዶክተር እያልኩ ልጥራዎት ወይ? ብላ ብትጠይቃቸው ወ/ሮዋ ምን አሉ? ከህክምና ዶክተሮች በቀር ያሉ ባለ ፒ.ኤች.ዲዎች ዶክተር ተብለው መጠራታቸው ትክክል እንዳልሆነ ተናግረው ሲያበቁ “አሁንማ በምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው ሁሉ ኢንጂኒየር እየተባለ ይጠራ ጀመር እኮ!” ሲሉ አሸሞሩ ቀጠሉና “እኔ ዶክተር እከሌ ኢንጂነር እከሌ ሲባል እንደድሮው ደጅ አዝማች እከሌ ቀኝ አዝማች እከሌ የተባሉ ነው የሚመስለኝ” በማለት ያልበሰለና አስገራሚ አስተሳሰባቸውን ገለጡልን፡፡ ቆይ እኔን የሚገርመኝ ወ/ሮ ገነት በዛሬው ዘመን ጄኔራል እከሌ ኮሎኔል እከሌ ሲባል ግን ይመችዎታል አይደል? በባዕድ ቃል የሚጠራው የጦር መሪዎች ሥያሜ ሲስማማዎት ሀገርኛው ግን ያቅለሸልሽዎታል ለምን? ግራ ዘመም በመሆንዎ የራሳችንን መጥላት ስላለብዎ ይሆን? ለመሆኑ የዚህችን ሀገር ነጻነት ያለእነዚህ የጦር መሪዎች ለማሰብ ይችላሉ? አዎ በእርግጥ ታሪክ ሠሪው ሰፊው ሕዝብ ነው ነገር ግን ንብ ያለ አውራው ይሰማራል ይዘምታል እንዴ? የትኛው ሕዝብና የት ነው ያለ መሪ ታሪክ የሠራ? ለምንም ጉዳይ ቢሆን ሲያስቡት አመራር ሳይኖር ሕዝብ እንዴት ሊሠማራና ሥራውን ጉዳዩን ሊከውን ይችላል? የጥላቻዎ ምንጭ ምን እንደሆነ ልንገርዎ? ከቅጥረኛነትዎ የተነሣ እውስጥዎ ያለው የጸረ ኢትዮጵያ ስሜትዎ ነው እንዲህ እንዲያስቡ የሚያደርግዎት፡፡
ለዚህም ነው ኢትዮጵያን ለ40 ዓመታት ያህል ወራ አማራን (የነገሥታቱንና የክርስቲያኑን ወገን) ከአክሱምና አካባቢው መንጥራ ባጠፋችው የተቀረውንም እንዲሰደድና እንዲበተን ባደረገችው፣ አብያተመንግሥታቱንና አብያተክርስቲያናቱን በውስጣቸውም የያዙትን ቅርሳቅርሶች አቃጥላ አፈራርሳና አውድማ የሀገሪቱን ሥልጣኔ ሀብትና የሰው ኃይሏን አጥፍታ ሀገሪቱን ለከፋችግር በዳረገችው ከዚህ ክፉ ሥራዋ በስተቀር አንዲት እንኳን መልካም ሥራ የሚጠቀስ ነገር በሌላት የጥፋት ልጅ በዮዲት ጉዲት ሲጠሩ ኩራት የተሰማዎት፡፡ በቀረቡበት መድረክ ሁሉ ዮዲት ጉዲት ስለ መባልዎ በተጠየቁ ቁጥር መልካም ሥራ ሠርታ እንዳለፈች ሁሉ “እሷ እኮ ታሪክ አላት” እያሉ የሌላትን መልካም ገጽታ ለማስያዝ ጥረት የሚያደርጉት፡፡ ለመሆኑ ምንድን ነው ይሄ ታሪኳ? ተብለው ቢጠየቁ ምን ብለው ሊመልሱ ነው? እርስዎ እኮ አያፍሩም “ሀገር ስላቃጠለች” ይሉ ይሆናል፡፡ ሌላ ሊባል የሚችል ነገር የላትማ! አየ ወ/ሮ ገነት፡፡ እንዴ! እንዴ! አንድ ነገር ትውስ አለኝ ይሄ ባለፈው ሰሞን “እኔ ተሰውሬ የነበርኩት ነቢዩ ኤልያስ ነኝ ከብሔረ ሕያዋን መጣሁ” እያለ ስንት የዋሀንን ያጃጃለው አይሑድ “ዮዲት ጉዲት ሀገር አልሚ እንጅ ታሪክ አለ እንደምትሉት ሀገር አጥፊ አይደለችም ስሟን ሲያጠፉ ነው” እያለ እንዲሰብክ ያደረጉት እርስዎ ይሆኑ? መቸም አያደርጉም አይባሉም እኮ ጠረጠርኩ፡፡
