FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Wednesday, July 3, 2013

ለጅምላ ጭፍጨፋ ህጋዊ ሽፋን?


በእስከ ነጻነት
  • ሰሞኑን በጣም እጅግ በጣም አስደናቂ፣ አስገራሚና ዘግናኝ ዜናዎች እየተሰማ ነው።
  • በርግጥ ለትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር አዲስ ነገር አደለም ሊሆንም አይችልም።
የህወሃትን ባህርይ ለምናውቅና የነጻውን አለም ህይወትና ሰብአዊ መብት አክብሮት ለቀመስነው ግን በጣም እጅግ በጣም የሚያስገርም፤ የሚያስደነግጥ: ከዚያም አልፎ  ይህን መቀበልና መዚህ መቀጠል አንችልም  ወያኔ ካልጠፋ ስራም: ኑሮም፤ ትምህርትም እምነትም የለም ክተት የሚያሰኝ ነው:
ዜናው እ አ አቆጣጠር ሰኔ 26 2013 በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዠን  (እኔ  የኢትዮጵያ ሳተላይት መገናኛ፣ Ethiopian Satellite media) ብዬ ብጠራው ደስ ይለኛል) ባስተላለፈው ዜና፡ የወያኔው የደህንነት አባላት ለሚፈጽሙት ማንኛውም ጥፋት በወንጀልም ሆነ በፍታብሄር አይጠየቁም የሚል የህግ ረቂቅ ለምክር ቤት መቅረቡን አርድቶን ነበር። ይሁን እንጂ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? እንዴት ጅምላ ጭፍጨፋ የህግ ሽፋን ሊሰጠው ይችላል በሚል ጥርጣሬ ተወጥረን እያለ፡  ነገሩ እኛ ያሰብነው ሳይሆን ወያኔ ያቀደው ሆነና በዛሬው እለት የትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር ታጣቂዎች ለሚፈጽሙት ጅምላ ጭፍጨፋ ወይም ንብረት ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት በወንጀልም ሆነ በፍታብሄር አይጠየቁም የሚል ህግ ባሻንጉሊት ስብስቦች አስጸድቋል፡ ነፃ  እርምጃ ባገሪቱ ታውጇል፡ ለትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር ጸጥ ለጥ ብለህ ካልተገዛህ ባደባባይ ትረሸናለህ፤ ለሞትህም ሆነ ለመቁሰልህ ማንም አይጠየቅም፡የሚል ቀጭን ትዛዝ እና አዋጅ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ተጭኗል።
ይህ ማለት ምን ማለት ነው? አብረው እየተከናወኑ ያሉት አባሪ ተግባራትስ ምንድናቸው?
በዝርዝር ሳይሆን ጠቅለልና አጠር ያለ የወያኔ ተግባራትን  ወደሗላ መለስ ብሎ መቃኘት አስፈላጊ ይሆናል፡
ህውሃት ገና የዕኩይ ጥንስሱ ሳይፈላ በስብሃት ነጋ አጋፋሪነት የመጀመሪያ አገራዊ አንድነትን ለመናድ ቅድመ ሁኔታዎችን ሲያመቻች የበረሃ ሲኖዶስ ማቋቋምና፤ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን በእምነቱ በጎለበቱና በጸኑ አባቶች ሳይሆን በህውሃት ካድሬዎች እንዲያዝ በረሃ ስልጠና መሰጠቱንና ካድሬዎች የመነኩሴ ልብስ ለብሰው በየገዳማቱ ያሉትን መናኝ ባሃታዊያን፤ መነኩሳትን፤ አረጋውያን ካህናትን አፍነው፤ ገድለው መጨረሳቸውንና አዲስ አበባም ሲደርሱ ዋናውን ፓትርያርክ ከነባር ካደሬዎች አንዱን አባ ገ/ማርያምን ማስቀመጣቸውን ቤተ ማህቶት እ. አ. አቆጣጠር ጥር 23 2013 ምስጢራዊው የበረሃው ሲኖዶስና የማህ በረ ቅዱሳን ፓትርያርክ፣ ከአብየ አዲ እስከ አዲስ አበባ በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ በሚገባ ዘርዝረው፤ ዋቤ አጣቅሰው አሰቀምጠውታል:   
በዛ ወቅት እነስበሃት ነጋ  ለእስልምና እምነት ተከታዮች የተሳሳተ ግንዛቤ ነበራቸው ብዬ እገምታለሁ፡  በነስ ቁንጽልና በጥላቻ የተቃኘ ህሊና ኢትዮጵያ የአማራና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ብቻ፤ ስለኢትዮጵያ የሚጨነቁ አማሮችና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ናቸው ብለው ራሳቸው የፈጠሩትን ውሽት አምነው፤ የእስልምና ተከታይ ወገኖቻችንን በቀላሉ መቀየር፤ እንችላለን ከሚል ግምት በመነሳት በረሃ እያሉ ያላሰቡበትን አሁን ግን በቀላሉ ልንተገብረው እንችላለን ከሚል ንቀት ተነሳስተው የሃባሽን እምነት ተከተሉ የሚል በየትም አለም ታይቶና ተሰምቶ የማይታውቅ እኔ የሰጠሗችሁን እመኑ የሚል ትእዛዝ ሊጭንባቸው ሞክረዋል። የእስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን ናቸውና፤ እንደነ ስብሃት፤ መለስና  መሰሎች የባንዳ ቅርንጫፍ አደሉምና፤ ሃገር የመናድ ፍላጎትም ሆነ ተንዳ የማየት ፍላጎት የላቸውምና ዞር በል አሏቸው፡ ተቃውሟቸውንም በሰላማዊ ድምጻችን ይሰማ ሲሉ አቤት ሲሉ ሁለት አመት ሊሞላቸው ጥቂት ወራት ብቻ ቀራቸው።Ethiopian government abusing and torches Ethiopian Muslims.
