FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Tuesday, September 24, 2013

በሳውዲ ወላጆችና የኤምባሲ ኃላፊዎች ተካርረዋል

ማቆሚያ ያጣው የኢህአዴግ ጣልቃገብነት

saudi4


ወላጆች ንብረቶቻቸውን ከዘራፊዎች ለማስጣል በሪያድ ከኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ጋር እያደረጉ ያለው ትንቅንቅ ዛሬ ወደ ግጭት አመራ።
በወላጆች እና በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ በዲፕሎማቶች መሃከል ሴፕቴምበር 22፣ 2013 ምሽት ተፈጥሮ የነበረው ግጭት ለጊዜው ጋብ ቢልም መንግስት በጉዳዩ ጣልቃ ገብቶ የተማሪዎቹ ወላጆች በተደጋጋሚ ላቀረቡት ጥያቄ አስቸኳይ መላምት ካላፈላለገ ጉዳዩ የከፋ ሊሆን እንደሚችል የወላጆች ኮሚቴ አባላት ይገልጻሉ!
በተለይ ዛሬ ሴፕቴምበር 22/2013 ምሽት በሪያድ ዓለምአቀፍ የኮሚኒቲ ት/ቤት ተማሪ ወላጆች ኮሚቴ የሳውዲ መንግስት በውጭ ሃገር ዜጎች ላይ ያወጣውን ህግ ተከትሎ በኤምባሲው የተመረጠው የት/ቤቱ ህገወጥ፣ የቦርድ አስተዳደር «የመኖሪያ ፈቃድ አልተሞላም፣ ፓስፖርት አልታደሰም፣ ቦንድ አልገዛችሁም፣ ወላጆቻችሁ የድምጻችን ይሰማ ደጋፊዎች ናቸው፣ … ወዘተ» በጣም አሳዛኝ እና ግብረገብነት በጎደለው ሰንካላ ምክንያት ከ1ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው ማፈናቀሉ ይታወሳል።
saudi3በመሆኑም የአያሌ ኢትዮጵያውያን ህጻናት በሰው ሃገር ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀል የአብዛኛውን ወላጆች በልጆቻቸው ላይ ያላቸው ተስፋ እንዲጨልም አድርጓ። ይህንንም የተረዳው 11 አባላት ያሉት የት/ቤቱ የወላጆች ኮሚቴ ከ1ሺህ የሚበልጥ የድጋፍ ፊርማ በማሰባሰብ ኤምባሲው በራሱ ስልጣን መርጦ ህገወጥ በሆነ መንገድ ያስቀመጠው የት/ቤቱ ቦርድ አዲስ የትምህርት ዘመን መጀመርን አስመክቶ ያወጣውን የአዲስ እና ነባር ተማሪዎች መመዝገቢያ መመዘኛዎች ትክክለኝነት በመጠራጠር ኮሚቴው የሳውዲ ት/ሚኒስቴር መ/ቤት ድረስ በመሄድ ለማጣራት ባደረገው ሙከራ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች በእጅ አዙር እንዳይመዘገቡ ታግደው ከነበሩ 1ሺህ ኢትዮጵያውያን ህጻናት ውስጥ 8 መቶው የሳውዲ ት/ሚ ያወጣውን ህግ የሚያሟሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ፡ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ኮሚቴው ማስቻሉን ተከትሎ ወላጆች በተጠቀሰው ቦርድ እና ከቦርዱ ጀርባ ሆነው በሪያድ ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ት/ቤትን የመማር ማስተማር ሂደት እያመሰቃቀሉ ባሉ ወገኖች ዙሪያ ለመነጋገር ሴፕቴምበር 22 ፣2013 የወላጅ ኮሚቴው በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ ስብሰባ ጠርቶ እንደ ነበር የወላጆች ኮሚቴ ተወካይ ይገልጻሉ።
ተወካዩም በማያያዝ ቀደም ብለው ስብሰባ ያደርጉባቸው የነበሩ ቦታዎች ወላጆች በግል በሚከራይዋቸው አካባቢያቸው በሚገኙ የመዝናኛ ቦታዎች መሆኑንን ጠቀሰው በሪያድ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ሃላፊ የሆኑት አቶ ተመስገን ኡመር ይህ አዳራሽ እያለ ለምን ለድህነታችሁ አስተማማኝ ያልሆነ ቦታ ትሰበሰባላችሁ ከኤምባሲው እና ከኮሚኒቲው ርቃችሁ በድብቅ ስብሰባ ለምን ታደርጋላችሁ በሚል ቅን አስተሳሰብ ለወላጆ ኮሚቴው በሰጡት ሞራል እና ምክር ኮሚቴው ለእሁድ ቀን ሴፕቴምበር 22 2013 ከምሽቱ 7 ስዓት ጀምሮ ወላጆች በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ፡ እንዲገኙ የስብሰባ ጥሪ በደብዳቤ እንደበተኑ ያወጋሉ።
እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ ምንም አይነት ተቃውሞ ከኤምባሲው እንዳልነበረ የሚናገሩት የወላጅ ኮሚቴው ተወካይ በስበሰባው እለት ወላጆችን ለማስተናገድ ኮሚኒቲው አካባቢ ወንበሮችን ስናስተካክል ውለን ለተለዩ ጉዳዩች ከግቢ ወጥተን ስንመለስ የግቢው በር ያለወትሮው በቁልፍ ተቆልፎ ጠበቀን። ጉዳዩን ለማጣራት ዘበኛውን በመስኮት ስንጠይቅ በአምባሳደር መሃመድ ሃሰን በተደገፈ ፊርማ በተጻፈ የደብዳቤ ትዕዛዝ መዘጋቱን ቢገልጽም በወቅቱ ጥሪ የተደረገላቸው ወላጆች ቁጥር እየጨመረ መምጣት አካቢው ተሽከርካሪ መተላለፊያ በመሆኑ ወላጆች ለአደጋ እንዳይዳረጉ ጠቅሰን በገዛ ቤታችን በር እንዲከፈትልን ብንማፀንም ዘበኛው ጉዳዩ ከአቅሙ በላይ ስለነበር ፈቃደኛ አልነበረም ብለዋል።
የኮሚኒቲው ሊቀመንበር አቶ ሙስጠፋ ሁሴን መጥተው በቁጣ የሚጉርመረመውን ወላጅ ለማረጋጋት ሙከራ በማድረግ የኮሚኒቲውን በር እንደሚከፍቱ እና ህዝቡ እንደሚገባ ቃል ገብተው ዲፕሎማቱን አነጋግሬ መጣሁ ብለው ህዝቡን በር ላይ አቁመው በዛው መቀረታቸው አስነዋሪ እና አንድ የኮሚኒቲ ተወካይ ከሆነ አካል የሚጠበቅ አለመሆኑን ገልጸዋል።
ከሰአታት ቆይታ በኋላ አልፎ አልፎ አምባሳደር መሃመድ ሃሰንን ወክለው እንደሚሰሩ የሚነገርላቸው ዲፕሎማት አቶ ዘላለም እና ቀደም ሲል በአዳራሹ እንደ ዜጋ መገልገል «መሰብሰብ» መብታችን መሆኑንን ምክራቸውን ሲለግሱ የነበሩ የዲያስፖራው ሃላፊ አቶ ተመስገን ኡመር በወቅቱ ህዝቡን ለማነጋገር መጥተው እንደ ነበር ቢታወቅም የህዝቡ ስሜት ጥሩ አለመሆኑ መንገድ ላይ እያሉ መረጃ ስለደረሳቸው እና በአንዳንድ ትእግስታቸው በተሟጠጠ ወላጆች በገዛ ቤታችን እንዴት እንከለከላለን በሚል ቁጣ እና ንዴት ሊፈጸምባቸው የሚችለውን እርምጃ በመስጋት በት/ቤቱ የጓሮ በር ድምጻቸውን አጥፈተው በመግባት ህዝቡ ከአካባቢው እስኪበትን እዛው ባሉበት ድምጻቸውን አጥፈተው ለመቆየት መገደዳቸውን የአይን ምስክሮች ገልጸዋል።
በመጨረሻ የወላጆች ኮሚቴው ወደፊት ተመሳሳይ የሆነ ስብሰባ እንደሚጠራ ጠቅሷል፤ ህዝቡ እልህ ውስጥ ሳይገባ በሰከነ መንፈስ እና ህጋዊ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ አይን ባልገለጹ ሃገር ተረካቢ ታዳጊ ህጻናት ልጆቹ ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት እና ንብረቱ የሆነውን በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ት/ቤት ከዘራፊዎች ለማዳን እያደረገ ያለውን ትግል አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመገስጽ የኢትዮጵያ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ስጥቶ አስቸኳይ የሆነ መፍትሄ እስካላበጀለት ድረስ በዲፕሎማቱ እና በተማሪ ወላጆች መሃከል የተፈጠረው ግጭት ወደ ከፋ ደረጃ እንደሚሸጋገር አበክረው አሳስበዋል።
Ethiopian Hagere ከሳውዲ አረቢያ ጅዳ በዋዲ በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት

No comments:

Post a Comment