እናም ለዚህ ነው በእሷ ስም መጠራትዎት ሊያኮራዎት እንጅ ሊያሸማቅቅዎት ያልቻለው፡፡ ከወያኔም ጋር እንዲያብሩና ከዚህ የጥፋት ጎጠኛ ቡድን ጋር ተሰልፈው ማጥፋትዎ ቅንጣት ሊሰማዎት ያልቻለውና መልካም እንደሠራ ሰው የሚያንቀባርርዎት፡፡ አየ ድንቁርና፡፡ ወ/ሮ መዓዛ “ፕሮፌሰር ዐሥራት ዮዲት ጉዲት ብለው ስም አወጡልዎት” ብላ ስትጠይቅዎት እኔ በዐይነ ሕሊናየ እንዴት እንደሚሆኑ የሣልኩዎት እንደተኮነነች ነፍስ ሽምቅቅ እንደሚሉ አድርጌ ነበር፡፡ ቢሉም ግን ይሄንን የተሰማዎትን መጥፎ ስሜት ደብቀው ምንም እንዳልተሰማዎት አስመስለው የሆነ ነገር ይመልሳሉ ብየ ስጠብቅ እርስዎ ግን እውነተ ጉዲት አስደሳች ነገር እንደሰሙ ሁሉ እየተፍነከነኩና ኩራት እየተሰማዎት “እሷ እኮ ታሪክ ያላት ናት” ብለው ሲመልሱ አሁን እኒህ ሴትዮ ምናቸው ነው የተማረው? ብየ ነበር እራሴን የጠየኩት፡፡
በነገራችን ላይ ፕሮፌሰር ዐሥራት እርስዎን ዮዲት ጉዲት ብለው ስም ሲያወጡልዎት እርስዎ እሽ እያሉ ለምን? እንዴት? ሳይሉ በፍጹም ታዛዥነት ለጥፋት ቡድኑ መጠቀሚያ በመሆን ወያኔ እርስዎን ብዙ ያስጠፋዎታል ብለው በማሰብ እንጅ በራስዎ በጭንቅላትዎ አስበው የመወሰን ሥልጣን ኖሮዎት የሚያደርጉት ነገር ይኖራል ብለው ያንን ከመፍራት እንዳልሆነ ጠንቅቀው የሚያውቁት ይመስለኛል፡፡
ለምሳሌ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተባረሩት የ41ዱን ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች በእርግጥ የተባረሩት 42 ነበሩ አንደኛው ግን አቶ ማንትስ የተባለው ሳይገባው ከእነሱ ጋር ተቆጥሮ የተባረረና ወዲያውም የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ የሆነ በመሆኑ የእሱ መቀነስ ትክክል ነው፡፡ እናም እነኝህ 41 ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች ሲባረሩ የእርስዎ የግል ውሳኔ ሊሆን እንደማይችል ማንም ሊረዳው የሚችለው ጉዳይ ነው፡፡ የዚህም ማረጋገጫ የሚሆነው እነሱን ካባረሩ በኋላ እነሱ ይሰጧቸው የነበሩትን ኮርሶች እነሱ ባስተማሯቸው በፍሬሽ (ደራሽ) ተመራቂዎች እንዲሸፈኑ መደረጉና ከፊሎቹ ዲፓርትመንቶችም (ክፍል ጥናቶች) ከናካቴው ተዘግተው መቅረታቸው ነው፡፡ ይህ የደነቆረ ፖለቲካዊ ውሳኔ መሆኑን እንጅ አሥተዳደራዊ ውሳኔ መሆኑን አያሳይም፡፡ የሚገርመው ይሄንን ካደረጋቹህ በኋላ የተከተለው ችግር እውነቱ ፈጦ እየታየ የብቃት ማነስ ብላቹህ መናገራቹህ ነው፡፡ ይሄ ምላሻቹህ የእነሱ ጉዳይ በተነሣ ቁጥር የምትሰጡት አሳፋሪ ምክንያት እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ከ12 ዓመታት በፊት በፋና ሬዲዮ የቀጥታ የስልክ ውይይት ላይ ይሄንን ጉዳይ አንስቸ ወያኔን በምወቅስበት ጊዜ አንድ የወያኔ ሹም የሥራ ኃላፊ የመለሰው መልስ አሁን እርስዎ የተናገሩትን ነው፡፡ የብቃት ማነስ የተባውን ክስ ሐሰተኛነት እንዲያጋልጡ አስከትየ ላቀረብኩለት ጥያቄዎች ግን ከመርበትበት በስተቀር ሊያቀርበው የቻለው በልስ አልነበረም፡፡
