FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Monday, July 22, 2013

ግዙፉ የጀሞ ኮንዶሚኒየም ዘምሟል

የ10/90፤ 20/80 እና 40/60 ችብቸባው ቀጥሏል
jemo


አጠገብ ያሉ ሕንፃዎች ውስጥ የሚኖሩ እንዲለቁ ተነገራቸው
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥናት ለማድረግ ስምምነት ሊያደርግ ነው
በግዙፉ የጀሞ የጋራ መኖሪያ ሕንፃዎች መንደር ውስጥ በአንድ በኩል በመስመጥ ላይ ከሚገኘው ኮንዶሚኒየም ሕንፃ ግራና ቀኝ የሚገኙ ሕንፃዎች ውስጥ የሚኖሩ ነዋሪዎች ከሕንፃው እንዲለቁ ተነገራቸው፡፡
በሁለቱ ሕንፃዎች ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች ከሕንፃዎቹ እንዲለቁ የተጠየቁት በክፍለ ከተማው የቤቶች ልማት ጽሕፈት ቤት አማካይነት መሆኑን፣ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
የውሳኔው መነሻ ወደ አንድ ጐን በማዘንበል ላይ የሚገኘው ሕንፃ አጠገብ ያሉት ሁለት ሕንፃዎች ተመሳሳይ ችግር አለባቸው በሚል ቢሆንም፣ በሕንፃዎቹ ላይ በዓይን የሚታይ ችግር መኖሩን ለማረጋገጥ አስቸጋሪ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሁለቱ ሕንፃዎች ተመሳሳይ መሰነጣጠቅ በውስጥ አካላቸው ቢኖርም፣ መሰነጣጠቁ መቼ እንደተፈጠረ በእርግጠኝነት መናገር የሕንፃዎቹ ነዋሪዎች አይችሉም፡፡ በጉዳዩ ላይ መረጃ እንዲሰጡ የአዲስ አበባ የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ ካሣ ወንድሙ ተጠይቀው፣ ስለተጠቀሱት ሕንፃ ነዋሪዎች የሰሙት ነገር እንደሌለ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን ነዋሪዎቹ በክፍለ ከተማው እንዲለቁና ተለዋጭ መኖሪያ ቤት እንዲወስዱ እንደተነገራቸው ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
ችግር በታየበት ሕንፃ ላይ ይኖሩ የነበሩ ሁሉም ነዋሪዎች በአሁኑ ወቅት  ተለዋጭ ቤት እንደተሰጣቸው ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
በሕንፃው ላይ የተፈጠረው ችግር እንዲጠና በዚህ ሳምንት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር ውል እንደሚፈረም ያስረዱት አቶ ካሣ፣ ጥናቱ የጂኦ ቴክኒካል፣ የኮንትራክሽንና ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን እንደሚያካትት አረጋግጠዋል፡፡
ጥናቱ ችግር ባለበት አንድ ሕንፃ ላይ ብቻ የሚከናወን ሳይሆን በጠቅላላ የጋራ መንደሩ ላይ እንደሚሆንም አስረድተዋል፡፡ (ሪፖርተር)

No comments:

Post a Comment