FREE ALL POLITICAL PRISONERS

FREE ALL POLITICAL PRISONERS
FREE ALL POLITICAL PRISONERS

Tuesday, January 22, 2013

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ግቢአቸውን ለቀው ወጡ


ጥር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- በባህርዳር ዩኒቨርስቲ ስር በሚገኙት በፔዳ ፣ ፖሊ፣ ይባብና  ዘንዘልማ  ካምፓሶች ይማሩ የነበሩ ከ95 በመቶ ሙስሊም ተማሪዎች ግቢአቸውን ለቀው መውጣታቸውን የተወሰኑትም ወደ መጡበት አካባቢ መመለሳቸውን  ተማሪዎች ገለጹ። ተማሪዎቹ ግቢአቸውን በመልቀቅ ትምህርታቸውን ለማቋረጥ የወሰኑት ከሶስት ሳምንት በፊት የግቢው አስተዳዳሪዎች በዩኒቨርስቲው ውስጥ የሚደረግ ጸሎት እንዲቆም፣ ሴቶች ጂሃብም ኒቃምብ እንዳይለብሱ መከልከላቸውን ተከትሎ ነው።
አንዳንድ ተማሪዎች ከትናንት ጀምረው ትምህርት በማቋረጥ ተቃውሞአቸውን ሲገልጹ የነበረ ቢሆንም፣ የዩኒቨርስቲው አስተዳዳሪዎች “ትእዛዙ ከበላይ አካል የመጣ ነው ምንም ማድረግ አንችልም” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ተማሪዎች ግቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። አንድ ተማሪ እንደገለጸው የተወሰኑ ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለሳቸውን ፣ ሌሎችም ትኬት በመቁረጥ ላይ ናቸው። 

No comments:

Post a Comment