እርስዎም እንዲህ በይ ተብለው ያኔ የተሰጥዎትን መልስ ሳይረሱ ከስንት ዓመታት በኋላም ያችኑ ሳይጨምሩ ሳይቀንሱ ተፏት፡፡ ሞጋች ጋዜጠኛ ስላላጋጠምዎት ዕድለኛ ነበሩ ሐሰተኛ ምክንያት ሰጥተው ተሳድበውም ለማለፍ ቻሉ፡፡ ከዚህ ውጭ ያለው ምክንያት እውነተኛውና ትክክለኛው በመሆኑ ሰዎቹ እንደዜጋና እንደምሁር በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በያገባኛል ስሜት ምሁራዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት መጣራቸው ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው በመሆኑና በዚህ ምክንያት ሰውን ከሥራ ገበታው ማባረር አንባገነንነታቹህን የሚያጋልጥ ስለሆነ ከመዋሸት ውጭ አማራጭ አልነበራቹህም፡፡ ባይሆን የምትሰጡት ሐሰተኛ ምክንያት በቅጡ (ቴክኒክሊ) ሲታይ ሐሰትነቱ በቀላሉ ሊታወቅ የማይችል ማድረግ ግን ነበረባቹህ፡፡ በነገራችን ላይ ይህች አሁን እርስዎ ያሏት ምክንያት እኮ ተሽራ ተሳስተን ነው በሚል በ1997ዓ.ም. በአቶ መለስ ተቀይሯል አልሰሙም ማለት ነው? ወ/ሮ ገነት እንዲያው ግን ሌላው ሌላውን ይተውትና ደርግን “ምሁራንን እንዲሰደዱ ያደረገ የተማረው ክፍል ጠላት ነው!” እያሉ ለሚከሱና ለሚንገበገቡ ዱላውንም ለቀመሱ ለእርስዎ ለሕሊናዎ ይሄንን የማባረር ውሳኔ እንደምን በጸጋ ሊቀበሉት ቻሉ፡፡ ነው ወይስ ያ ስሜትዎ የውሸት ነበር? አዎ በእርግጥም የውሸት ነው፡፡ ስለ ሰብአዊ መብቶችና ደርግ በዜጎች ላይ ስለፈጸመው ግፍ እንደዚያ በስሜት የሚናገሩት የውሸትና የማስመሰል ነው፡፡ ልጅዎ ምን አድርጎ ሥልጣንዎን መከታ በማድረግ ኃይልዎን አላግባብ በመጠቀም ምን እንዳይደረግ እንዳደረጉ የሚረሱት አይመስለኝም፡፡ ወ/ሮ ገነት እስኪ ለአንድ አፍታ እራስዎን በሰለባ ቤተሰብ ቦታ አድርገው ያን አደጋ ለማሰብ ይሞክሩ? ምን ተሰማዎት? ሲጀመር የሰብአዊና የዜጎች መብት የሚያንገበግበው የሚቆረቁረው የሚሰማው ቅንና ስስ ልብ ቢኖርዎት ኖሮ በምንም ተአምር ወያኔ ሊሆኑና ወያኔነት ሊስማማዎት ባልቻለ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ደሞ አማራ ሆነው! አይ ወ/ሮ ገነት አማራ ነኝ ሲሉ ግን ትንሽ አያፍሩም? መቸም ወያኔ ለአማራ ምን አስቦለት ሥልጣን ከያዘ ማግስት ጀምሮ ምን ሥልጣን ከያዘ ገና በረሀ እያለ ጀምሮ ምን አስቦበት እስከአሁንም ምን እያደረገው እንደሆነ በገሀድ በአደባባይ የሚታይ ነገር ነውና ከሆድዎ ሻገር ብሎ ማሰብ የሚችል ጭንቅላት ስለሌለዎት እንጅ ነጋሪ የሚያስፈልግዎ አልነበረም፡፡ እባክዎን አማራ ነኝ አይበሉ እንዳልሆኑ እኔ እነግርዎታለሁ፡፡ ስለዚህ ወ/ሮ ገነት የሚያስብ ጭንቅላት ካለዎት እርስዎ ምንም ሊሉ የሚችሉበት አፍ የለዎትምና ነውረኛ ማንነትዎን እንደታቀፉ ነግቶ ውርደትዎን እስኪከናነቡ ድረስ አርፈው ይቀመጡ እሽ?