በእበሪት የተወጠረው ወያኔ ይህን ሁለተኛ አመቱን የያዘውን  እምነቴን አንተ አትመርጥልኝም የሚለውን ሰላማዊ ተቃውሞ በሰላማዊ መንገድ እልባት እንደመሰጠት መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን በሃሰት ወንጅሎ እንደለመደው በሃይል ለመጨፍለቅ  የእስልምና እምነት ተከታዮች ያልሆኑ ግን ልክ በረሃ ካድሬ መነኩሳትን እንዳስተማረና የኦርቶዶክስ ቤት ክርስቲያንን እንደተቆጣጠረ ሁሉ አሁንም በስለላ የሰለጠኑ አረብኛ ቋንቋን የተማሩና ቁርአንን የቀሩ 987 በእስራኤል የሰለጠኑ የደህንነት አባላት በየመስጊዶቹ ማሰማራቱን እየሰማን ነው። እነዚህ የደህንነት ሰላዮች በየመስጊዱ  የሚሰማሩት መስጊድ ሊያረክሱ፤ ብጥብጥ ሊያስነሱ፤ ከዛም የሚፈልጉትን ለማጥፋት፤ ለመግደል የተዘጋጁ መሆናቸውን የሚጠራጠር ያለ አይመስለኝም፡
ሼሆችን፤ ይማሞችን ቢገሉ፤ መስጊድ ቢያቃጥሉ በወንጀልም ሆነ በፍታብሄር እንደማይጠየቁ በህግ ተረጋግጦላቸዋል፡
የሚገርው ደግሞ  እስራኤል ከሰለጠኑት 987 ሰላዮች መካከል የእሰልምና ተከታዮች 11 ብቻ መሆናቸው ነው፡ (11 ግን ምትሃታዊ ቁጥር ነች እንዴ? የኢኮኖሚ እድገት 11% ሌላም፡ ይቺ  እንኳ ለፈገግታ ነች እልፏት) ከነዚህ ስልጣኞች ውስጥ 613ቱ ደግሞ የትገራይ ተወላጆች ናቸው፡ ራሳቸው ባስቀመጡት ስሌት፤ ብሄር ብሄረ ስቦች ቀመር ቢተነተን  ለአንድ ሚሊየን 11 ሰላይ ሂሳብ ማለት ነው፡ በዚህ ሂሳብ ሲሰላ ትግራይ የሚደርሳት የሰልጣኝ ሰላይ ብዛት 55 ገደማ መሆን ነበረበት፤ አሁን ግን ትግራይ 1115% አንድ ሽህ አንድ መቶ አስራ አምስት በመቶ ድርሻ ወስዳለች ማለት ነው። ከ22 አመት አገዛዝ በሗላ 1115% የደህንነት አባላት ከትግራይ ተመልምለውና ስልጥነው፡ መስጊድ ለመበጥበጥና ስልክ ለመጥለፍ ሲዘጋጁ በምንም መስፈርት አገሪቱን እየገዛ ያለው ኢትዮጵያዊ አገዛዝ ነው የሚል ብዥታ ሊኖር እንዳይችል አድርጎታል፡ የገሃዱ አለም ቁልጭ አርጎ እንዲሚያስረዳው ኢትዮጵያ በትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር የቅኝ አገዛዝ ለመውደቋ ከዚህ በላይ  ማረጋገጫ የሚያስፈልግ አይመስለኝም።
ዋናው ቁጥሩ አደለም፡ የህውሃት ደህንነቶች በጅምላ ለሚፈጁት (በርግጥ ከዚህ ቀደምም ተጠያቂ ሆኖ የሚያውቅ የለም) ለወንጀላቸው ተጠያቂ እንደማይሆኑ መስጊድ፤ ቤተክርስቲያን ቢያቃጥሉ እንደማይጠየቁ፤ የህግ ሽፋን መሰጠቱ የህውሃትን አገር የማፍረስ፤ ዘር የማጥፋት፤ እና ለምንም ተጠያቂነት ሊወስድ አለመፈለጉንና አለመዘጋጀቱን ቁልጭ አርጎ የሚያሳይ ነው፡
