FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Wednesday, April 24, 2013

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ቤንሻንጉሉ መፈናቀል ተናገሩ


በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የሚገኙ አርሦ አደሮች ሕገወጥ በሆነ መንገድ መፈናቀላቸውን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አረጋገጡ፡፡Haile
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ብዙ ሰው እንደተንገላታበት በተደጋጋሚ የተዘገበበትንና ብዙም ያነጋገረውን ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ የተናገሩት ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የስምንት ወር አፈፅፀም ሪፖርታቸው ወቅት በሰጡት አስተያየት ለድርጊቱ ተጠያቂ በሆኑ የበታች ባለሥልጣናት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቀዋል።
በየትኛውም የሀገሪቱ ክልል የሚገኙ የአመራር አባላት የዜጐችን ሕገመንግሥታዊ የመዘዋወርና የመሥራት መብት እንዲያከብሩም አሳስበዋል።
ለተጨማሪና ዝርዝር ማብራሪያ የተያያዘውን እስክንድር ፍሬው ከአዲስ አበባ የላከውን  ዘገባ ያዳምጡ፡፡

No comments:

Post a Comment