እስከአሁን ድረስ እኔ በእርግጠኝነት የድንቁርና ምንጩ ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ በተፈጥሮው ደንቆሮ የሆነ እንደሌለ ግን እርግጠኛ ነኝ፡፡ የድንቁርና ካፋቱ ልክን አለማሳወቁ ሰውን ያለ ፍርሐትና ሐፍረት በድፍረት ማናገሩ ነው፡፡ ወ/ሮ ገነት “የኢትዮጵያ ሴቶች” ብለው አጠቃለው በመጀመል ሀገራችን ኢትዮጵያ ሴቶችን በተመለከተ ተስተካካይ የሌለውን ቀና አስተሳሰብና በሀገራችን ታሪክ ሴቶች ምን ያህል ቦታ እንደነበራቸው ማጤን ይገባቸው እንደነበር መጽሐፍ ለመጻፍ የተነሣ ሰው አይደለም የቡና ወሬ ለሚያወራ ሰው እንኳ የሚዘነጋ ጉዳይ አልነበረም፡፡ ወ/ሮ ገነትን ግን ይሄ ጉዳይ ጨርሶ አላሳሰባቸውም እንዲያው ብቻ አፋቸው እንዳመጣላቸው “ሴቶች በኢትዮጵያ እንደሰው አይቆጠሩም” ሲሉ በውይይታቸውም ያውም አእላፋት እየሰሙ ይሄ የቅጥረኛነት አጀንዳቸው እውነት መስሎ እንዲታሰብላቸው በሀገራችን የሴቶችን ገናናነት የሚመሰክረው ታሪክ የያዘው የሀገራችን ታሪክ ድራሹ እንዲጠፋላቸው እየተመኙ የደደረ ድንቁርናቸውን በሚቀፍ መልኩ ሲያሳዩን ቅንጣት እንኳን አልተሰማቸውም፡፡ ወ/ሮ ገነት እርስዎ እንደሰው ሳይቆጠሩ ኖረው ከሆነ ይሄ ከራስዎ ከግል ማንነትዎ ጋር በተያያዘ የራስዎ ችግር እንጅ የሀገሬና የወገኔ ችግር እንዳልሆነ ላረጋግጥልዎት እወዳለሁ፡፡
ወ/ሮ ገነት ለመሆኑ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሴቶች ብቃት እንዳላቸው አውቃ በታሪኳ ከ15 በላይ ሴቶችን ለመጨረሻው የሥልጣን ደረጃ ያበቃች ሀገር እንደሆነች ያውቃሉ? ግራ ዘመም ስለሆንኩ ነባሩን የሀገር ማንነት ባሕል እሴቶችን በሙሉ መጥላት አለብኝ ብለው እያሰቡ እንዴት ብለው ሊያውቁ ይችላሉ? ይሄንን የሀገሬን ስኬት እርስዎን ቀጥረው የራሳቸውን ችግር የእኛ ችግር እንደሆነ አድርገው በእርስዎና በመሰሎችዎ አፍ የሚናገሩት አውሮፓውያን እንኳን አግኝተውት ያውቃሉ? አይደለም 15 አንድ እንኳን አይደለም በጥንት ዘመን አሁን ሠለጠን በሚሉበት ዘመን እንኳን ያሳኩ ሀገራትን ሊጠቅሱልኝ ይችላሉ? እኔ ግራ ዘመም ነኝና ይሄንን ታሪካቹህን መቀበል መመስከር አልችልም ብለው የሚያምኑ ቢሆንም እንኳን ዝም ይባላል እንጅ ታዲያ እንደሌለ አድርገው ያወራሉ እንዴ! ነውር አይደለም? ለነገሩ እርስዎ ነውር የት ያውቁና፡፡
