FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Tuesday, December 3, 2013

መቀሌ በእሳት ቃጠሎ አደጋ ተናጠች

አብረሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው፦ ዛሬ ሌሊት (ማክሰኞ አጥብያ) ህዳር 23/24, 2006 ዓም በመቐለ ከተማ ሰሜን ወረዳ 06 ቀበሌ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደርሶ 70 የFurniture and Metal works Workshops ሙሉ በሙሉ ወድመዋል። በዎርክሾፖቹ የሚተዳደሩት ከ250-300 የሚሆኑ ሰራተኞች የነበሩ ሲሆን በጠቅላላ ከ22 ሚልዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድመዋል።
ማዘጋጃቤት መርዳት ባለመቻሉ ኗሪዎቹ ወደ አየርመንገድና ሲሚንቶ ፋብሪካ በመሄድ የእሳት አደጋ መከላከያ መኪኖች እንዲረዱ የጠየቁ ሲሆን የአየር መንገዱ በመጨረሻ አከባቢ ደርሷል፤ የሲሚንቶ ፋብሪካው ግን በቂ ዉኃ ሳይዝ በመምጣቱ ብዙ ንብረት ማዳን አልቻለም።የአደጋው መንስኤ ባከባቢው የሚገኘው የመንግስት የመብራት ትራንስፎርመር በመቃጠሉ ነው። ትራንስፎርመሩ ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ የመቃጠል ምልክቶች እንደነበሩትና ያከባቢው ኗሪዎችም በተደጋጋሚ ለመንግስት አካላት ትራንስፎርመሩ እንዲጠግኑት ጥያቄ ቢያቀርቡም መልስ ባለመግኘታቸው ችግሩ መፈጠሩ ተጠቅሷል። ስለዚህ አደጋው ያጋጠመው በመንግስት አካላት ቸልተኝነት መሆኑ ነው።የእሳት አደጋው በቀላሉ መቆጣጠር ይቻል የነበረ ቢሆንም ሁለቱም የመቐለ ከተማ ማዛጋጃቤት የእሳት አደጋ ማጥፍያ ተሽከርካሪዎች ‘ተበላሸተው ጋራጅ ገብተዋል’ በሚል ምክንያት አደጋው የመቆጣጠሩ ጥረት አዳጋች አድርጎታል።
የመቐለ ማዛጋጃቤት የእሳት አደጋ ማጥፍያ ተሽከርካሪዎች ተበላሽተዋል ሲባል ገረመኝ። BTW, የተቃጠሉ ድርጅቶች ፎቶ ለማስነሳት ያደረግነው ጥረት በፖሊስ ሃይል ተከልክለናል። የመቐለው 06 ቀበሌ ‘የኢንዱስትሪ ዞን’ ነው።
በመንግስት ቸልተኝነት ምክንያት ንብረት ሲወድም ያሳዝናል።

No comments:

Post a Comment