ጠበቆቹ ስለምስክሮቹ መግለጫ ካቀረቡ በኋላ አቃቤ ህጎቹ በ1ኛ እና 2ኛ ምስክር ላይ ተቃሞ እንዳላቸው ተቃሟቸውን አቀረቡ:: 1ኛ ምስክር ዶ/ር ያሬድ የህግ ባለሙያ ቢሆኑም ህገመንግስቱን የመተርጎም ስልጣን የላቸውም : ህገመንግስቱን የመተርጎም ስልጣን ያለው የፌዴሬሽን ም/ቤት ብቻ ነው ስለዚ የሳቸው ምስክርነት አያስፈልግም:: 2ኛ ምስክር ፕ/ር መስፍን ኢሰመጉ ሊቀመንበር ሆነው የሰሩ ቢሆንም ከ97 በኋላ ባላቸው የፖለቲካ እንቅስቃሴ እና አቋም ገለልተኛ ሆነው መመስከራቸው ያጠራጥረናል ስለዚህ የሁለቱን ምስክር ሆኖ መቅረብ ፍ/ቤቱ ውድቅ እንዲያደርግ ጠይቀዋል::
የተከሳሽ ጠበቆችም ምላሽ ሲሰጡ : 1ኛ ምስክር ዶ/ር ያሬድ ህገመንግስቱን እንዲተረጉሙ ሳይሆን ደንበኛቸው የተከከሰሰባቸው ፅሁፎች ከህገመንግስቱ እና ኢትዬጵያ ከፈረመቻቸው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ከሚደነግጉ አለም አቀፍ ህጎች አንፃር እንዴት ትክክል እንደሆኑ ለማስረዳት መሆኑን 2ኛ ምስክር ፕ/ር መስፍን ደግሞ የሚያቀርቡት ኢሰመጉ ሲሰሩ በነበሩባቸው ጊዜያቶች ያዩትን የሰሙትንና ድርጅቱም በሪፖርቱ ያካተታቸውን ጉዳዮች እንጂ ሌላ ነገር አለመሆኑም..የገለልተኝነታቸው ጉዳይ በተመለከተ ደግሞ በህጉ ምስክሮች ገለልተኛ መሆን አለባቸው የሚል እንዳልተጠቀሰ ..አቀረቡ:: ዳኛውም ግራ ቀኙን ካዳመጡ በኋላ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላለፉ:: በአቃቤ ህግ ተቃሞ የቀረበባቸው ምስክሮች 1ኛ ምስክር ዶ/ር ያሬድ ህገመንግስቱን መተርጎም እንደማይችል ነገር ግን ከዛ ውጪ ባለው እውቀት ክስ የቀረበባቸውን ፅሁፎች ከህገመነግስቱ እና ሌሎች ህጎች አንፃር እንደማያስከስሱ ብቻ ማቅረብ እንዳለባቸው 2ኛ ፕ/ር መስፍንም ኢሰመጉ ሲሰሩ በነበሩበት ወቅት የሚያቁትን ብቻ እንዲያቀርቡ፡፡ ገለልተኛ ለተባለው…መስካሪዎች ገለልተኛ እንዲሆኑ የሚል ደንብ ስለሌለ ማንኛውም ሰው ያለምንም ልዩነት የምስክርነት ቃል መስጠት ይችላል::
በፍትሕ ጋዜጣ ላይ፣ የተዘገቡ ”የካቲት 23 2004 ዓ.ም በተሰራጨው የፍትህ ጋዜጣ ቅጽ 05 ቁጥር 177 እትም የፈራ ይመለስ በሚል” : ”በቅጽ 5 ቁጥር 179 መጋቢት 7 2004 ዓ.ም ዕትም መጅሊሱና ሲኖዶሱ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ማጥመቂያ” እና “ ሐምሌ 22 ቀን 2003 ዓ.ም የሁለተኛ ዜግነት ህይወት በኢትዮጵያ እስከመቼ?” በሚሉ ርእሶች በወጡ መጣጥፎችን ተከትሎ ”የሕዝብን ሐሳብ ማናወጥ፣ሕዝቡን በሕገ-መንግስቱ ላይ ማነሳሳትና የመንግስትን ስም በማጥፋት” በሚሉ ሶስት ክሶች ነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የተከሰሰው::
No comments:
Post a Comment