ወ/ሮ እርስዎ እያሉ ያሉት “ሀገራችን ሴቶች ሴት በመሆናቸው ብቻ የሚጠቁባት ሀገር ናት” ነው የሚሉት እኔ ደግሞ ፍጹም ሐሰት ነው እያልኩዎት ነው ያለሁት፡፡ ምክንያቱም ሴቶችን የሚያጠቁ ወይም የሚበድሉ ባሎች ወይም ጓደኞች ወይም ወንድሞችን ስናይ ሴቶቻቸውን የሚያጠቋቸው ሴት ስለሆኑ ወይም ወንድ ስላልሆኑ አይደለምና፡፡ ሴት ስለሆነች ወይም ወንድ ስላልሆነች ብቻ ጥቃት የሚያደርስ ሰው ካለ እስካሁን ሰምቼ ዐይቸም አላውቅም ይኖራል ብዬም አልገምትም አለ ከተባለ ግን ይህ ሰው ጤነኛ ባለመሆኑና ለየት ያለ (Exceptional) በመሆኑ ጉዳዩ መታየት ያለበት በተለየ ሁኔታና ቦታ እንበል ለምሳሌ በአእምሮ ሕሙማን ማዕከላት ዓይነት ቦታ ነው፡፡
ጉዳዩ ወይም ችግሩ ግን ፈጽሞ የማኅበረሰቡ ተደርጎ መታየት የለበትም፡፡ ይህንን ካደረግን ግን ማኅበረሰቡን መስደብና ማዋረዳችን ነው፡፡ በደል የተፈጸመባቸውን ሴቶች የበደል ዓይነቶች ያየን እንደሆነ እነዚያ የተፈጸሙ በደሎች ሁሉም በተመሳሳይ ሁኔታ በወንዶችም ላይ የሚፈጸሙ ናቸውና፡፡ በመሆኑም በደሉ የተፈጸመባት ሴት ያ በደል የተፈጸመባት ሴት በመሆኗ አይደለም ማለት ነው፡፡ ታዲያ ምንድነው? ያልን እንደሆነ በጉልበትና በመሳሰሉት ነገሮች በደል ከሚያደርሰው ሰው ያነሰች ስለሆነች ነዋ! በማነሷም በጉልበት ከእሱ ማነሷን ምቹ ሁኔታ ተጠቅሞ ከእሷ የሚፈልገውን ነገር ለማግኘት ወይም ለመበዝበዝ ነው፡፡ ወንዶች ያላቸውን ጉልበት የሴቶች ሴቶች ያላቸውን የአቅም ውሱንነት ለወንዶች አድርገን ብናስበው ይህ አሁን በሴቶች ላይ እየተፈጸመ ነው ያሉት ችግር ሁሉ የሚታሰብ ባልሆነም ነበር፡፡ በመሆኑም ጉዳዩ የጉልበተኞች እና የአቅመ ውስኖች ጉዳይ እንጂ በፍጹም የጾታ ጉዳይ ወይም ሴት እና ወንድ የመሆን ጉዳይ አይደለም ማለት አይመስልዎትም ወ/ሮ ገነት? በወንዶችም ላይ የሚፈጸመው ይሄው ነውና፡፡ ጉልበተኛው አቅመ ቢሱን ወይም ደከም ያለውን ሲጎዳው ሲያጠቃው ሲበድለው ሲበዘብዘው እንደሚታየው ሁሉ ማለት ነው፡፡ ሕፃናት ወንዶች አንዳንዴም አዋቂ ወንዶች ለመግለጽ የሚቀፍ የጥቃት ሰለባ እየሆኑ ባሉበት ሁኔታ የጥቃት ዓይነቶችን በፆታ ወስነን እንዴት ነው የሴቶች እንደዚህ ልንል የምንችለው? ፆታ የለየ ጥቃት ከሌለስ እንዴት ነው ጥቃትንና ፆታን ልናያይዝ የምንችለው?
