FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Friday, September 13, 2013

ኮሎኔል ሃይማኖት ይፈቱ…! ርዮት አለሙም ትፈታ! (አቤ ቶኪቻው)


ኮሎኔል ሃይማኖት ይፈቱ…! ርዮት አለሙም ትፈታ!
ኮሎኔል ሃይማኖት የአቶ ገብረዋህድ ባለቤት ናቸው፡፡ ከጫካ ታግለው መጥተው ሹመት በሹመት ሆነው “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ምን ሊበላ ነው” ብለው ሲበሉ፣ ሲበሉ፣ ሲበሉ…”የተበሉ” ሴትዮ ናቸው፡፡Abe Tokichaw (Abebe Tolla) the Popular Ethiopian Political Satirist
አቶ ገብረውሃድ ማለት ደግሞ፤ “ስልጣናቸውን በመጠቀም ያከማቹት መሬት ቢሰበሰብ ኤርትራን የሚያክል ሀገር ይወጣዋል እና ትልቁ ስጋት ሰውዬው መሬቱን ለምን ወሰዱ… ሳይሆን ይሄንን መሬት ይዤ የራሴን እድል በራሴ ወስኛለሁ እና የመገንጠል መብቴ ይከበርልኝ እንዳይሉ ነው…” በሚል ሀገሬው ሲያማቸው የነበሩ ግለሰብ ናቸው፡፡
እንግዲህ እኒህ ቱባ ባለስልጣን ቱባ ቱባ ዝርፊያ አድርገዋል ተብለው ሲታሰሩ ባለቤታቸው ኮሌኔል ሃይማኖት ደግሞ የራሳቸውንም የባለቤታቸውም ዝርፊያ ውጤት የሆነውን ንብረት “ለማንኛውም መደበቅ ነው የሚሻለው…” ብለው ሲያሸሹ ተገኝተው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት፡፡
ከላይ ያየነው ከመንግስት ሚዲያዎች እንደሰማነው እና በራሳችን ቋንቋ ተርጉምን እንደፃፍነው ነው፡፡
ይሄን ያክል ከተንደረደርን፤
ኮሎኔል ሃይማኖት አዲሱን አመት በእስር ቤታቸው ድል ያለ ድግስ ደግሰው ቤተሰቦቻቸው እዛው ቃሊቲ ድረስ ሄደውላቸው ያማራቸውን ለብሰው ያሰኛቸውን በልተው ደስ ያላቸውን ጠጥተው ስቀው ተጫውተው ነው ያሳለፉት፡፡
ከሁለት ቀን በፊት ከጋዜጠኛ ርዮት አለሙ ጋር ክፍል የተጋሩት ኮሎኔል ከጋዜጠኛይቱ ጋር ከተገናኙበት ቀን አንስቶ “ቀልባቸው አልወደዳትም” ይዝቱባታል፡፡ ይሰድቧታል፡፡ ያንጓጥጧታል፡፡ ለዚህ ደግሞ የስጋ ዘመዳቸው የሆነችው የቃሊቲ ሴት ዋርዲያዎች ሃላፊ አሚናዘር “እሰይ አበጀሽ የኛ ልጅ” ብላላቸዋለች፡፡
“ሙስና ይብቃ” ብላ ስትፅፍ ተገኝታ በቁጥጥር ስር የዋለችው ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ፤ ከእናት እና ከአባቷ ውጪ ሌላ ሰው ማናገር አትችይም ተብላ ስትከለከል፤ ሙስና ይስፋ ብለው በሙስና የተዘረፈ ንብረቶችን ሲያሸሹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኮሎኔል ያለ የሌለ ሃይላቸውን ተጠቅመው ሊያበሳጯት እየተጉ ነው፡፡ ለዚህም አበል እንዲሆን በዓልን እስር ቤቱ መኖሪያ ቤታቸው እስኪመስል ድረስ አሸብርቀውበት ውለዋል፡፡
በተቃራኒው ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ በዓሉን በርሃብ አድማ አሳልፋለች፡፡ እንደ ኮለኔሏ እና እንደ ዋርዲያዎቹ ዛቻ ከሆነ ርዮት አለሙን በተለያየ ዘዴ ምግብ መመረዝን ጨምሮ ጥቃት ሊያደርሱባት እንደሚችሉ… ዝተውባታል፡፡
ኮሎኖል ሃይማኖትን ያሰራቸው አካል በጥፋታቸው እስር አስሯቸው ይሁን በስልጣናቸው ስራ እያሰራቸው ይሁን ግራ ተጋብተን እንገኛለን! ማሰሩ ከሆነ ግን፤ ይሄ እስር ሙስናን የሚዋጋ ሳይሆን ጭራሽ በሙስና የሚያስወጋ ነውና እና ዛሬውኑ ይፈቱልን! ጋዜጠኛ ርዮት አለሙም ትፈታልን! ሌላው ይቅር …ቢያንስ እስር ቤት ውስጥ ድጋሚ መታሰሯ ይቁም!

No comments:

Post a Comment