FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Monday, November 26, 2012

ከሁለት ልጆቿ ጋር የቤት እመቤቷን ገድለዋል የተባሉ የቅርብ ዘመዶች በቁጥጥር ስር ዋሉ


ህዳር ፲፯ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በሻሸመኔ ከተማ ሀይማኖት ደሳለኝ የተባለች የቤት እመቤት ባለፈው ሀሙስ ማንነቱ ባልታወቀ ግለሰብ በተኛችበት ከሁለት ልጆቿ ጋር በመጥረቢያ ተቆራርጣ የእናትየውና የልጆቹ ምላሶች ተቆርጠውና አይናቸውም ወጥቶ መገደላቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
ከፖሊስ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው በግድያው ከተያዙት መካከል የቤት እመቤቷ እናት አንዷ ናቸው። እናትየው በልጃቸው ላይ ሲዝቱ እንደነበር መታወቁ፣ በለቅሶው ጊዜም አርፍደው መምጣታቸውንና ከሌሊቱ ስድስት ሰአት ላይ ውጭ መታየታቸው ነው ለጥርጣሬ በር ከፍቶ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረገው። ቤቱን ዘግታ የጠፋችው የቤት ሰራተኛም በቁጥጥር ስር ውላለች። የሟችን ሞባይልና አንገት ሀብሎች ይዛ መገኘቱዋንም ከፖሊስ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።   ከሟች እናት ጋር ግንኙነት አለው የተባለ ሌላ ሰውም በቁጥጥር ስር ውሎአል።
የሟች እህት ታስራ መለቀቁዋን ለማወቅ ተችሎአል።

No comments:

Post a Comment