FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Saturday, December 1, 2012

አሁንም የተሃድሶ ያለህ!!!


(ርዕሰ አንቀጽ)
intellectual reform



“አንድነትን ስንመሰርት በቅንጅት ወቅት ስለሰራነው ጥፋትና የፖለቲካ ስህተት የገመገምነው ነገር የለም” ዶ/ር ያዕቆብ ሃ/ማርያም አንድነት ፓርቲን ከቅንጅት ጋር በማነጻጸር ከተናገሩት፡፡
በኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፓርቲና ድርጅቶች መዋቅራዊ ጥንካሬና ደጋፊዎቻቸውን አስተባብረው ውጤት ማስመዝገብ ያለመቻላቸው ጉዳይ አነጋጋሪ ነው። ተቃውሞ በኢትዮጵያ በፓርቲ መሪዎችና በገዢው ኢህአዴግ መካከል የሚደረግ እሰጥ አገባ ካልሆነ በስተቀር በደጋፊዎች ተሳትፎ ገዢውን ፓርቲ የማስገደድና እጁን የመጠምዘዝ ደረጃ ላይ ደርሶ ሊታይ አልቻለም።  ከቅንጅት መፈራረስና ልዕልናው መክሰም ጋር የህዝብ ስሜትም አብሮ ተዳፍኗል የሚለው አስተያየት ሚዛን የደፋ የሚሆንባቸው የበዙት ለዚሁ ነው። በድርጅት ደረጃ ችግሩን ተመልክተው ስለመታደስ የሚያስቡ ስለመኖራቸው ግን ለረዥም ጊዜ አልሰማንም።
በኢትዮጵያ ህዝብን ለትግልና ለእምቢተኝነት የሚያነሳሱ ጉዳዮች ሞልተው የፈሰሱ ቢሆንም ህዝብ በስርዓቱ ከመበሳጨት የዘለለ እንቅስቃሴ አለማድረጉ ስርዓቱ ከዘረጋው የአፈና መዋቅር ጋር የሚያገናኙት ቢኖሩም በዋናነት የተቃዋሚዎች ድክመት ጎልቶ እንደሚታይ አሁን አሁን ይፋ እየሆነ ነው። በተለይም ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ሰሞኑን “የግል አስተያየቴ ነው” በማለት ያቀረቡት ጽሁፍ የችግሩ ቁልፍ ነውና ሁሉም ወገኖች አሰራራቸውን ሊፈትሹ እንደሚገባ ይሰማናል – አሁን!!
“ከኔ አመለካከት ጋር የማይስማሙ እንዳሉም እገነዘባለሁ፡፡ በበኩሌ ከኔ ጋር የማይስማሙትን አከብራለሁ፡፡ ሃሳባቸውንና አመለካከታቸውን ባልጋራና ባልስማማባቸውም እነሱንም ሆነ ሃሳባቸውን፣ አመለካከታቸውንና አቋማቸውን አዳምጣለሁ። አከብራለሁ፡፡ የመረጃ ስህተት ካለ ስህተቴን ለመቀበልና ለማረም ዝግጁ ነኝ፡፡ የኔን ሃሳብ፣ አመለካከትና አቋም የማይጋሩት ግን እንዲያዳምጡኝና እንዲያከብሩልኝ አደራ እላለሁ” ሲሉ የወቅቱን የአገራችንን ሁኔታና የወደፊቱን የትግል አቅጣጫ በተመለከተ ለመወያየት በተጠራ ስብሰባ ላይ የአንድነት ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ባቀረቡት ንግግር የተናገሩት ነው። ሌላስ ምን አሉ?
“ኅብረሰባችንን ስናይ ብሶተኛና የማጉረመርም ደረጃ ላይ እንጂ ተናድዶ ንዴቱን በእንቅስቃሴ ለማሳየት ዝግጁ የሆነበት ደረጃ ላይ የደረሰ አይመስልም፡፡ ብዙ የማህበራዊና የኢኮኖሚ ችግሮች አሉበት፡፡ ይህንን ሰቆቃውንና ብሶቱን ያማርራል፡፡ በይፋና በአደባባይ አይገልጽም፡፡ ብሶቱ በማጉረምረም ደረጃ የሚገልጽ ነው እንጂ በአጠቃላይ ወደ ኅብረተሰባዊ ንዴት አልተለወጠም፡፡ የተናጠል ንዴቶች አልፎ አልፎ ቢገለፁም ሠፊና የአጠቃላይ የኅብረተሰቡ አልሆኑም፡፡ እነዚህ የተናጠልና ትናንሽ ንዴቶች ወደ ተደራጀና የተቀናጀ ሕዝባዊ እምቢተኝነት እና የእምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች አልተለወጡም፡፡ በሌሎች አገሮች በዳቦ ወይም በነዳጅ ዋጋ ላይ ትንሽ ጭማሪ ከታየ የኅብረተሰቡ ንዴት ይገነፍላል፡፡ በኛ ህዝብ ዘንድ ግን ይህ አይታይም፡፡ ምልክት ከታየም ጥቂት፣ የተናጠል፣ ያልተደራጁና ያልተቀናጁ ናቸው” ነበር ያሉት።
