FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Wednesday, January 30, 2013

በጉርዳፈርዳ በአማራ ተወላጆች ላይ የሚደርሰው የሰብአዊ መብት ረጋጣ ቀጥሏል


ጥር ፳፪ (ሀያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በደቡብ ኢትዮጵያ ቤንች ማጂ ዞን በጉርዳፈርዳ ወረዳ በአማራ ተወላጆች ላይ የሚደርሰው የሰብአዊ መብት ረገጣ መቀጠሉ ተገለጸ።
በወረዳው ባለፈው ታህሳስ አንዲት የ8 ልጆች እናት በጥይት ሲገደሉ፣ ሁለት ህጻናት በመስተዳድሩ መኪና ተገጭተው መሞታቸውን የመኢአድ ም/ሊ/መንበር አቶ ወንድማገኝ ደነቀ ለኢሳት ገልጸዋል።
ታህሳስ 28/ 2005 ከምሽቱ 4 ሰአት ሲሆን 5 መሳሪያ የታጠቁ ወታደሮች የ8 ልጆች እናት የሆኑትን ወ/ሮ አይቼሽ ስጦታውን በመኖሪያ ቤታቸው እንደገደሉዋቸው ነው ም/ ሊቀመንበሩ የተናገሩት።
ጥር 15 ቀን 2005 ዓ/ም ደግሞ የ4 እና የ7 አመት ህጻናት በመስተዳድሩ መኪና ተገጭተው ህይወታቸው ማለፉን ከአቶ ወንድማገኝ ማብራሪያ ለመረዳት ተችሎአል።
ሌሎች 23 የአማራ ተወላጆች በወህኒ ቤት በመሰቃየት ላይ መሆናቸውንም የመኢአድ ተቀዳሚ ም/ል ሊቀመንበር አክለዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን ለማናገር ብንሞክርም አልተሳካልንም።

No comments:

Post a Comment