FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Wednesday, February 12, 2014

የሳውዲ ጉዳይ … ሰበር የመረጃ ግብአት (ነብዩ ሲራክ)

የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ኋላፊ ቆንስል ጀኔራል አቶ ዘነበ ከበደ ከኃላፊነታቸው ተነሱ !

* ትናንት ረፋዱ ላይ በገደምዳሜ “ጉልቻ ቢቀያየር …” ብለን ያንሹካሾክነው መረጃ ተረጋገጠ !
* ለጊዜው ቆንስል ጀኔራሉን ተክተው በጊዜያዊነት ቆንስል መስሪያ ቤቱን ለቀጣይ ሁለት ወራት የሚያስተዳድሩት በቆራጥ አመራራር ብቃታቸው የማይመሰገኑት ቆንስል ሸሪፍ ከይሩ ናቸውም ተብሏል ።Ato Zenabe Kebda
* ቆንስል ጀኔራል አቶ ዘነበ ከበደ ትናነት ምሽት ጉዳዩን ለማሳወቅ የኢህአዴግ ድርጅት አባላት ስብሰባ ጠርተው እንደነበርና አብዛኛው አለመገኘታቸው ታውቋል። ድርጅት አባላት በተለይም ከጎናቸው የማይጠፉ የነበሩት ተጽዕኖ ፈጣሪ የህወሃት አባላት እንኳ አልተገኙም ተብሏል።
* አቶ ዘነበ ከበደ በቆንስሉ ዙሪያ የህወሃት አባላትን አምባገነንነትን በማውረድና በማቀዝቀዝ ፣ በሙስና ፣ በድለላ ፣ በማጭበርበር ስራ በቆንስሉ ዙሪያ የነበሩትን በማጥፋት እና በሌብነት አካባቢውን በማጽዳት ይታወቃሉ።
* ህግ አዋቂ ሆነው በህግ ማዕቀፍ የመጡ ዜጎች ግፍ ሲፈጸምባቸው በመከላከሉ የረባ ስራ አልሰሩም የምላች ሃላፊው ስልጣን ከተረከቡ ወዲህ ሶስት ከባባድ የህዝብ ማዕበል የተነሳባቸውን ፈተናዎች በጽናትና በቆራጥ አመራራቸው ድል ነስተው ማለፋቸውን አውቃለሁ። ሃላፊው በአንጻሩ በመረጃ ልውውጥ የማያምኑ ፍትሃዊ በመሆኑ ሳይሆን በግላቸው ላመኑበት ጉዳይ ግንባራቸውን የሚሰጡ ኋላፊ ነበሩ ።
* አቶ ዘነበ ከበደ በሳውዲ ከፍተኛ ሃላፊዎች ዘንድ ክብር የሚሰጣቸው በአማርኛም ሲናገሩ ወጋቸውን ለማስረዳት ተረት የሚያበዙ ፣ ከዚህ በፊት ከነበሩት ኃላፊዎች እንግሊዝኛ አቀላጥፈው የሚናገሩ አንደበተ ርቱዕ ግርማ ሞገስ ያላቸው ፣ በአለባበሳቸው ጸዳ ያሉ ትክክለኛ የአንድ ሃገር ዲፕሎማት ክብርን የተጎናጸፉ ኃላፊ ነበሩ ።
* ከግማሽ ሚሊዮን የማያንሱ ኢትዮጵያውያን የኮንትራት ሰራተኞች ባለፉት ሶስትና አራት አመታት የገቡ ሲሆነ ኮንትራት ሰራተኞች ስለመጡበት ውል አቶ ዘነበ በጀርመን ራዲዮ ውይይት ፕሮግራም ተጠይቀው በኢትዮጵያና በሳውዲ በመንግስት መካከል የሁለትዮሽ የስራተኛ ልውውጥ ስምምነት አንደሌለ በግላጭ የነገሩን ኀላፊም ናቸው ።
* አቶ ዘነበ ከበደ ከዚህ በፊት በቆንስሉ ውስጥ የነበረውን የበከተ ቢሮክራሲና ኢ ፍትሃዊ አመራር በአደባባይ የተናገሩ ደፋርም ናቸው። ነዋሪው በግዳጅ ምንም የገንዘብ መዋጮ ሲጠይቁ ያልተሰሙ ፣ ኮሚኒቲው ያልሆነ ምንገድ ሲሄድ እንደ በላይ ጠባቂነት ኢ ፍትሃዊ አካሔዱን እያዩ ሲያልፉም ታይተዋል። ለዚህ ተጠቃሹ ትምህርት ቤቱ በኮሚኒቲው ለከፋ አደጋ ሲዎድቅ የተመለከቱበት አካሔድ ሲሆን በመጨረሻው ሰአት ገብተው 120 ሽህ የሳውዲ ሪያል ከዝርፊያ አዳንኩ ብለው ቢነግሩንም ዛሬ ድረስ የ3000 ታዳጊዎችና የ200 መምህራንና ሰራተኞች ያቀፈው መመኪያችን በጅዳ የኢትዮጵያውያን አለም አቀፍ ትምህርት ቤቱን ከአደጋ አላወጡትም ። ያም ሆኖ ለትምህርት ቤቱ የተዝረከረከ አሰራር ምክንያትየየተባሉ አንዳንድ መሰረታዊ ለውጦችን ግን በቅርብ ተንቀሳቅሰው አምጥተዋል!