አዎ!! ያለመደራጀት ችግር፣ የግንዛቤ ችግር፣ ደጋፊን አሳምኖ የመምራት ችግር፣ ከስህተትና ከውድቀት ያለመማር ችግር፣ የተሃድሶ ችግር፣ የእውቀት ተሃድሶ ችግር፣ የራዕይ ችግር፣ በስድብና ተቃውሞ ላይ ያተኮረ ትግል፣ ፍረጃና ማግለል ላይ የተንጠለጠለ የትግል ጉዞ፣ ካለፈው ያለመማርና ይሉኝታን ያዘለ ትግል፣ በግልጽ ራስንና ተሞክሮን ያለመገምገም ችግር፣ የተድበሰበሰ አቅጣጫ የመከተል ችግር፣ እንደኔ አስብ የሚል አባዜ፣ ድርጅትህን አፍርሰህ እኔ ጋር ተጠቃለል የሚል ሌላውን ያለማክበር ችግር፣ እኛ ያልባረክነው የተቃውሞ መንገድ ውግዝ ነው የሚል የትምክህት ስሜት፣ በተመሳሳይ አጀንዳ እየተመሩ መቧደን፣ ማነስ፣ ትንንሽ መሆን፣ ከትግልና ከትግሉ መስመር ይልቅ ወንበርና ስልጣን መናፈቅ፣ ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ በውይይት ከማስወገድ ይልቅ በሃሜትና በማሳጣት መስመር መረባረብ … የሚጠቀሱት በሽታዎች ናቸው። በተግባር እንደታየውና ሁሉም እንደሚመሰክሩት እነዚህ ችግሮች የተቃዋሚውን ጎራ ጨረቃ ላይ ጥለውታል። ባለበት እንዲረግጥ አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አብዛኞች ከየትኛው ወገን እንደሚሆኑ መወሰን አቅቷቸዋል። በኛ እምነት ይህኛው የኅብረተሰብ ክፍል ታላቅና ሃይል ያለው ስለሆነ በእውቀት ተሃድሶ ወደ ትግሉ የሚገባበት መንገድ መቀየስ አለበት። የተከፈለው ዋጋ ተከፍሎ!!
“እውቀት የሌለው፣ መረጃ የማያገኝ ህዝብ፣ የተደራጀና የተቀናጀ አደረጃጀቶች የሌለው ሕዝብ ለውጥ ሊያመጣ አይችልም፡፡ ከፖለቲካ ድርጅቶች የሚጠየቀውና የሚጠበቀው የተናደደ ኅብረተሰብን መፍጠር ሳይሆን መረጃ የሚያገኝ፣ እውቀት ያለው፣ የተደራጀና ድርጅቶቹ የተቀናጁ ኅብረተሰብ መፍጠር ነው” ሲሉ አሰተያየታቸውን ያሰፈሩት ዶ/ር ነጋሶ ደግ ብለዋልና ጆሮ ላላቸው ታላቅ መልዕክት ነው።
ስለሆነም የወደፊት የትግል አቅጣጫችንን የማሳወቅ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ፣ የማደራጀትና፣ ድርጅቶችን የማቀናጀት ሥራን ማዕከል ያደረገ መሆን እንዳለበት ልምዳቸውንና በግልጽ የተመለከቱትን አስታከው ያቀረቡት የመፍትሄ ሃሳብ በስፋት መድረክ ሊሰጠው የሚገባ ነው ብለን እናምናለን። በእውቀት ላይ የተመሰረተ ትግል እንደገለባ መንሽ በተመለከተ ቁጥር አይቦንም፤ እውቀቱም ቀላል ነው። በየወቅቱ የሰለቸንን የመቡነን አደጋና ከድርጅት ወደ ድርጅት የመገላበጥ እንዲሁም ስም እየቀየሩ ብቻ ለቁጥር የሚያዳግት ድርጅት መመስረት የሚቆመው ይኸው የእውቀት ተሃድሶ ተግባራዊ ሲሆን ነው። እውቀቱ በኮሌጅ ወይም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚሰጥ አይደለም። በእውነተኛነትና በቅንነት ላይ የተመሠረት እውቀት ነው፡፡ ከራስ በራስ የሚቸር ቀናነትን መሰረት ያደረገ ለራስ የመታመን ጥያቄ ነው። ሰው ምን ይለኛልን አውሎቆ የጣለ እውቀት ነው፡፡ በጥቅምና በወዳጅነት የሚደለል ሳይሆን በሐቀኝነት ዓለት ላይ በመተማመን ጸንቶ የቆመ እውቀት ማለት ነው፡፡ ለራሱ የሚታመን የትግል መስመርና ታጋይ ራዕይ አለው። ለለውጥ ንቅናቄ መሪውን አይጠብቅም፡፡ ያነገበው ራዕይ እያንደረደረ የድሉ በር ላይ ያደርሰዋል። ከሁሉም በላይ የነቃና በመረጃ የታጠቀ ህዝብ ድርሻውን ያውቃል። መብቱን ለማስከበር የትኛውንም ወገን የማስገደድ አቅም ያዳብራል። እንዲህ ያለ ህዝብ በተፈጠረ ቁጥር የአምባገነኖች ጡንቻ እየሰለለ ይሄዳል። ልባቸውም ይርዳል። እንዲህ ያለው የእውቀት ተሐድሶ ከድርጅት ወይም ከፓርቲ አይመጣም፡፡ በስብሰባ ብዛትና በጥናትና ምርምር ምጥቀት አይከሰትም፡፡ ግንኙነት ማድረግ በሚቻልበት አጋጣሚ ሁሉ ወሬ በመውቀጥ በተዓምር ብቅ አይልም፡፡ እንዲያውም ይህንን ዓይነቱ አካሄድ በሙሉ የራስ ማንነትን በማጥፋት በአጀብ፣ በቡድን ተግበስብሶ ለመመራት ያጋልጣል፡፡ ስለዚህ ተሃድሶው ከራስና በራስ መጀመር አለበት፡፡ እያንዳንዱ ሰው የሚፈልገውን በደመነፍስ ሳይሆን በእርግጠኝነት ማወቅ አለበት፡፡ ስለዚህ ከመምራትም ሆነ ከመመራት፤ ከመደራጀትም ሆነ ከማደራጀት በፊት እውቀት ይቀድማል! ለዚህ ደግሞ ተሃድሶ ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም አሁንም ደግመን የምንለው ቅድሚያ ከራስ የሚጀመር ተሃድሶ ባስቸኳይ!!

