FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Sunday, September 7, 2014

የአፋርን ሕዝብ ወኃ ጠማው

አኩ አብን አፋር ለዘ-ሐበሽ አንደዘገበው፦
በአፋር ክልል በ32 ወረዳዎች ህዝብ በውኃ ጥም በከፈተኛ ችግር ውስጥ ይገኛል። ባለፉት 5 አመታት ለኢህአዴግ ባለስልጣናት ኢንቨስትመንት ተብሎ ከህዝቡ የተቀማው የአፋር ህዝብ መሬት ለህዝብ በከፍተኛ ደረጃ የውኃ እጥረት አስከተሏል!! በአዋሽ ወንዝ ዳር ሲኖሩ የነበሩ አርብቶ አደሮች በግዴታ በመንደር በማሰባሰብ ከፍተኛ ኪሳራ በህዝቡ ላይ አድርሷል።
(ፎቶ ፋይል)
(ፎቶ ፋይል)

ለምሳሌ ፦ በግብርና አስተዳደር የነበረው ህዝብን በግዴታ በመንደር በመሰብሰብ ለከፍተኛ አደጋ እያጋለጡ ነው። ትምህርት ፣ ህክምና፣ ኤሌክትሪክ፣ ውኃ እና የመሳሰሉትን ነገሮች ሳይዘጋጀላቸው ህዝብን እያፈናቀሉ ነው። በአሁኑ ወቅት በጭፍራ ወረዳ «በወአማ» ቀበሌ የሚገኙ ህዝቦች በመጀመሪያ በመንግስት የተሰበሰቡ ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት ግን ከመንግስት ልያገኙ የሚገባቸውን ነገሮች እንደማያገኙ ይናገራሉ። ከጭፍራ ፣ከሚሌ፣ ከገዋኔና አካባቢው ወጣቶች ለስደት ወደ ጅቡቲ እንዲሁም ወደ አረብ ሃገራት እየተሰደዱ መሆናቸው ይደመጣል።
በጣም ነው የሚያሳዝነው በሎግያ አካባቢ አንድ ጄርካን ውኃ በ17 ብር እየገዙ የሚጠጡ አሉ! «የክልሉ መንግስት ምን እየሰራ ነው? እኛ መንግስት የለንም! መንግስት የራሱን የስልጣን እድሜ ለማራዘምና ለቤተሰቦቻቸውን ብቻ ለመርዳት የሚሰራ የሙስና ቡድን እንጂ መንግስት የለንም» ሲሉ ብዙዎች ይናገራሉ!! ህክምና ለማግኘት ወደ ደሴ መሄድ አለባቸው ወደ ደሴ በመሄድ መንገድ ላይ የሚሞቱም አሉ! ከ4 ወር በፊት አንዲት አዛውንት በእባብ ተነድፈው ወደ ደሴ ሆስፒታል እየወሰዷቸው መንገድ ላይ ህይወታቸው አልፏል! «እውነት ለመናገር የአፋር ክልል ችግር ከሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተለየ ነው» ሲሉ ነዋሪዎች ብሶታቸው ይናገራሉ። «ክልሉ እየተመራ ያለው ኃላፊነት በማይሰማቸው መሀይሞች በመሆኑ ነው ከአሁን በኋላ የምንጠበቀው እድገት የለም» ይላሉ ነዋሪዎቹ።
በአፋር ክልል 32 ትላልቅ ወረዳዎች ይገኛሉ፣ በመላው የአፋር ክልል ብቸኛው እና እድሜ ጠገብ የሆነው አንድ ሆስፒታል አለ፤ እሱም የተገነባው በደርግ ጊዜ ነው። በዱብቲ የሚገኘው ይህ ሆስፒታል ለህዝብ የሚሰጠው አገልግሎት በጣም አነስተኛ ነው! የወባ መድኃኒት እንኳን አይገኝበትም የዱብቲ ወረዳ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሆነ ለሆስፒታሉ የሚሰጠው ማቴሪያልና መድኃኒቶች ለግል ፋርማሲዎች ይሸጣሉ።
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/34404

No comments:

Post a Comment