በዚህም ምክንያት የሴቶች ምንትስ የሴቶች እንደዚህ አሁንም የሴቶች ቅብርጥስ የሚባሉ ነገሮች ሁሉ ችግሩንና ጉዳዩን በትክክል ማየት መግለጽ መወከል ካለመቻላቸው የተነሣ ሥያሜዎቹ ፈጽሞ አይመቹኝም፡፡ ይሄ እንዲያውም የእናንተ ቁማር ይመስለኛል፡፡ ኅብረተሰቡን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር ሲያቅታቹህ ወይም ከማኅበረሰቡ ለሚሰነዘሩ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ሲሳናቹህ የማኅበረሰቡን ትኩረት ማስቀየሻ እና ከእናንተ ላይ ዞር ማድረጊያ ለዚያ ማኅበረሰብ እዚያው ባለበት የሚይዝላቹህን ፆታን እና የመሳሰሉትን ርእሰ ጉዳዮች መሠረት ያደረጉ የተለያዩ የቤት ሥራዎችን ሆን ብላቹህ ትፈጥራላቹህ፡፡ ይሄም እንግዲህ ከቤት ሥራዎቹ አንዱ መሆኑ ነው፡፡ ይህን ስል ግን ለተገፉ ወይም ለተጠቁ ሰዎች ጥብቅና አይቆም ይረሱ ይገለሉ ማለቴ እንዳልሆነ መረዳት የሚችል ጭንቅላት ያለው ሰው ሁሉ ይረዳኛል ብዬ እገምታለሁ፡፡ ነገር ግን ዓላማችን የተገፉትን ወይም የተጠቁትን ሰዎች መብት ማስከበር ወይም ማስጠበቅ ከሆነ፤ይሄንንም ለማድረግ አቅምን አይቶ ወይም ገምቶ በአቅም ውስንነት ምክንያት በተወሰኑ የማኅበረሰብ ክፍል ላይ ብቻ አትኩሮ መሥራት ካስፈለገ ወይም ግድ ካለ፤ በተሳሳተ ሚዛን ጾታን መሠረት ባደረገ ሥያሜ በጅምላ የሴቶች መብት በማለት ሳይሆን የተጠቂ ሴቶች ጉዳይ ወይም የተበደሉ የግፉአን ማለትም የተገፉ ሴቶች መብት ተከራካሪ ወይም አስጠባቂ ቢባል ትክክለኛ ሥያሜ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ምክንያቱም የማይጠቁና ያልተጠቁ ሴቶች አሉና፣ ያልተገፉና የማይገፉ ሴቶች አሉና፣ የተከበሩ እና የሚከበሩ ሴቶች አሉና ለእኛ ለሐበሾች ይሄ ሊነገረንና በዚህ ልንታማ ጨርሶ የሚገባ ጉዳይ አልነበረም፡፡ ከተሞከረም ድፍረት ነው፡፡
ማንም ነጭ ለእኛ ለሐበሾች አፍ አለኝ ብሎ እና ደፍሮ በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ሐበሻን እንደ ሐበሻ ሊነቅፍ ወይም ሊኮንን የሚችልበት የሞራል (የቅስም) አቅም ብቃትና ነፃነት ከቶውንም የለውም፡፡ በታሪኩ የሴት መሪ አይቶ ወይም አግኝቶ ወይም አብቅቶ የማያውቅ ድኩም ኅብረተሰብ ከቀዳማዊት ሳባ (ከዛሬ 4380-4370 ለ10 ዓመታት የነገሠች) ጀምሮ እስከ ቀዳማዊት ዘውዲቱ ከ15 በላይ ገናና ብልህ አስተዋይ ብቁ ሴቶችን ያፈራንና ያበቃን ሕዝብ እና ሀገር ሊነቅፍ ሊመክር ሊኮንን ሊተች