SOURCE: http://www.goolgule.com

ህወሃት አረጋግቶ አገገመ


ብቸኛው ተቃዋሚ የንግድ ሚኒስትሩን ሹመት ኮነኑ
Assigned EPRDFist
ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ አገሪቱን በመሩበት ሶስት ወራት ካቢኒያቸውን በደንብ መገምገማቸውን በግምት በመግለጽ ተቃውሞ ያቀረቡት አቶ ግርማ ሰይፉ በምደባው በተወሰነ ደረጃ እንደሚስማሙ ተናግረዋል። የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔን ምደባ የተቃወሙት በማስረጃ ነው። የዓለም ባንክ ለንግድ ምዝገባ የማያመቹ አገሮችን ዝርዝር ጥናት ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያ ከ185 አገሮች የ165ኛ ደረጃ ማግኘቷን፣ ለዚህም የዳረጉት ቀደም ሲል በተጠባባቂ ሚኒስትርነት ለረዥም ጊዜ ያገለገሉት አቶ ከበደ ጫኔ በመሆናቸው አዲሱ ሹመት እንደማይገባቸው አቶ ግርማ በተቃውሞ ተናግረዋል። በተጨማሪም ህዝብ የማወቅ መብት ስላለው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከሃላፊነታቸው ሲነሱ ምክንያቱ ይፋ ሊሆን እንደሚገባው ማሳሰቢያ አቅርበዋል።
አቶ ግርማ ብቻ የተቃውሞ አስተያየት ያቀረቡበት ምደባ በስፋት ሃሳብ ሲሰጥበት ለነበረው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ወንበር መልስ በመስጠት ተጠናቋል። ምደባውን ህወሃት ሲያሸንፍ የተመደቡት ሚኒስትር አቶ መለስ በህይወት እያሉ ይተኳቸዋል የተባሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ናቸው። የግራ ዘመሙን የፖለቲካ ጎዳና እምብዛም የማያውቁት ዶ/ር ቴዎድሮስ “ልምድ ያላቸው ታጋይ አይደሉም” በሚል ህወሃትን በከፍተኛ አመራርነት ስለመወከላቸው ጥያቄ የሚያቀርቡባቸው ነበሩ።
ለሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲን እጅግ ቅርብ  የሆኑት አዲሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ድር /ኔትዎርክ/ አካል ናቸው። በምደባው በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪ ሆነው የተመደቡት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልም በተመሳሳይ የአቶ መለስ ቅርብ ሰው ናቸው። ጎልጉል ዶ/ር ደብረጽዮን ወደ ከፍተኛው ስልጣን ርካብ እንደሚሻገሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚሆኑ ዘግቦ ነበር።
ክፍት በነበሩና በአዲሶቹ ሶስት አደረጃጀቶች መሰረት የተካሄደውን የባለሥልጣናት ምደባ አስመልክቶ አቶ ሃይለማርያም “ጠ/ሚኒስትሩ በቀጥታ ከሚከታተላቸውና ከሚመራቸው የመከላከያ፣ የደህንነት፣ የዲፕሎማሲ፣ የማክሮና ሜጋ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ ያሉትን የማህበራዊ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የኢኮኖሚና የፋይናንስ ዘርፎችን የመከታተል ስራ እንዲሰሩ ክላስተሮች ተቋቁመዋል” ብለዋል። አይይዘውም  አደረጃጀቱ ስራዎችን በየደረጃው ለመምራት የሚያስችል እንደሆነ አመልክተዋል።
የኢህአዴግ ፓርላማ በዛሬው ዕለት የቀረቡለትን ምደባዎች ሲያጸድቅ ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ያቀረቡት የከፍተኛ ባለሥልጣናት ምደባ ከአቶ ደመቀ መኮንን በተጨማሪ ሁለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችን አካትቷል። ምደባው ከትግራይ ሁለት፣ አንድ ከኦሮሚያ፣ አንድ ከጉራጌ ብሄረሰብ የተካተቱበት መሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለተመዳቢዎቹ ሲያስታውቁ ገልጸዋል።
ምደባው በደፈናው ሁሉም የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች የተካተቱበት ቢመስልም ጎልጉልን ጨምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች አስቀድሞ እንደተነገረው ከአቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ ተግባራዊ ተደርጓል ለተባለው የቡድን አመራርማረጋገጫ ተደርጎ ተወስዷል። በጸደቀው ምደባ መሰረት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አቶ ሙክታር ከድር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር፣ አቶ ከበደ ጫኔ የንግድ ሚኒስትር እንዲሆኑ  ተደርጓል።
