FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Tuesday, April 15, 2014

በስደትም መሰለል – በኖርዌይ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አሰሙ

“እነሱ ሁለት አገር አላቸው፤ እኛ አገር አልባ ሆነናል”

1


የኢህአዴግን የስለላ መዋቅርና አካሄድ አስመልክቶ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ተበራክተዋል። ኢህአዴግ ራሱን እንደሚስለው ዓይነት ድርጅት ሳይሆን በሰብዓዊ መብት አያያዝ ጉድለት ያለበት፣ በሚዲያ ነጻነት ኋላ ቀር፣ የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን በማሳደድ ግንባር ቀደም፣ አፋኝ ህግ በማውጣትና በማሸማቀቅ ወደር የማይገኝለት፣ ለሚያወጣው ህግና ደንብ የማይገዛ፣ የውስጥ ችግሩ ታይቶ በማይታወቅ መጠን ዜጎችን ለስደት እየዳረገ እንደሆነ እየተመሰከረበት ነው።
ኦባንግ ሜቶ
ኦባንግ ሜቶ
ኢህአዴግን ሸሽተው አገር ለቀው የተሰደዱ በስደት ምድርም ኢህአዴግ እየተፈታተናቸው እንደሆነ መግለጽ ከሰነበቱ ቆይቷል። በአሜሪካ፣ በካናዳ፣ በጀርመን፣ በስዊድንና በእንግሊዝ አገር ስደተኞችን በመሰለል ተግባር ላይ የተሰማሩ “የስደተኛ ሰላዮች” በስፋት ስለመኖራቸው መረጃ ማቅረብ እንደሚችሉ የሚገልጹ ጥቂት አይደሉም። የተለያዩ ድርጅቶች በዚህ ጉዳይ ምን ያህል እንደገፉበት መረጃ ባይወጣም አቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ስራውን ያገባቸዋል ከሚላቸው ክፍሎች ጋር እየሰራ እንደሆነ በዚሁ መድረክ መገለጹ ይታወሳል። በወቅቱ አቶ ኦባንግ “ስደተኛ ሆኖ ስደተኛን መሰለል በህግ የተከለከለ ወንጀል ነውና በዚህ ጉዳይ ርህራሄ ሊኖር አይችልም” ነበር ያሉት።
ማርች 11 ቀን በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር አስተባባሪነት ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዶ ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የፓርላማ ተወካይ፣ የኖአስና/NOASና ዘረኝነትን የሚቃወመው ድርጅት መሪ ተገኝተው ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ተገኝተው ንግግር ካደረጉት መካከል ወ/ት የሺሃረግ በቀለ ይጠቀሳሉ። በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር ጸሐፊ ወ/ት የሺሃረግ በቀለ “እነሱ አገር ቤትም አገር አላቸው፤ በስደትም አገር አላቸው” በማለት ነበር ለጎልጉል አስተያየታቸውን መስጠት የጀመሩት።
yeshihareg
የሺሃረግ በቀለ
በሰልፉ ላይ ካቀረቡት ንግግር በተጨማሪ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡት ጸሐፊዋ፣ ስደተኞች ሁሉ አንድ አይደሉም። “ሆን ተብሎ የስደት መረጃና ማስረጃ ማመልከቻው ተመቻችቶላቸው የሚላኩ የወያኔ ቅጥረኛ ሰላዮች አሉ። እነሱ ባለሁለት አገር ናቸው። እኛ አንድም አገር የለንም” ብለዋል። ይህንን ጉዳይ አቅም በፈቀደ ሁሉ ማህበሩ ከአባላቱና ድጋፍ ከሚሰጡት ሁሉ ጋር በመሆን ከዳር እንደሚያደርሰው ገልጸዋል።
