FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Saturday, November 2, 2013

“አንድነት” በአባላቶቹ ላይ የሚደርሰው ጥቃት መባባሱን ገለፀ

“አንድነት” በአባላቶቹ ላይ የሚደርሰው ጥቃት መባባሱን ገለፀ
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በአባላቱና በደጋፊዎቹ ላይ የሚደርስባቸው ጥቃትና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ መባባሳቸውን ገለፀ፡፡

ከትላንት በስቲያ ፓርቲው በፅ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት፤ ከ2003 አንስቶ በአባላቱና ደጋፊዎቹ ላይ የደረሱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በዝርዝር አቅርቧል፡፡ ፓርቲው “የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት” በሚል ባወጣው ሰነድ፤ ከተዘረዘሩ ጥቃቶች መካከል:- በድብደባ አካል ማጉደል፣ በህገወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር ማዋል፣ ማሰቃየት፣ ማስፈራራትና መዛት እንዲሁም በማስገደድ መረጃ ከፓርቲያቸው እንዲያመጡ ማድረግ፣ የመኖሪያ ቦታን በህገወጥ መንገድ መበርበር፣ ይዞታና ንብረትን ያለ ካሳ ነጥቆ መውሰድ… የሚሉት ይገኙበታል፡፡

አቶ ደምሴ መንግሥቱና አቶ ገበየሁ ይርዳው የተባሉ የፓርቲው አመራሮች፤ በአባላትና ደጋፊዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደመጣ ጠቁመው፣ ጥቃት የደረሰባቸው አራት አዛውንት አባላቶቻቸው ጉዳታቸውን በአካል በማሳየት በህገመንግስቱ እውቅና የተሰጣቸውን:- በህይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነት እንዲሁም በህግ ፊት እኩል የመታየት ተብለው የተዘረዘሩት መብቶች መጣሳቸውን ገልፀዋል፡፡

http://www.addisadmassnews.com

No comments:

Post a Comment