በዚሁ ምደባ መሰረት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪ ሆነው ቢመደቡም ከደህንነት ጋር የተቆራኘውን የመገናኛና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትርነታቸውን አልተነጠቁም። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሃላፊነታቸውን ስለመቀጠላቸው በይፋ ያልተገለጸው አቶ ሙክታር ከድር በምክትል ጠ/ሚኒስትርነት ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ ዘርፍ አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ሆነዋል። አቶ ሙክታር ከኦሮሚያ ምክትል ፕሬዚዳንትነታቸው ተነስተው ለሁለት ዓመት ኢህአዴግ ጽህፈት ቤት ያለ ስራ እንዲቀመጡ ተደርጎ የነበረው በመልካም አስተዳደር ችግርና አቅም ማነስ እንደነበር በማስታወስ አስተያየት የሰጡ “ምደባው ኦህዴድ የምክትል ጠ/ሚኒስትርነት ቦታ አገኘ በሚል የፖለቲካ ጨዋታ ለመጫወትና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነቱን ቦታ በመጠየቁ ለማስተዛዘኛ ነው” ብለዋል። በሌላ በኩልም አቶ ሙክታር ለባለሃብቱ አላሙዲ ቅርበት ያላቸውና በዚሁ ቅርበታቸው ሳቢያ ኦሮሚያ ክልል ባለሃብቱ ግብር እንዲከፍሉና የወሰዱትን ቦታ እንዲያለሙ ለማስገደድ ሲንቀሳቀስ አቶ ሙክታር በመቃወማቸው በኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ በጉድለት መገምገማቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ይናገራሉ።
ደመቀ መኮንን እና ሃይለማርያም ደሳለኝ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ ሶስት  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች የሚደገፉት አቶ ሃይለማርያም፣ አቶ መለስን ተክተው መስራት በጀመሩ ማግስት “የምንሰራውና የምንመራው በቡድን ነው” ባሉት መሰረት በሶስት ም/ጠቅላይ ሚኒስትሮች መታጀባቸው ይፋ ሆኗል። ጎልጉል ብዙም ትኩረት ያልተሰጣቸውን ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ጠ/ሚኒስትር ለማድረግ ታስቦ በአሜሪካን  ተጽዕኖና በቅድመ ማግባባቱ ላይ የኦህዴድን ድጋፍ ሊያገኙ ባለመቻላቸው አቶ ሃይለማርያም በነበሩበት እንዲቀጥሉ መደረጉ መዘገቡ ይታወሳል
በአዲሱ ምደባ የዶ/ር ቴዎድሮስን ቦታ በመረከብ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የሆኑት ምክትላቸው ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ ናቸው። የአምስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ምደባ ይፋ በሆነበትና በዛሬው ዕለት አቶ ሃይለማርያም እንደ ወትሮው ሁሉ ንግግራቸውን የጀመሩት የአቶ መለስን ስም በማስቀደም ነበር። በዚሁ ንግግራቸው “ቀደም ሲል የተያዘው የአመራር መተካካት ከታቀደው በፊት ተግባራዊ ይደረጋል” ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ግርማ ሰይፉ ላቀረቡት ተቃውሞ መልስ የሰጡት አቶ ሃይለማርያም ቀደም ሲል አቶ ግርማ ብሩ ይመሩት የነበረውን የንግድ ሚኒስቴር “የንግድ ምልክትና የንግድ ስያሜ እንኳን መለየት የማይችል እጅግ ኋላ ቀር” ሲሉ ነው ያንኳሰሱት። የዓለም ባንክ ሪፖርት ይፋ ባይደረግም አቶ ከበደ ጫኔ ችግር እንዳለ በማወቅ አዲስ አዋጅ በማዘጋጀትና ዘመናዊ አሰራር በመዘርጋት ተቋሙን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመለወጥ እየሰሩ ያሉ ሚኒስትር መሆናቸውን በመግለጽ አቶ ሃይለማርያም ተከራክረውላቸዋል። አዳዲሶቹ የፌደራል ስራ አስፈጻሚዎች ቃለመሃላ ፈጽመዋል። ኦህዴድ ያገኘዋል የተባለውን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት መቀመጫ ማጣቱን ተከትሎ አስተያየት ለማሰባሰብ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። ምደባው እንደተለመደው በአንድ ድምጸ ታቅቦ ነው የጸደቀው። በዕለቱ ምክንያቱ ባይታወቅም አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ አልተገኙም።
SOURCE: http://www.goolgule.com