“ልብ እንበል” በማለት አስረግጠው የገለጹት ስለ ሁለተኞቹ ስደተኞች ነው። ስርዓቱ ባለው የግፈኛነት፣ የዘረኛነት፣ የከፋፋይነት፣ የዴሞክራሲና የነጻነት እጦት የገፋቸው እውነተኛ ስደተኞች ባግባቡ መልስ ያለማግኘታቸው ጉዳይ ነው። “እነዚህ እውነተኛ ስደተኞች እኔን ጨምሮ አገር የለንም” ሲሉ አገር አልባ የመሆንን ስሜት ይገልጻሉ። ወ/ት የሺሃረግ የኖርዌይ ሚዲያዎችና በስለላ ተግባር የተሰማሩ “ስደተኞች” እንዳሉ በይፋ ቢናገሩም መንግሥት መልስ አለመስጠቱ ቢያሳዝናቸውም ማህበራቸው ትግሉን ይበልጥ እንዲገፋበት እንዳደረገው ነው የሚናገሩት።
የዲሞክራሲ ለውጥ ድጋፍ ሰጪ በኖርዌይ ተወካይ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ያረጋገጡትን በመጥቀስ ወ/ት የሺሃረግ የትግሉን መደጋገፍ አመላክተዋል። ድጋፍ ሰጪው መረጃ የማሰባሰብ ስራውን ማጠናቀቁን ማረጋገጡ፣ የስደት ከለላ ካገኙ በኋላ በስለላ የተሰማሩትን ክፍሎች አደባባይ ለማውጣት የሚደረገውን ትግል እንደሚያፋጥነው ከምስጋና ጋር እምነታቸውን ገልጸዋል።
3ማህበራቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ባሉበት ሁሉ ወኪሎችን በመሰየም የግንኙነት መረብ መፍጠሩን ያመለከቱት ጸሐፊዋ፣ የግንኙነት ሰንሰለቱ መረጃዎችን በቅርብ ለመሰብሰብ እንደሚረዳ አስታውቀዋል። ላለፉት ሰባት ዓመታት የስደት ማመልከቻቸው አዎንታዊ መልስ እንዳላስገኘላቸው የጠቆሙት ወ/ት የሺሃረግ፣ “እንደ እኔ አይነቶች ብዙ ነን። ከኔም የሚብሱ አሉ። ከሚደርስብን የማህበራዊ ችግር በተደራቢ ካገራችን እንድንባረር ያደረጉን ሰዎች እዚህም እረፍት ሊነሱን አይገባም። አገር አልባ መሆን ያሳዝናል። እዚህ ኖርዌይ የተወለዳችሁ ወገኖችም ብትሆኑ ስደተኞች ናችሁና በመረጃ ማሰባሰቡ ስራ ተባበሩን” ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ቀደም ሲል ለተባበሩትም ምስጋና አቅርበዋል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሙያዊ ምክርም ሆነ አግባብነት ያለው አስተዋጽዖ ለማበርከት ለሚፈልጉ ሁሉ ማህበራቸው በሩ ክፍት እንደሆነም ተናግረዋል።
በኖርዌይ የኢትዮጵያዊ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር አቶ ፋሲል አለባቸው በበኩላቸው በተጠቀሰው ቀን ለተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡ ገልጸዋል። “ሆን ተብሎ የስደት መረጃና ማስረጃ ተመቻችቶላቸው የሚመጡት ሰላዮች የስደት ሂደቱን በማበላሸት እውነተኛ ስደተኞች የከለላ ምላሽ እንዳይሰጣቸው ያደርጋሉ። በዚህ ዜጎች ተጎድተዋል” ሲሉ ለጎልጉል ገልጸዋል።
