FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Monday, March 18, 2013

ኢትዮጵያና የግለሰቦች ስለላ በኢንተርኔት – ጥናት፣ ክስና ምላሽ


የኢትዮጵያ መንግሥት የኢንተርኔት ማልዌር እየተጠቀመ በተቃዋሚዎች ላይ ስለላ ያካሂዳል ሲሉ በካናዳው ቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲና በዩናይትድ ስቴትሱ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለዶክትሬት ዲግሪ የሚዘጋጁ ሁለት አጥኝዎች ያወጧቸው የክትትል ሪፖርቶች ለሕትመት በቅተዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት የኢንተርኔት ማልዌር እየተጠቀመ በተቃዋሚዎች ላይ ስለላ ያካሂዳል ሲሉ በካናዳው ቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲና በዩናይትድ ስቴትሱ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለዶክትሬት ዲግሪ የሚዘጋጁ ሁለት አጥኝዎች ያወጧቸው የክትትል ሪፖርቶች ለሕትመት በቅተዋል፡፡
ድንበር የለሽ ጋዜጠኞች የሚባለው ፓሪስ-ፈረንሣይ የሚገኘው ዓለምአቀፍ ቡድን ኢትዮጵያ ያንን የርቀት መከታተያ ሶፍትዌር ግለሰቦችን ለመሰለል ጉዳይ እንደምትጠቀም እንደሚያውቅ ቢገልፅም አንድ የኢትዮጵያ የመገናኛና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባለሥልጣን የሚባለውን ክስ አስተባብለዋል፡፡
ሲቲዘን ላብ የሚባለው የካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ማዕከል ባወጣው ዘገባ መሠረት የስለላ ማልዌሩን ኢትዮጵያን ጨምሮ ለሃያ አምስት ሃገሮች የሸጠው ድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ቡድኑ – አርኤስኤፍ “የኢንተርኔት ጠላቶች” ሲል ከፈረጃቸው አምስት ሃገሮችና አምስት ድንበር ዘለል ድርጅቶች አንዱ የሆነው “ጋማ ኢንተርናሽናል” የሚባል ለንደን – እንግሊዝ የሚገኝ በመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፈጠራና ንግድ ላይ የተሠማራ ቡድን ነው፡፡
ጋማ ኢንተርናሽናል ማልዌሩን የሠራውና የሚሸጠው ሕፃናትን የሚያማግጡና ጥቃት የሚያደርሱባቸውን፣ ሽብርተኞችንና የተደራጁ ወንጀሎችን፣ ጠላፊዎችንና ሕገወጥ የሰዎች ሽግግርን ለመከታተል መሆኑን ተናግሯል፡፡ ደንበኞቹ እነማን እንደሆኑ ግን መግለፅ አልፈለገም፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት “ፊንስፓይ” የሚባለውን የጋማውን ማልዌር የሚጠቀመው የግንቦት ሰባት አባላትንና ግንኙነቶቻቸውን ለመከታተልና ለመሰለል ነው የሚለውን የሲቲዘን ላብን ጥቆማ አስመልክቶ የተጠየቀው ግንቦት ሰባት የተባለው ክትትል በአባላቱና በአመራሩ ላይ በኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚካሄድ፣ የአሁኑ የመጀመሪያ ጊዜ አለመሆኑንና ሁኔታውን ለመቆጣጠርና አደጋን ለመከላከል የሚያስችለው የተጠናከረ የመገናኛና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን፣ ባለሙያና አሠራር ያለው መሆኑን አስታውቋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ መንግሥቱን ለመጣል ማንኛውንም የትግል ዘዴ የሚጠቀመው ድርጅታቸው ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የኢንተርኔት ወይም ሳይበር ጦርነት እያካሄደ መሆኑን የግንቦት ሰባት ምክር ቤት ፀሐፊ አቶ አምሣሉ ፅጌ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡ http://amharic.voanews.com/flashaudio.html

No comments:

Post a Comment