የሚችልበት ኧረ በየትኛው ሒሳብ ይሆን ወ/ሮ ገነት? እንደ አለመታደል ሆኖ በዚህ ዘመን ካለን ሐበሾች ጥቂት የማንባለው አፈር ያብላንና ለነገሩ በልተናል ከዚህ በላይ አፈር መብላት የት አለና፡፡ ክብራችንን ዋጋችንን (ቫልዩአችንን) ባለማወቅ የዚያ ችግር ባለቤት ወይም ተጠቂ የሆኑ የበርካታ ምዕራባዊያን ሀገሮች ጩኸት ሴቶችን ለመሪነት ማብቃት አይደለም ለሴቶች እንደ ሰው የሰውነት መብት ከሰጡ እንኳን ከአንድ የእድሜ ባለጸጋ እድሜ የማያልፉትን፣ የሴቶችን ሰብአዊ መብቶች ሕገ መንግሥቶቻቸውን ጨምሮ በተጻፉ ሕጎቻቸው ሁሉ በይፋ የደፈለቁትን ኅብረተሰቦች ወይም ሀገሮች ጩኸት የሴቶችና የወንዶች የሚል ልዩነት ሳታደርግ እስከ የመጨረሻው የሥልጣን ደረጃ አብቅታ ባረጋገጠች ሀገር፣ ሴት ልጅ ክብሯን ለመጠበቅ ካልሆነ በቀር ጾታዋን እንደበደል እንደእርግማን በመቁጠር ምንም ዓይነት ገደብ አድርጎ በማያውቅ ኅብረተሰብና ሀገር ኢትዮጵያ ውስጥ በእኛው በሐበሾች አፍ ስንጮኸው ጉዳዩ ምን ያህል አሳዛኝና ልብ የሚሠብር እንደሆነና በዚህ ዘመን ያለነውን ሐበሾች ያለንበትን የሞራል (የንቃተ ወኔ) ዝለት፣ ኪሳራና ዝቅጠት የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡
ምንአልባት አንዳንድ የሚታዩ የሚመስሉ ነገሮች ካሉ ወይም ቢኖሩ እነኚህ የድህነት ገጽታችን የፈጠራቸው ሳንኮች የድሀነታችን መገለጫዎች እንጂ በፍጹም እንደ ሐበሻ የባሕላችን አካል ወይም የአስተሳሰባችን ደረጃ ሆነው አይደለም፡፡ አስተዋይ ልቡና ያለው ማንኛውም ሰው ይህንን በሚገባ ይረዳል፡፡ ሀገራችን ለሴቶች ያላት ክብርና ቦታ ተወዳዳሪ የሌለው ነው ይሄንንም አድርገን አሳይተናል፡፡ በሀገራችን እግዚአብሔር እንኳን በወንድ ብቻ አይጠራም በሴትም እንጅ ቅድስት ሥላሴ ተብሎ፡፡ ሀገርም እራሷ የምትጠራው በሴት ስም ነው እናት ሀገር በመባል፡፡ ሌሎች የሚወደዱ ነገሮች ሁሉ በሴት ስም ነው የሚጠሩት፡፡ ከዚህ በላይ የጾታ እኩልነት የት አለ? እስኪ ይሄንን የአስተሳሰብ ጣራ እንደኛ አንድ ሳያጓድል በቋንቋው በባሕሉ በሥልጣኔው የያዘ ሀገርና ሕዝብ ይጥሩልኝ?
ይሄን ይሄን እኮነው ድንቁርና የምልዎት ወ/ሮ ገነት፡፡ የምለው ነገር ሁሉ ይገባዎታል ግን? በእርግጥ ድንቁርና እኮ የሌለበት ሰው የለም ምን ያህል በማን ላይ ይጠናበታል ይገንበታል የሚለው ነው የሚለያየው እንጅ ሁሉም ሰው እኮ ድንቁርና አለበት፡፡ ምን ሰብስቦ አንድ ላይ እንዳጎራቹህ እንጃ እንጅ በወያኔ ቤት ያለው ድንቁርናና የደናቁርት ዓይነትና ብዛትማ ለጉድ ነው!