* አቶ ዘነበ ከበደ እንደርሳቸው ጊዜያቸውን ሳይጨርሱ እንደ እርሳቸው ከስልጣን የተነሱትን አምባሳደር መርዋንን እና 12 አመት የጅዳን ቆንስል አንቀጥቅጠው የመሩት የህወሃት ከፍተኛ ሰው አምባሳደር ተክለ አብ ከበደን አስተዳደር ብልሹ አካሔድ ብቻ ሳይሆን የቆንስሉን ሰራተኞች በአደባባይ መመንቀፋቸው በኢህአዴግ የድርጅት አባላትና በሰራተኞች ዘንድ የተፈሩ ሲያደርጋቸው ለዛሬ ከስልጣናቸው መነሳትም የህወሃት አባላት ተጽዕኖ እንዳለበት ራሳቸው ህወሃቶች እየነገሩን ነው። ትናንት አንባሳደር መርዋንን ከስልጣን በማስነሳቱ ረዥም እጅ የነበራቸው ህዎሃትን ጨምሮ የተቀሩት የኢህአዲግ አባል ድርጅቶች ዛሬም በውጭ ጉዳ ከፍተኛ ሃላፊዎች ተጽዕኖ ፈጣሪነት በገሃድ ማሳያው ቀድምው የነገሩን እየደረሰ ማየት መጀመራችን ነው ! ዛሬም ማን ሊመጣ የሚችለው ሃላፊ የዲፕሎማሲያዊ እና የአስተዳደር ብቃት ሳይሆን አነጣጥሮ ተኳሽነቱና የዋለበትን የጦር አውድማ ድረስ በአድናቆት የህወሃት ካድሬዎች ይነግሩን ጀምረዋል።
መዝጊያ …
ለመዝጊያ ፣ ለመደምደሚያ ያህል ትናንት መረጃው ከምጣዱ እንደ ወጣ ስሰማ ያጫወጥኳችሁ አጭር ገደምዳሜ ወግ መዝጊያ መደምደምደሚያ ላድርግ …
ጉልቻ ቢቀያየር …
ከረፋድ እስከ ቀትር ( ትናንት ማክሰኞ መሆኑ ነው) አንዱ መረጃ ከተለያየ አቅጣጫ እዚህም እዚያም ደረሰኝ ፣ በሹክሹክታ ስሰማው የሰነበትኩትን መረጃ እውነትነት ለማረጋገጥ ቢገደኝም የጭምጭምታውን አንድምታ ለማጣራት መሞከሬ አልቀረም። ብዙ ጣርኩ ግን ከመንግስት የቀረቡት ምንጮቸ እያወቁ “አናውቁም ” ያሉኝ ! ወደው ሳይሆን የእንጀራ ነገር ሆኖባቸው እንጅ አዲስ ነገር እንዳለ በከባቢው የሚታየው ድባብ ያሳብቃል … ይህን እያሰብኩ እያለሁ አንድ የማለዳ ወግ ርዕስ ከአፊ ገባ ” ሳያልቅ የተጠናቀቀው ዘመቻና አልረጋ ያለው የጅዳ ቆንስል ወንበር … ” ብየ ጀመርኩት … መቀጠል ግን አልቻልኩም !
በሰሞነኛው በባጀንበት የሳውዲ ኢትዮጵያውያን ክራሞት ዙሪየ የወገን እንግልት የሚያማቸው ወንድም አሉኝ። እኒሁ ከወደ ጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ሁሌም መረጃ የሚያጋሩኝን ወዳጀን ” ሹም ሽር ይደረጋል !” ተበሎ ሰምተው ያልተረጋገጠውን መረጃ ሲያቀብሉኝ “ሰማው ብየ እንጅ ፣ እውነት እንኳ ሆኖ ወንበር ቢቀያየር ምን ዋጋ አለው ፣ ለፖለቲካቸው የሚጠቅማቸውን እንጅ ለስደተኛው የሚፈይደውን አይልኩልን ! ” ነበር ያሉኝ … … ” ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም !” እንዲሉ …
የሚፈለገው ሁሉ ይሆናል … የሚያቆመው የለም ! ለሁሉም አንድየ የሚበጀንን ይስጠን ፣ ከሁሉም በላይ ለሃገራችን ምድር አብቅቶ በሰላም በፍቅርና በህብረት የምንኖርባት ሃገር ፣ መድልኦ የማያውቅ ፣ ሃገርና ህዝቡን የሚወድና ለዜጎቹ መብት የሚቆረቆር መንግስት ይሰጠን …ትናንት የሚፈለገው ሁሉ ይሆናል… የሚያቆመው የለም ብለን ነበር የተለያየነው ! አዎ የሚፈለገው ሁኗል ፣ ይሆናል … የሚያቆመው የለም ! …
” ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይሾማል ፣ የኢህአዴግ የድርጅት አባላትና ካድሬዎች ተጽዕኖ ፈጥረው በተናጠልና ተሰብስበው ያሽሩታል ፣ እንዲህ ተጉዘን የት እንደርስ ይሆን? ” ነበር ያሉኝ አንድ አልረጋ ያለውን የጅዳ ቆንስል ሹም ሽር ያስገረማቸው እህት …
እስኪ ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ
http://ecadforum.com/Amharic/archives/10981/

No comments:

Post a Comment