ከፍተኛ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉት ግለሰብ የኦሮምያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ


ህዳር ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ጉባኤውን ሲያጠናቅቅ የ77 ዳኞችን ሹመት አጽድቋል።የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው የተሾሙት አቶ ፍቅሩ አያና ከምክር ቤት አባላቱ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ቢቀርብባቸውም፣ ከፍተኛ አመራሮች ስለፈለጉዋቸው ብቻ እንዲሾሙ መደረጉን የኦህዴድ ምንጮች ገልጸዋል።
የምክር ቤት አባላት በአቶ ፍቅሩ ላይ ካቀረቡዋቸው የመቃወሚያ ሀሳቦች መካከል ግለሰቡ በሙስና የተዘፈቁ ናቸው፣ በዞናቸው ዳኛ ሆነው በሰሩበት ወቅት በህዝብ የተጠሉና ህዝብን ያንገላቱ ናቸው፣ የስነምግባር ችግር አለባቸው፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም የሚሉት ይገኙበታል። የክልሉ ባለስልጣናት ከምክር ቤት አባላት ለቀረበባቸው ተቃውሞ አጣርተን መልስ እንሰጣለን የሚል ድፍንፍን ያለመልስ በመስጠት ሹመቱ እንዲጸድቅ አድርገዋል።
የምክር ቤት አባላቱ በባለስልጣኑ አሰራር ላይ ነቀፌታ ሲያቀርቡ እንደነበር ታውቋል።
በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ ክልሉን ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳን ጨምሮ የስራ አስፈጻሚዎች የስልጣን ሹም ሽር ይኖራል የሚል አጀንዳ ተይዞ የነበረ ቢሆንም ምክንያቱ በውል ባልታወቀ ሁኔታ አጀንዳው እንዲሰረዝ ተድርጓል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት አቶ አለማየሁን ለመተካት ሀሳብ ቢቀርብም በሚተካው ሰው ላይ የስራ አስፈጻሚዎች ለመስማማት ባለመቻላቸው እንዲቀር ተድርጓል። አንዳንድ የስራ አስፈጻሚ  አባላት ስብሰባ ረግጠው እስከመውጣት መድረሳቸውን ለማወቅተ ችሎአል።
በሰሞኑ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ አርብ እለት ከተገኙት ከምክትል ፕሬዚዳንቱ ከአቶ አብዱላዚዝ በስተቀር ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት በማጠቃለያው ጉባኤ ላይ አልተገኙም።
ሰሞኑን ለአቶ ሙክታር ከድር የተሰጠው የምክትል ጠቅላይ ሚኒሰትርነት ቦታ በተወሰነ መጠን በምክር ቤቱ ውስጥ ይነሳል ተብሎ የተጠበቀውን ተቃውሞ ማብረዱ ታውቋል።
በሌላ ዜና ደግሞ አዳማ 5ኛውን ከንቲባ ሾማለች። ከሙስና ጋር በተያያዘ ከህዝብ በቀረበ ተቃውሞ ከስልጣን እንዲባረሩ በተደረጉት የተወካዮች ምክር ቤት አባሉ በአቶ ጉታ ላንጮሬ በአቶ ባካር ሻሌ ተተክተዋል። አቶ ባካር ሻሌ አቶ በረከት የሚመሩት የኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ምክት ሃላፊ የነበሩ ናቸው።
አንዳንድ ወገኖች ግለሰቡ በእርግጥም ከሙስናና ከአስተዳደር ብቃት ጋር በተያያዘ በከተማው ህዝብ ዘንድ ተቃውሞ ተነስቶባቸው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ከስልጣናን የተባረሩት ግን ምናልባትም በኦህዴድ ውስጥ ከተፈጠረውን ችግር ጋር ተያይዞ ሊሆን እንደሚችል ይናገራሉ።
ኢሳት የከንቲባውንና የከተማ ልማት ቢሮ ሀላፊውን ከስልጣን መባረር መዘገቡ ይታወሳል።

