FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Friday, September 20, 2013

አዳፍኔ ለመተኮስ የ “iPad” ዕገዛ


iPad to fire


ከአንድ መቶ ሺ በላይ ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለውና እጅግ ደም አፋሳሽ በሆነው የሶሪያ የእርስበርስ ጦርነት የአማጺያኑ ኃይል ከሚጠቀመው ቤት ሰራሽ መሣሪያዎች ሌላ የቴክኖሎጂ እሴቶችን በመቀላቀል የሚጠቀሙ መሆኑ ተገለጸ፡፡
የሬውተር ዘጋቢ የሆነው መሐመድ አብደላ ባነሳው በዚህ ፎቶ ላይ እንደሚታየው የነጻ ሶሪያ ሠራዊት አማጺያን ከደማስቆ ወጣ ብሎ በሚገኝ ቦታ ላይ አዳፍኔ ለመተኮስ በ iPad ሲታገዙ ይታያል፡፡
የጦር መሣሪያ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ አማጺያኑ በፎቶግራፉ ላይ እንደሚታየው በቴክኖሎጂ ቢታገዙም የመተኮሻው ቱቦ አቅጣጫና አቀማመጥ በጣም በቅርብ በሚገኝ ዒላማ ለመምታት አስበው ካልሆነ በስተቀር አዳፍኔውን የሚተኩሱት ራሳቸውን ለማጥፋት ይመስላል፡፡
በምስሉ እንደሚታየው አማጺያኑ በጉዳዩ የረቀቁበት ቢመስልም አነጣጠራቸውና አተኳኮሳቸው “ቦምብ ጥሎ የመጸለይ” ዓይነት ይመስላል በማለት በጉዳዩ ላይ ዕውቀት ያላቸው የጦር መሣሪያ ባለሙያ በምጸት ለሬውተርስ ተናግረዋል፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)
(ፎቶ፡ በነጻ ሶሪያ ሠራዊት ሥር የአሱድ አላህ ብርጌድ አካል የሆነው የአንሳር ዲማክ ብርጌድ አባላት “iPad” በመጠቀም ደማስቆ፤ ጆባር አካባቢ ቤት ሰራሽ አዳፍኔ ሲተኩሱ፤ መስከረም 5፤2006፡፡ ሬውተርስ)

No comments:

Post a Comment