FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Thursday, August 8, 2013

ለተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ደቡብ ኮርያ ከመጡት 59 ኢትዮጵያዊያን መካከል 38 ጥገኝነት ጠየቁ


Ethiopian Asylum Seekers in Korea
ሰበር ዜና፣ ከስምንት ወር በፊት ለተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ደቡብ ኮርያ ከመጡት 59 ኢትዮጵያዊያን መካከል 38 ኢትዮጵያዊያን የኮርያን መንግስት ጥገኝነት ጠየቁ። ከነዚህ ኢትዮጵያዊያን መካከል ኣንዳንዶቹ በሲቪል ሰርቪስ፣ በባንክ ፣ በግብረ ሰናይ ድርጅቶች፣ በተለያዩ ፋብሪካዎችና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ የሚሰሩ ነበሩ። ጥገኝነት ከጠየቁት መካከል ኣንዱ የኣዲስ ኣበባ ፖሊስ ባልደረባ መሆኑም ታውቋል።
እነዚህ ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ላለፉት ስምንት ወራት በኮርያ መንግስት የተዘጋጀላቸውን ስልጠናዎች ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን የሙያ ስልጠናውን ከጨረሱ በሁዋላ ጥገኝነት ለመጠየቅ መወሰናቸውን ኣሳውቀዋል። ጥገኝነት ለመጠየቅ ያበቃቸውን ነገር ሲገልጹ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰባዊ መብት ጥሰት በመቃወም፣ በግላቸው በሚሰሩባቸው መስሪያ ቤቶች የመንግስት ኣካላት ባደረሱባቸው በደል ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
እነዚህ ወገኖች በኣሁኑ ሰኣት ፒናን በተሰኘ የመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ሲሆን በኮርያ ቆይታቸው ሃገራቸውን ከኣምባገነን ኣገዛዝ ለማላቀቅ ከሚታገሉ ሃቀኛ ድርጅቶች ጋር ኣብረው በቆራጥነት ለመታገል መወሰናቸውን በኣንድ ድምጽ ገልጸዋል። ስለተሰጣቸው ስልጠና የኮርያን መንግስት ኣመስግነው ወደፊት ለሚያደርጉት የነጻነት ትግል የኮርያ መንግስት ድጋፍ እንደማይለያቸው ተስፋቸውን ገልጸዋል።
ተጨማሪ መረጃ ለሚሹ ወገኖች ከጥገኝነት ጠያቂዎቹ መካከል የቡድኑን ተወካዩች በስልክ መግኘት ይቻላል።
ሲሳይ ወልደግብሬል 821059503443
ቶማስ ኣሻሜ 821059506511
ኣልዓዛር ስዩም 821059503443
ከኣክብሮት ጋር
ገለታው ዘለቀ
Ethiopian Asylum Seekers in Korea 1

No comments:

Post a Comment