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ክስ እንደገና ተቀሰቀሰ


ህዳር ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከዚህ ቀደም በፌዴራል ዐቃቤ- ሕግ ቀርቦበት የነበረው ክስ እንደገነ ተቀሰቀሰ፤
ትላንት ሃሙስ ህዳር 20 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀትር በኋላ ወደ ጋዜጣው ቢሮ የፍርድ ቤት መጥሪያ ይዘው የመጡት የፖሊስ አባላት ጋዜጠኛ ተመስገን ከአዲስ አበባ ውጪ መሆኑ ተነግሯቸው ተመልሰዋል ።
ዓርብ ህዳር 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከሰሃት በኋላ የፌዴራል ፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 16ተኛ ወንጀል ችሎት ጋዜጠኛ ተመስገን በሌለበት ችሎት የሰየመ ሲሆን የፍርድ ቤት መጥሪያ ለጋዜጠኛው ሊያደርሱ የሄዱት ፖሊሶች በጊዜው ሊያገኙት አለመቻላቸውንና ለሥራ ባልደረቦቹ ግን መንገራቸውን ገልጸዋል፡፡
ቀደም ሲል የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን የዋስትና መብት የነፈጉት ዳኛ መጥሪያው እንዳልደረሰው ካረጋገጡ በኋላ ዐቃቤ- ሕግን የውሳኔ አስተያየት የጠየቁ ሲሆን ዐቃቤ- ሕግ በበኩሉ በቀጣይ እንዲቀርቡልኝ ማዘዣ ይጣፍልኝና አጭር ቀጠሮ ይሰጠኝ ብሏል፡፡
የችሎቱ ዳኛ በበኩላቸው የፍርድ ቤት መጥሪያ ለፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ እና ለድርጅቱ ጠበቃ እንዲደርስ ማዘዣ እንዲወጣ አዘው ቀጣይ ቀጠሮውንም ለታህሳስ 2 ቀን 2005 ዓ.ም ጊዜ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ  ከጤናው ጋር በተያያዘ ወደ አዋሳ መጓዙን ተከትሎ መጥሪያ እንደደረሰው ለኢሳት ገልጿል።
የፕሬስ አፈናው በአቶ ሀይለማርያም የስልጣን ዘመንም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በአዲስ ታይምስ መጽሄት ላይ ሲሰራ የገጠመውን ችግር በመዘርዝር ገልጿል
ተመስገን ፍትህ ጋዜጣን ሲያሳትም በነበረበት ወቅት ከ39 ባላነሱ እንያንዳንዳቸው ከ106 በላይ ዝርዝር ክሶችን በያዙ ወንጀሎች መከሰሱ ይታወቃል።
ከታዋቂው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጋር በፕሬስና በወቅታዊ የአገራች ፖለቲካ ዙሪያ ያደረግነውን ቃለምልልስ ከዜናው በሁዋላ በትኩረት ክፍለ ጊዜ የምናቀርብ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

ከአንድ ሺ በላይ የሚሆኑ የሚኒስትር መ/ቤቶች የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች በደሞዝ ልዩነት ቅሬታ አሰሙ


ህዳር ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- “ሁላችንም የህዝብ ግንኙነት ሠራተኞች ብንሆንም ጥቂት ሠራተኞች በመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ፅ/ቤት ስልጠና ስለተሰጣቸው ብቻ ከፍተኛ የደሞዝ ጭማሪ ይደረግላቸዋል” በማለት ጋዜጣው ዘግቧል።
በኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ለ13 ቀናት የሚሰጠውን ስልጠና የተከታተለ ባለሙያ ደሞዙ ከ2250 ብር ወደ
4150 ብር ከፍ እንደሚል የተናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በአንድ ሙያ ላይ ለተሰማሩ ሠራተኞች የዚህን ያህል የደሞዝ ልዩነት መፈጠሩ ከፍተኛ የሞራል ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል፡፡ እኒሁ አቤቱታ አቅራቢዎች ፊርማ አሰባስበው ለመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ማስገባታቸውንም ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው የሚሰጠው ለተወሰኑ ሠራተኞች ብቻ መሆኑን የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎች፤ ይሄም ለተፈጠረው ልዩነት ሌላው ችግር እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ሁሉም ፖሊሲውን ለማስፈፀም ብቁ ናቸው ተብለው መቀጠራቸውን በመግለፅም በአንድ መ/ቤት በተመሳሳይ የስራ ዘርፍ ላይ እየሠሩ የዚህን ያህል የደሞዝ ልዩነትን መኖሩ ፍትሃዊ እንዳልሆነ ይናገራሉ እንደጋዜጣው ዘገባ
ከዚህ ቀደም በሚሠሩበት መ/ቤት ችግሩን ለሃላፊዎቻቸው ቢያቀርቡም በሚቀጥለው ወር ጠብቁ እየተባሉ አንድ አመት እንዳለፋቸው የሚናገሩት ሠራተኞቹ፤ በመጨረሻም ችግራቸውን ለመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ለማቅረብ መገደዳቸውን ገልፀዋል፡፡
ስልጠናውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ሚኒስትር አቶ በረከት ስምኦን እና የፅ/ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል በየሁለት ወሩ ለ13 ቀናት እንደሚሰጡ በዘገባው ተጠቅሷል።
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል በበኩላቸው፤ የንግግር እና የመፃፍ ችሎታቸውን የበለጠ ለማዳበር እና የመ/ቤታቸውን አላማዎች ማብራራት እንዲችሉ የፖሊሲ ስልጠና እንደሚሰጥ ለጋዜጣው ገልጸዋል።
የህዝብ ግንኙነት ስራ በራሱ የፖለቲካ ተሿሚም ስለሆነ የተለያዩ ወቅታዊ ስልጠናዎች ለባለሙያዎቹ እንደሚሰጣቸው የተናገሩት አቶ ሽመልስ፤ ሠራተኞቹ ያሉባቸውን ችግሮች ለሀላፊዎቻቸው አቅርበው መፍትሔ ካላገኙ ወደ እኛ መምጣት ይችላሉ ብለዋል፡፡

