FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Friday, June 7, 2013

ወ/ሮ ንፁህብር ጥላሁን ገሠሠ ታማኝ ለአባቷ ስላደረገው ውለታ ስትናገር – Video

“ታማኝ ለጥላሁንዬ የዲፕሬሽን መድሃኒቱ ነበር”

ከስንታየሁ በላይ
በቨርጂኒያ አካባቢ ቴሌቭዥን በጥላሁን ገሠሠ ስም የከፈተውና ጥላሁን ገሠሠ “ካገባቸው” በጣት ከሚቆጠሩት ሚስቶች መካከል የአንዷ የወ/ሮ ሮማን በዙ ወንድም ነኝ የሚለው መስፍን በዙ ከወያኔ ፍርፋሪ አገኛለሁ በሚል ከንቱ ህልም የጀግናውን ታማኝ በየነ ስም ሲያጠፋ ቆይቷል። መስፍን በዙ በኢሜይልና በዩቲዩብ በታማኝ በየነ ላይ እያደረሰ ያለውን በሃሰት የስም ማጥፋትን እስከዛሬ ድረስ ዝም ብዬ ንቄው ትቼው ነበር። ለዚህም ምክንያቴ የዚህን ጀግና አርቲስት ከተኛበት መቀስቀስ ይሆናል በሚል ነው። ሆኖም ግን አቶ መስፍን በጥላሁን ገሠሠ ስም መነገዱን ስለቀጠለበት ከአሁን በኋላ ግን ዝም የምልበት መንገድ አይታየኝም። ለዛሬው የጥላሁን ገሠሠ ልጅ ወ/ሮ ንጹኅብር ታማኝ ለአባቷ ስላደረገው ውለታ በህዝብ ለተወደደው አርቲስት ታማኝ በየነ ክብር ተዘጋጅቶ በነበረው የራት ምሽት ላይ የተናገረችውን ቪድዮ አቀርብላችኋለሁ። በተከታታይ ደግሞ ጥላሁን ገሠሠ አንድ እግሩን ካጣ በኋላ በቨርጂኒያ ውስጥ እየኖረ በነበረበት ወቅት በር እየተዘጋበት ሥራ እየተሄደ፤ በረሃብ ስለተጎዳባቸውና ስላዘነባቸው ጊዜያት፣ ሚኒሶታ ላይ በተደረገ ኮንሰርት የስኳር በሽታ እያለበት በአንድ ቀን 7 “ሬድቡል” (ሃይል ሰጪ መጠጥ) ማን እንዳጠጣው፣ እግሩን ባጣበት ወቅት “አንተ ሰውዬ እዚህ ተወዝፈህ ሶፋው ተቀደደ እኮ..” እያሉ በሞራሉ ሲረማመዱበት ስለነበረው፣ ሌሎችንም ታሪኮችን በማስረጃ በተደገፈ መልኩ “ሆድ ይፍጀው” ስል በውስጤ ይዤው የነበረውን ምስጢሮች ሁሉ አጋልጣለሁ።
ወ/ሮ ንፁህብር፦

No comments:

Post a Comment