FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Thursday, January 23, 2014

በኢትዮያ እና ሱዳን ድንበር ዙሪያ ወቅታዊና ትምህርታዊ የውይይት መድረክ (ሰማያዊ ፓርቲ )

ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮ ሱዳን ጉዳይ ላለፉት ወራት ነገሩን በቅርበት ሲከታተል የቆየ ሲሆን በጉዳዩም ላይ አቋሙን በመግለጫ መልክ ማውጣቱ ይታወሳል አክሎም ፊታችን ጥር 25 ቀን ለቦታው ቅርበት ካላቸው ከተሞች አንዷ በሆነችው ጎንደር ከተማም ተቃውሞ ሰልፍ መጥራቱ ይታወቃል፡፡ ከነዚህ እንቅስቃሴዎች በተጨማሪም ድንበራችንን ጉዳይ በተመለከተ በተጨባጭ መረጃ በህብረተሰቡ ውስጥ ግንዛቤ ይፈጠር ዘንድ ትምህርታዊ ውይይት መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን በዝግጅቱ ላይም በዘርፉ ለረጅም አመታት በመስራት የሚታወቁት የረጅም ጊዜ የጆግራፊ ባለሞያ የሆኑት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ድንበሩን በተመለከተ ሰፋ ያለ ትምህርት ይሰጣሉ፡፡ እርስዎም በዝግጅቱ ላይ እንዲሳተፉ በአክብሮት ተጋብዘዋል!

ቀን፡- ቅዳሜ ጥር 17 ቀን
ሰዓት፡- ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ
ቦታ፡- በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት
(የጽ/ቤታችን መገኛ ከካሳንችዝ ቶታል ወደ አዋሬ በሚወስደው መንገድ ላይ “የአዋሬ አጥቢያ ወንጌላውያን ቤተክርስቲያን” ጋር ሲደርሱ ወደ ቀኝ በሚያስገባው መታጠፊያ 50 ሜትር ላይ ነው)
Blue Party Ethiopia

http://ecadforum.com/Amharic/archives/10798/

1 comment:

  1. I didn't forget his interview with Deutsche Willo Amharic Service in late 2008. I believe that Professor Mesfin is the right person for briefing the people.

    ReplyDelete