የእስራኤል ኩባንያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ማኔጅመንት ሊረከብ ነው



-    ሌሎች 50 ኩባንያዎች በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት ለማድረግ ጠይቀዋል
-    እስራኤል በአፍሪካ ኅብረት መድረክ አለማግኘቷ ቅሬታ ፈጥሮባታል

በታደሰ ገብረማርያም
የእስራኤል ኤሌክትሪክ ኩባንያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ማኔጅመንት ተረክቦ ለሦስት ዓመታት ያህል ለመምራት የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቅቋል፡፡ ሌሎች ወደ 50 የሚጠጉ የእስራኤል ልዩ ልዩ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ወይም ኢንቨስት ለማድረግ መጠየቃቸውን በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር በላይነሽ ዘቫዲያ ገለጹ፡፡

የእስራኤል ኤሌክትሪክ ኩባንያ 20 መሐንዲሶች በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ መጥተው ሥራውን ይጀምራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አምባሳደሯ አስረድተዋል፡፡ የእስራኤል የኤሌክትሪክ ኩባንያ የኮርፖሬሽኑን ማኔጅመንት ለሦስት ዓመታት ለመምራት የሚያስችለውን ሥራ ያገኘው ለዚህ ተብሎ የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ በማሸነፉ መሆኑ ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን በሁለት እንዲከፈል የተወሰነ ሲሆን፣ የኃይል ሽያጭ፣ የደንበኞች አገልግሎትና አስትዳደራዊ ጉዳዮች ለእስራኤሉ ኩባንያ ይሰጣሉ፡፡ ሁለተኛው ኃይል የማመንጨትና የማስፋፋት ሥራዎች በኮርፖሬሽኑ አማካይነት ይከናወናል፡፡ ከዚህ ቀደም መንግሥት የቀድሞውን ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ማኔጅመንት ለፈረንሳዩ ፍራንስ ቴሌኮም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ሌሎቹ 50 ኩባንያዎች ለመሰማራት የሚፈልጉት በሶላር ኢነርጂ፣ በውኃ ቴክኖሎጂ፣ በመስኖ ልማት፣ በጤናና በሌሎችም በርካታ የልማት ዘርፎች መሆኑን አምባሳደሯ አስረድተው ከኩባንያዎቹ መካከል የተሟላ አቅም፣ ብቃትና የአሠራር ጥራት ያላቸውን ለይቶ ለማወቅ የሚያስችል የማጣራት ሥራ ኤምባሲው በማከናወን ላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ 

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ኅብረትና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መቀመጫ፣ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት፣ ለማንኛውም ዓይነት እርሻ ተስማሚ የሆነ ለምና ድንግል መሬትና በርካታ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት መሆኗ፣ የውጭ ባለሀብቶችን ወይም ኩባንያዎችን ቀልብ ለመሳብ መቻሉን አምባሳደር በላይነሽ አስረድተዋል፡፡

“ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ እያደገች፣ የቀድሞ አስከፊ ገጽታዋን እየለወጠችና ተስፋ ሰጪ የሆነ የዕድገት አቅጣጫን ይዛ ትታያለች፡፡ አሁን የተያያዘችውን የዕድገት ጎዳና አጠናክራ ከቀጠለች በቅርብ ጊዜ ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ትሰለፋለች፡፡ ይህ ዓይነቱ አካሄድም ታላቅ አገር ያደርጋታል፤” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

እስራኤል ከባዶ ተነስታ ያንን ደረቅና በረሃማ መሬት አልምታ፣ የተማሩ ሰዎችንና የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን አፍርታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ካደጉ አገሮች ተርታ ለመሰለፍ በቅታለች ብለው፣ ኢትዮጵያ ደግሞ የትም የማይገኝ ሰፊና በርካታ የተፈጥሮ ሀብት እያላት በድህነት አረንቋ ውስጥ መዘፈቅ የለባትም የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

‹‹የኢትዮጵያና የእስራኤል ግንኙነት ከንግሥተ ሳባ ወይም ከሦስት ሺሕ ዘመን በፊት ጀምሮ ተያይዞ የመጣ መሆኑን ለማንም የተሰወረ አይደለም፤›› ያሉት አምባሳደር በላይነሽ፣ በአሁኑ ጊዜ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው ግንኙነት በጥሩ ደረጃ ላይ መሆኑንና ይህ ዓይነቱም ግንኙነት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉን አቀፍ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ለዚህም እውን መሆን በቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግርና በባህል ልውውጥ ዙሪያ በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

