FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Saturday, April 19, 2014

አይ አዜብ!

(ዘመናይ ዘ አራት ኪሎ)

azeb a


አዜብ ሲባል ማን በአዕምሮህ ሊመጣ እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ በውስጥህ ያሰብከው ‹የባለራዕዩን መሪ› ባለቤት አዜብ መስፍንን ከሆነ ለጊዜው ግምትህ አልሰራም፡፡ አሁን አዜብ የምልህ ሌላ ሴት ናቸው፡፡ አዜብ አስናቀን ነው፡፡ (አስናቀ ስልህም እንዳትደነግጥ…የሰው ለሰው ድራማው አስናቀ አይደለም፡፡) ለማነኛውም አዜብ አስናቀ የግልገል ጊቤ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጅ የነበሩትን ሴት ነው እየጠቀስኩልህ ያለሁት፡፡
እና አዜብን እንዴት አነሳኋቸው ካልክ ጉዳዩ ወዲህ ነው፡፡ ሴትዮዋ ከግቤ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅነታቸው ተነስተው ወደ ሌላ ‹ከፍ› ወዳለ ሹመት መጥተዋል፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚነት አድገዋል፡ ፡ ሹመታቸው በቀድሞው ስራ አስፈጻሚ አቶ ምህረት ደበበ ቦታ መሆኑ ነው፡፡ እኒህ ሴት ታዲያ ‹አይ› የሚያስብል ነገር ገጥሟቸዋል፤ ወይም እንዲያ እንድንል አድርገውናል፡፡
ሴትዮዋ ይህን ሹመት ካገኙ ወዲህ የት እንዳሉ ጠፍተዋል፤ ማለቴ ከበፊቱ የበለጠ ስልጣን ይዘው ከበፊቱ ያነሰ ነው ወደ ህዝብ በሚዲያ እየወጡ ያሉት፡፡ ታዲያ በእኒህ አዜብ በተባሉ መሐንዲስ ሴት ምክንያት አንዳንድ ‹ጉድ-ዳዮች› እየተሰሙ ነው እልሃለሁ፡፡ ይህ ኢህአዴግ የሚባል ድርጅት ጉዱ ብዙ ነው መቼም! ድርጅቱ የአራት ውላጆች ጥርቅምም አይደል! እና አልኩህ የእኒህ ሴትዮ አባልነት ወይም ወገንተኝነት ከወዴት እንደሆነ ግራ ያጋባል፡፡
አብረን እንጠይቅ እስኪ…እውነት ሴትዮዋ ለማን ይወግናሉ? ለህወሓት ነው? ለኦህዴድ ነው? ለደኢህዴን ነው? ወይስ ኢህአዴግ የሚባለው ራሱን ችሎ ያለ መስሏቸው ተታለው ነው?! በነገርህ ላይ ብአዴን ብዬ ያለጠየኩት በምክንያት ነው፡፡ ምክንያቱ ምን መሰለህ…ሴትዮዋ ብአዴንን እንደማይወግኑ የታወቀ ጥርጣሬ ነው፤ (የታወቀ ጥርጣሬ ምን ማለት ነው አልክ?)
እውነትም ሴትዮዋ ተታልለዋል! እኔን ካልወገንሽ የሚል አተያይ ይገጥመኛል ብለው የሚገመቱ አልመሰሉም ነበር ማለት ነው! ለዚህ ነው ‹መደበቅ› ያበዙት፡፡ ታዲያ አልኩህ ብአዴን ሆዬ ቦታው ለእኔ ይገባኝ ነበር ብሎ ዘራፍ ለማለት ቃጣው አሉ፡፡ በዚህ ምክንያት አለመግባባቱ አይሏልም እየተባለ ነው፡፡ ምክንያት ህወሓት ማንም ዘራፍ እንዲል አለመፈለጉ ነው! በዚህ ምክንያት እኮ ነው አሉ የመብራት መቆራረጡ የባሰበት፡፡ እንዴ ማን ማንን ይምራ!? ፍትጊያቸውን እንጂ ህዝቡን ማን ልብ ብሎት!
አይ አዜብ! ባላሰቡት መልኩ ፍትጊያውን ተቀላቅለው ቁጭ አሉት፡፡ (ከፍትጊያው ከሌሉበት እንኳ በፍትጊያው ምክንያት ስራቸውን እንዳይሰሩ ተደርገዋል!) አንተዬ እነዚህ ኢህአዴጎች ሊበላሉ እኮ ነው፡፡ (ለነገሩ ህዝብን ብቻ እያኘኩ ከሚኖሩ እርስ በእርሳቸውም ቢናከሱ ይሻላቸዋል፡፡ ድሮስ ጅብና ጅብ መቼ ተስማምቶ በልቶ ያወቃልና!)፡፡ የህዝብ አምላክ መልካሙን ቢያመጣ ያምጣ ብሎ ዝም ያለው ህዝብም አንድ ቀን መነሳቱ አይቀርም፡፡ ያኔ ምን ይውጣቸዋል? ካሁኑ እርስ በእርስ ቢበላሉ ከአደባባዩ ገመና ይሻላቸዋል! ለማነኛውም መሐል ሜዳ ላይ የሚዋልሉት አዜብ ጥግ ቢይዙ ሳይሻላቸው አይቀርም፡፡ ምስኪን አዜብ!
http://www.goolgule.com/oh-azeb/

No comments:

Post a Comment