በዚህ አጋጣሚ ግን እስራኤል ለአረብ ሃገራት ያላትን ጥላቻ በኢትዮጵያ የአስልምና እምነት  ተከታዮች ላይ ለመወጣት ስላዮችን ማሰልጠኗ ታሪካዊ ስህተት መፈጸሟን ሳልጠቅስ ማለፍ አልፈልግም። ወያኔን ስልጣን ላይ ለማውጣትና ስልጣኑ ላይም ለማቆየት እንግሊዝና አሜሪካ የተጫወቱትን ሚና፤ ሰላዮችንና ያፈና ሰራተኞችን በማስልጠንና ማፈኛ መሳሪያ በመሸጥ ህንድ፤ ቻይና እና እስራኤል ተጠያቂ መሆናቸውን ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሊገነዘቡት ይገባል።፡አሁን አቅሙ ላይኖረን ይችላል ግን የቴክኖሎጂ እድገት ሌላውን ለማጥፋት ያመረቱት መሳሪያ በራሳቸው ላይ ሊውል የሚችልበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፤ እነዚህ ሃገራት አቶ ገ/መድህን አርአያ እንደጠቀሱት ለ8 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን እልቂት ተባባሪ መሆናቸውን መረዳትና መዝግቦ ለትውልድ ማስተላለፍ የያንዳንዱ ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለዚህ በትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር ታጣቂዎች ለግንባሩ የማያጎበድዱትን፡ እንቢ አልገዛም ያሉትን ኢትዮጵያውያን፤ በጅምላ እንዲፈጁ፤ ንብረታቸውን እንዲያቃጥሉ፤ እንዲዘርፉ እና ዘር እንዲያጠፉ ትዕዛዝና የህግ ሽፋን ተሰጥቷቸዋል። ዘር በማጥፋታቸው፤ ህዝብን በመጨረሳቸው፤ ንብረት በማውደማቸው ይሸለሙ እንደሆነ እንጂ በወንጀልም በፍታብሄርም እንደማይጠየቁ ግልጽ ሆኗል፡
የትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር ተግባራዊ ተሞክሮ የሚያስረዳን ደግሞ በጣም ግልጽ ነው፡ በደኖ፤ ወተር፤ አርባ ጉጉ፤ ጋምቤላ፤ አዲስ አበባ፤ አረካ፤ አዋሳ፤ ሸካ ማጂ፤ አሶሳ፤ ጉሙዝ፡ ወልቃይት ጠገዴ ስንቱ ተዘርዝሮ ይዘለቃል፡በነዚህ ቦታዎች ሁሉ ሁሉ ወያኔ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው የፈጸመው። አሁን ይህ በአዋጅ ደረጃ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መሆኑ ግልጽ ነው፡
የትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር በየንዳንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ላይ የሞት ፈርድ አውጆበታል የሚቀረው ተግባራዊ የሚሆንበት ቀን ብቻ ነው።
ስለዚህ የትግሬ ነጻ አውጭ ታጣቂዎች በጅምላ ሲፈጁን ቆመን ሞታችንን እንጠብቅ? እንደ ጅግራ አንገታችንን ሰጥተን እንታረድ ወይስ ይህ ሁሉ ከመድረሱ በፊት እንደ ግብጾች ወያኔ አሁኑኑ ስልጣን እንዲለቅ ህዝባዊ አመጽ እንጀምር፡ አሁን፤ ዛሬ፡ ወያኔ ስልጣን አሁኑኑ ካልለቀቅህ ስራም፤ ትምህርትም፤ ኑሮም፤ እምነትም፤ ሃገርም የለም ብለን እየመከትንና፤ እየተከላከልን እንሙት? ወያኔ ግድያውን ነገ ይጀምራል፡ ጊዜ የለም፡ ያለችው ጊዜ አሁን ይች ቅጽበት ነች።
መልሱን ለያንዳንዳችሁ እተዋለሁ።
እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይጠብቅ
እስከ ነጻነት

No comments:

Post a Comment