FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Tuesday, April 30, 2013

አንድነት ፓርቲ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ፔቲሽን ሊያስፈርም ነው



  • digg
  • 135
     
    Share
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በመላ ኢትዮጵያ የሚካሄደውን የዜጎች ማፈናቀል እንዲቆም፣ ተዘዋውሮ የመኖር ዋስትና እንዲረጋገጥ፣ የመስራትና ሀብት የማፍራት መብት እንዲከበር እንዲሁም በሀገሪቱ ያለውን ለከት ያጣ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት በመቃወም የኢትዮጵያ ህዝብ የሚተባበርበትን  ዘመቻ ጀመረ፡፡
UDJይህንን አስመልክቶ የህዝብ ግንኙነት ክፍል እንደገለፀው ይህንን ሀገራዊ ዘመቻ በበላይነት የሚመራው የፓርቲው የፖለቲካ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሲሆን ዕቅድ በመንደፍ ተግባራዊ ለማድረግ የተግባር ኮሚቴ አቋቁሟል፡፡
በዕቅዱም መሰረት ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሀገራዊ ዋስትና እንዲኖራቸውና መብታቸውን ማስጠበቅ የሚችሉባቸውን ዕቅዶች አውጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት በቅድሚያ ሀገራዊ ይዘት ያለውን ማፈናቀል ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም፤ የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ እንዲመለሱና ካሳ የሚገባቸውም ተገቢ ካሳ እንዲፈፀምላቸው፤ ወንጀለኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ ለማድረግ ፔቲሽን በማስፈረም ወደሚመለከተው አካል ማስገባት ቀዳሚው ነው፡፡ በተጨማሪም በሀገራቀፍ ደረጃ ምሁራን የተሳተፉበት የፓናል ውይይት በማካሄድ ከሙህራኑ የመፍትሄ አቅጣጫ የሚጠበቅ ሲሆን በሀገራቸው ጉዳይ ተሳታፊ ማድረግ ሌላው ዓላማ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር ህዝቡ መብቱን ለማስከበር እንዲችል ህዝባዊ ውይይቶችና ሰላማዊ ሰልፎች የሚደረጉበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ከህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

No comments:

Post a Comment