አምባሳደር በላይነሽ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጎንደር፣ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በአዲስ አበባ ኮከብ ፅባህ ትምህርት ቤት አጠናቅቀዋል፡፡ ከዚያም ኑሮአቸውን እስራኤል በማድረግ በመጀመሪያ የእብራይስጥ ቋንቋ መማራቸውንና ከዚያም በሒብሩ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ግንኙነት የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪዎችን ካገኙ በኋላ፣ በ1985 ዓ.ም. የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባልደረባ ሆነዋል፡፡ ባለትዳርና የሦስት ልጆች እናት ሲሆኑ ባለቤታቸው ጎንደር ተወልደው የተማሩት ደግሞ አዲስ አበባ ነው፡፡

‹‹ወደ እስራኤል የሄድኩት በ17 ዓመቴ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ከወጣሁም 28 ዓመት ሆኖኛል፡፡ በሌላ አገር ከሚኖሩት ትውልደ ኢትየጵያውያን መካከል እኔ አምባሳደር ሆኜ መመለሴ የመጀመሪያው ያደርገኛል፡፡ ሌሎችም ዳያስፖራዎች ይህ ዓይነቱ ዕድል እንዲገጥማቸው ምኞቴ ነው፤›› ብለዋል፡፡ አምባሳደር በላይነሽ ዘቫዲያ በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የብሩንዲና የሩዋንዳ የእስራኤል አምባሳደር ናቸው፡፡ ሹመታቸውን አግኝተው ኢትዮጵያ ከመጡም ጥቂት ወራት ተቆጥረዋል፡፡

በሌላ በኩል እስራኤል ከ42 የአፍሪካ አገሮች ጋር የዲፕሎማቲክ ግንኙነት እያላትና በአኅጉሩ ውስጥ በበርካታ የልማትና የዕድገት ሥራ ላይ ተሰማርታ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ላይ መሆኗ እየታወቀ፣ በአፍሪካ ኅብረት የታዛቢነት መድረክ አለማግኘቷ በእጅጉ እንዳሳዘናቸው አምባሳደሯ ተናግረዋል፡፡

አምባሳደር በላይነሽ እንደገለጹት፣ ኅብረቱ እስራኤልን በሚመለከት ወይም በእስራኤልና በፍልስጤም መካከል ባሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት በሚያደርግበት ወቅት የፍልስጤም ተወካይ ሲገኝ፣ ለእስራኤል ግን ይህ ዓይነቱ ዕድል መነፈጉ አግባብ አለመሆኑን አስረድተዋል፡፡

‹‹እኛ በሌለንበት ወይም እንድንሳተፍ ባልተጋበዝንበት ጉባዔ ላይ ስለእኛ ተነጋግሮ ውሳኔ ማሳለፍ ትክክለኛ አካሄድ አይደለም፤›› ያሉት አምባሳደር በላይነሽ፣ እስራኤል በአውሮፓ ኅብረትና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በመሳሰሉት ዓለም አቀፍ ተቋማት ዘንድ ድምጿን ከፍ አድርጋ የምታሰማበት መድረክ እንዳላት ሊታወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ላይ ግን የፍልስጤሙ ተወካይ ሲገኝ እስራኤል መነፈጓ ኅብረቱ ለአንድ ወገን ያደላ አስመስሎታል ብለዋል፡፡

የእስራኤል መገኘት አስፈላጊ በሆነበት በኅብረቱ ጉባዔ ላይ እንዳትሳተፍ ሊያደርጋችሁ የቻለበት ምክንያት ምን ይመስልዎታል? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ “ምክንያቱን ባውቀው በጣም ደስ ይለኛል፤ እኔ እንደሚመስለኝ ከሆነ ግን ከእኛ ጋር ግንኙነት የሌላቸው የኅብረቱ አባል አገሮች የፈጠሩት ጫና ሳይሆን አይቀርም፤” ሲሉ አምባሳደር በላይነሽ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  



በአገር የምትመሰለዋን ትልቅ ክብር ያላትን ውድዋን ሴትን በዚህ መልኩ ያሰቃያሉ እህቶቻችን በፌደራል ታፍነው ሲወሰዱ


እህቶቻችን በፌደራል ታፍነው ሲወሰዱ

እንደው እስከ መች ነው እንደዚ እያየን ዝም የምንለው በዚህ በኩል አገራችን ለማች አደገች ይላሉ በሌላ በኩል ደግሞ ይኸው እንደምናየው በአገር የምትመሰለዋን ትልቅ ክብር ያላትን ውዶዋን ሴትን በዚህ መልኩ ያሰቃያሉ ። እንደው ከምን ይሆን የተፈጠሩት ከሴት ወይስ ? ምነው እነሱን እንኩዋን ቢተዋቸው ለራሳቸው በአረብ አገር  ላይ የሚደርሰው ሰብዓዊ መብት ረገጣ የነጻነት እጦት ሌላው ይቅርና የአለም ደቻሳ እንባን በደንብ  ሳያብሱ ዛሬ ደግሞ አፍነው ይወስዱዋቸዋል ። ለነገሩ ለካስ እነዚህ ሰዎች የተፈጠሩት ከሴት አይደለም