“እነዚሁ የተመቻቸላቸው ስደተኞች መልስ ካገኙ በኋላ ሆን ብለው ወደ አገራችን መመለስ እንፈልጋለን በማለት የስደተኛ ጉዳይ ለሚያስተናግዱት ክፍሎች የተሳሳተ መረጃ በመስጠት የሌሎች ስደተኞችን ጉዳይ በማበላሸት ስራ ይሳተፋሉ” የሚሉት አቶ ፋሲል አንዳንዴም የተሳሳተ መረጃና የተሳሳተ ምክንያት እንዳቀረቡ በመግለጽ እውነተኛ ስደተኞች ላይ ተጽዕኖ ሊያሳርፍ የሚችል ተግባር እንደሚፈጽሙ አመልክተዋል።2
ከዚህ በተለየ መልኩ ገንዘብ በመላክ /በሃዋላ/ ስራ የተሰማሩ ሰዎች እንዳሏቸው የሚገልጹት አቶ ፋሲል፣ “ወያኔዎቹ ገንዘብ በመላክ ስራ ባሰማሯቸው ሰዎች አማካይነት አገር ቤት ያሉትን ቤተሰቦች በመለየት እንደሚያስፈራሩ ይታወቃል” ሲሉ የትግሉን አስፈላጊነትና ከስደተኞች ማህበር ጥሪ ጎን ስለመቆም ይናገራሉ።
ኮሚኒቲው ለወገኖቹ ጉዳይ ዘወትር እንደሚያደርገው ሁሉ አሁን ለሚደረገው ትግል ከድጋፍ መስጠት ባለፈ አብሮ ለመስራት ዝግጁ እንደሆነ ያሳሰቡት አቶ ፋሲል፣ ማንም ቢሆን ለህግ ሊገዛ እንደሚገባ በሚያስገድድ ስራ ላይ መሰማራት እንደሚኖርበት አመላክተዋል። በማያያዝም አሁን ወደ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ወደ ማህበረሰቡ፣ ወደ አክቲቪስቶችና አቅም ያላቸውን ክፍሎች ግንዛቤ የማስጨበትና ጉዳዩን አጀንዳ አድርጎ የመትከል ስራ ላይ ትኩረት ተደርጎ ስራው እንደሚሰራ አስረድተዋል።
ወ/ት የሺሃረግ የመረጃ ማሰባሰቡ ስራ ሲጠናቀቅ ጉዳዩን ከኖርዌይ የፍትህ ተሟጋች አካላት ጋር በመሆን አስቀድሞ ለፍትህ ሚኒስትር፣ በመቀጠልም በየደረጃው ለሚመለከታቸው ክፍሎችና ለዓለም አቀፍ ተቋማት የማሳወቁ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለጎልጉል ተናግረዋል።
4በሰላማዊ ሰልፉ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ሃሳቡን የደገፉ ተገኝተዋል። አቶ መለስ ለመጨረሻ ጊዜ ኖርዌይ በመጡ ጊዜ የተፈጠረውን ጉዳይ በማስታወስ የስደተኞች ማህበር ቢዘገይም አሁን የደረሰበት ደረጃ ሊበረታታ እንደሚገባ የጠቆሙ አሉ። ስቴንሻዬር የስደተኞች ካምፕ “ስደተኛ” ተብሎ ተመዝግቦ የነበረ እብድ ወጣት አብረውት ካምፕ የሚኖሩ አገር ቤት ያለውን ስርዓት በመቃወም ለህዝብ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ሲሰሩ አብሯቸው ይሳተፍ ነበር። ሲሰለፉና ህወሃትን ሲያወግዙ፣ ኢህአዴግን ሲቃወሙ፣ አብሮ በመሆን እየተቃወመ ቪዲዮ ይቀርጽ ነበር። በመጨረሻ በድንገት ተነስቶ አገር ቤት ተመለሰ።
የልጁ በድንገት መሰወር ያሳባቸው የካምፑ ነዋሪዎች ሲያጣሩ በስም የጠቀሱት ሰው አዲስ አበባ መመለሱ ተረጋገጠ። ከወራት በኋላ አቶ መለስ ኦስሎ ሲመጡ ይኸው ሰው ኦስሎ ተገኘ። በማለት የጠቆሙት ክፍሎች ይህንን ጉዳይ ፖሊስ እንደሚያወቀው፣ ማመልከቻ እንደገባለት አብረውት የነበሩት አሁን ድረስ በስጋት ላይ እንዳሉ ይገልጻሉ።
http://www.goolgule.com/eprdf-tplf-spying-ethiopians-in-norway/

No comments:

Post a Comment