ድንቁርና አነስተኛም ሊሆን ይችል ይሆናል እንጅ የቀለም ቀንድ የበቃ ምሁር በሚባል ሰውም አይጠፋም፡፡ በትምህርት የሚወገድ የድንቁርና ዓይነት አለ በሌላ በኩል ደግሞ ፕሮፌሰር ተብሎም ፊደል ካልቆጠረ መሐይም በማይሻል መልኩ ድንቁርናውን ትምህርት የማያጠፋለት የሰው ዓይነትም አለ፡፡ የእርስዎ ድንቁርና መገለጫዎችን ልንገርዎት? በካፈርኩ አይመልሰኝ ፈረስ ሽምጥ መጋለብዎት፣ በእልሀቸው እያሉ በጥፋት ላይ ጥፋት በመደረብ ጌቶቸ ለሚሏቸው ምቹ አጋሰስ መሆንዎ፣ ምክንያታዊ አለመሆንዎ፣ ከተኮነንኩ አይቀር በሚል አስተሳሰብ በየትኛውም ቦታ በመቸም ሰዓት ገዢ ለሆኑ እውነቶች ለመገዛት አለመፍቀድዎ ለሞራል (ለቅስም) ድንጋጌዎች ጨርሶ ለመገዛትና ለመዳኘት አለመፍቀድዎና ጭራሽም ዐይንዎን በጨው አጥበው ሰው ምን ይለኛል ሳይሉ እየፈጠሩ እየቀጠፉ እየዋሹ ማውራትዎ ወዘተ. ናቸው፡፡ ያው ወያኔ ሆኖ ሕሊናንና ጭንቅላትን መጠቀም አይቻልም አይደል? እንዴት ብለው ታዲያ ከዚህ የድንቁርና በሽታ ይድናሉ? ያው መቸስ ቢጤ ከቢጤው ጋር አይደል የሚቧደነው? ወያኔ ሊሆኑ የቻሉትስ እንዲህ ዓይነት ሰው በመሆንዎም አይደል? እንጅ አሁን ማን ይሙትና የወያኔ ማንነት ማንን መማረክ ማንን ማታለል ይችላልና ነው ወያኔ የሆኑት? ደርግ የፖለቲካ ተቃዋሚዎቸ ናቸው በሚላቸው ላይ ግድያን ለሁለትና ሦስት ዓመታት የፈጸመውን ግፍ ወያኔ በዚህኛው ላይ ጠላትና መጥፋት ያለበት ብሎ የፈረጀውን ብሔረሰብ ጨምሮበት በከፋ መልኩ በግልጽም በስውርም ለ23 ዓመታት እየፈጸመው ያለውን ግፍ በደል ኢሰብአዊ ድርጊቶች ሳያውቁ ሳይሰሙ ቀርተው አይደለም፡፡ ዛሬ እነሱ እንኳን በሥራቸው አፍረው ሞራልም (ንቃትም) አጥተው እንደ ድሮው ደፍረው ማውራት በተውበት ዘመን ይህ ሥርዓት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ ለእኩልነት የቆመ እንደሆነ አድርገው የሚወሸክቱት፡፡
ስለ ትምህርት ሥርዓቱ በሌላ ጽሑፍ እመጣልዎታለሁ ነገር ግን “ላለው የትምህርት ጥራት ማሽቆልቆል ተጠያቂው መምህሩ ነው ፖለቲካዊ በሆነ ምክንያት የትምህርት ሥርዓቱን ስላልተቀበለው” ማለትዎ ያልተቀበለበት ምክንያት ፖለቲካዊ ብቻ አይደለም እንጅ እውነትነት አለው፡፡ እንዲህ ከፊል እውነት መናገርዎም ጥሩ ነው ይበርቱ፡፡ ስለዚህ ወ/ሮ ገነት በሕዝብ ዘንድ ያላቹህን ተቀባይነት በሚገባ ያውቁታል ማለት ነው፡፡ መምህሩ ብቻ አይደለም የማይቀበላቹህ፡፡ መምህሩ ከሌላው ማኅበረሰብ ተነጥሎ ሊጠላቹህ ላይቀበላቹህ የሚችልበት ምክንያት ሊኖር አይችልም፡፡ ምክንያቱም መምህራን የኅብረተሰቡ አንኳር አካል እንጅ ከሌላ ዓለም የመጡ ልዩ ፍጥረቶች አይደሉምና፡፡ ሕዝብ ወዶ መርጦን እያላቹህ የምትወሸክቱት ውሸት መሆኑን ስላረጋገጡልን እናመሰግናለን፡፡ ስለዚህ በሌላ ጊዜ ሕዝብ መርጦን ፖሊሲያችንን (መመሪያዎቻችንን) ወዶልን ነው እያሥተዳደርን ያለነው ብለው ደግመው እንደማይዋሹን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ አይደል ወ/ሮ ገነት?
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
http://www.goolgule.com/genet-zewdie-is-it-really-how-it-is/