FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Saturday, August 31, 2013

ከስልጣን የተነሳው የደህንነት ሹም፣ እስር ቤት ተወረወረ!!

(ኢ.ኤም.ኤፍ) የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በህይወት በነበረበት ወቅት፤ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ምክትል የደህንነት ሹም ሆኖ ይሰራ ነበር። ወልደስላሴ የህወሃት ታጋይ የነበረ ሲሆን፤ በትግላቸው ወቅት… ወንድ እና ሴት ታጋዮችን “ፍቅር ስትሰሩ ተገኝታችኋል” በማለት ብዙዎችን በመረሸን  ይታወቃል። ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ፤ የመለስ ዜናዊ ክርስትና እናት ልጅ የሆነው፤ ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ የቤተ መንግስቱ ዋና ኃላፊ፣  ወልደስላሴ ደግሞ የቀድሞው ደህንነት ሃላፊ ክንፈ ገብረመድህን ረዳት ሆኖ እንዲሰራ ተደርጎ ነበር።
….
አሁን ጌታቸው አሰፋ በፌዴራል መንግስት ደረጃ ያለውን ስልጣን እያደራጀ የመጣ ይመስላል። ከስር ሆኖ የሚያዘው ወልደስላሴ እስር ቤት ገብቷል። ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ ከቤተ መንግስት እየደወለ ት እዛዝ እና መመሪያ አይሰጠውም። ጌታቸው አሰፋ አሁን ነጻ ሰው ነው። ይህ ነጻነቱ የሚቆየው ግን ቀጣዩ የህወሃት/ኢህአዴግ ስብሰባ እስከሚደርስ ይሆናል። እስከዚያው ድረስ ግን እነ ኢሳያስን በአይነ ቁራኛ መጠበቅ አለበት። አዜብ መስፍን ከኢፈርት ስልጣንዋ ወርዳ፤ ስለመለስ ፋውንዴሽን ብቻ እያወራች እንድትኖር እድል ሰጥቷታል። ቢሆንም ግን ህወሃት ውስጥ ሌሎች የጌታቸው አሰፋ ጠላቶች አሉ። እስከሚቀጥለው የህወሃት ስብሰባ እና ሌላ ውጥንቅጥ ድረስ፤ ድራማውን ከዳር ሆነን እናያለን።

No comments:

Post a Comment